"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Monday, 1 April 2013

አዜብ መስፍንና የቼኮሌቱ ታሪከ


Azeb Mesfin for refusing to leave the palace.
ሰለሞን ታረቀኝ
ድሮ ነው አሉ፤ አንዲት በናዝሬት ትምህርት ቤት ትማር የነበረች ተማሪ ጥርሷን ጣፋጭ ጨርሶት ነበርና ወላጆቿ በፍጹም ቼኮላት እንዳትበላ ያስጠነቅቋታል፤ ከዚያም አንድ ቀን አንዲት ጓደኛዋ ቼኮሌት አምጥታ ኖሮ በእረፍት ሰዓታቸው ጓደኛዋ የሰጠቻትን ጥቂት ቼኮሌት ታናሽ ወንድሟ እንዳያሳብቅባት ተደብቃ ስትበላ ያ ከውካዋ ወንድሟ ድንገት ቢደርስባት እጅዋ ላይ የቀረውን በድንጋጤ ወደ አፍዋ አስግብታ ቁልቁል መስደድ፤ ወንድምየውም ቼኮሌት እንድትሰጠው ቢጠይቃት እንዳለቀባት ትነግረዋለች። እሱም ይናደድና አሳብቃለሁ ብሎ ያስፈራራታል። ከዚያም ከትምህርት ቤት ወጥተው ቤታቸው እንደደርሱ ወንድሟን ለመቅደም ብላ ማንም ሳይጠይቃት፥ እማዬ፥ እማዬ እኔ እኮ ዛሬ ቼኮሌት አልበላሁም አለች ይባላል።
የቀድሞዋ ቀዳማዊትም እንዲሁ ቀደም ቀደም ብላ ሳትጠየቅ ተክለፍልፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባሌ የ፮ ሺህ ብር የወር ደመወዝተኛ፥ ከዚህም ተቆራርጦ ፬ ሺህ ብር ያገኝ ነበር ስትል አበሰረችን። የቼኮሌቱ አይነት መሆኑ ነው።
ሁላችንም እንደምናስታውሰው ከጥቂት ዓመታት በፊት የትንሳኤ ሬድዮ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሀብት የዘረፉ የወያኔ መንግስት ባለስልጣኖችን፥ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ የዘረፉትን ሀብት መጠንና ገንዘቡን ያስቀመጡበትን አገር ጭምር ይፋ አድርጎ ነበር። በትክክል ካስታውስኩ አቶ መለስ ዜናዊ በማሌዥያ በባንክ ፬፪ (አርባ ሁለት) ሚሊዮን ዶላር እንዳስቀመጡ ገልጾ ነበር። ይህንን ተከትሎ የመለስ ዜናዊ መንግስት የትንሳኤ ሬድዮን አሜሪካን አገር በቨርጂኒያ ስቴት በሚገኝ ፍርድ ቤት በስም ማጥፋት ወንጀል በሚል የክስ ፋይል መስርቶ እንደነበርና በሁዋላ ግን የሚያስከትለውን መዘዝ በመፍራት ይመስላል ክሱን መሳቡ (ዊዝድሮው ማድረጉ) ተነግሮ እንደነበር ይታወሳል።
ይህ ሲገርመን ከጥቂት ቀናት በፊት አንድ በኢሳት ሬድዮ ቀርቦ የነበረ ጋዜጠኛ እንዳመለከተው ሴሌብርቲ ኔትወርዝ የተባለ ድረ ገጽ አቶ መለስ ዜናዊ ያላቸው ሀብት ፫ (ሶስት) ቢሊየን ዶላር እንደሆነ ያሳያል። ይህንን በርግጥም ማንም በተባለው ድረ ገጽ አድራሻ በ http://www.celebritynetworth.com/ ሊመለከተው የሚችል ዘገባ ነው። ድረ ገጹ በዓለም ላይ ያሉ ታዋቂ ሰዎችንና እንደ እነ አቶ መለስ ዜናዊ ያሉ አምባ ገነን መሪዎች ያላቸውን ሀብት የሚዘግብ በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አላቸው ተብሎ የተዘገበው ከፍተኛ ሀብት ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠውና ሊመረመር የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል።
እዚህ ላይ በተለይም ኢትዬጵያውያን ጋዜጠኞች፤ የሕግ ባለሙያዎች፤ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራት እንዲሁም ይህን ጉዳይ ለማጣራት አቅምና ችሎታ ያላቸው ግለሰቦች በትንሳኤ ሬድዮም ሆነ በሴሌብሪቲ ኔትወርክ የተመለከቱትን የወያኔ ባለስልጣኖች የተካባተ ሀብት መጠንና የሚገኝበትን ስፍራ መርምረውና አጣርተው ለሕዝብ ማጋለጥ ያለባቸው ይመስለኛል።
እንደሚታወቀው ባገራችን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሙስና በከፍተኛ ደረጃ መስፋፋቱና ያገራችን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመዘረፍ ላይ እንደሚገኝ የአደባባይ ምስጢር ነው። ትናንት ምንም ያልነበራቸው የዛሬዎቹ ባለጊዜ የወያኔ ባለስልጣኖች ባገር ውስጥ የባለ ብዙ ሕንጻዎችና ሌሎችም ንብረቶች ባለሀብቶች መሆናቸው በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች መገለጹ ይታወሳል። ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተለያየ ጊዜ እንደዘገቡት ካገራችን ብዙ ቢሊዮን ዶላር እንዲሸሽ መደረጉን መግለጻቸው ያገር ሀብት ዘረፋው በከፍተኛ ደረጃ መስፋፋቱን በግልጽ የሚያመለክት ነው።
የቀድሞዎቹ አምባገነኖች የግብጹ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክና የሊቢያው ኮሎኔል ሙዓመር ጋዳፊ በውጭ አገሮች በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት አካብተው እንደነበርና፤ የስርዓታቸውን መገርሰስ ተከትሎ የያገራቸው ሕዝቦች ይህን የተዘረፈ ሀብት ለማስመለስ እንደሚንቀሳቀሱ መገለጹ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ሁኔታ እኛም ኢትዮጵያውያኖች እነዚህን ለ፪፩ ዓመታት እንደመዥገር ከሕዝባችን ተጣብቀው የዘረፉትን ቋሚም ሆነ ተንቀሳቃሽ ሀብት በሚቻለው አቅም ተከታትለን ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ማጋለጥ እንዳለብን ይሰማኛል። ይህም ወደፊት ከአይቀሬው የስርዓቱ መገርሰስ በሁዋላ ሀብታችንን ለማስመለስ ለምናደርገው ጥረት እንደ ቅድመ ዝግጅት ሊያገለግል እንደሚችል አምናለሁ።
ኢትዮጵያ አገራችንን እግዚአብሔር ይጠብቅልን።
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር።

Friday, 29 March 2013

Cheers and congratulations to Endale Getaneh

Cheers and congratulations to Boschendal Getaneh, finally, after 5 years and 5 months have been granted a residence permit? In the process, I congratulate Norway; continue happily so - grant more political permits to Ethiopian refugees, and relation to the severity and consequences of it in relation to Ethiopia.

It sings Endalen Getaneh during last year's memorial ceremony in Oslo for the victims of the great massacre in Addis Ababa in 2005. A natural protest against the regime under TPLF and Meles Zenawi did not let the opposition, which was heavy with votes during elections, led to an enormous tragedy, that many of the asylum seekers from Ethiopia are highly influenced by. 193 people were killed, and around 20,000 were imprisoned and tortured. I have been told that the families of the victims were forced to pay the bullets that killed their lost close.

About massacre: http://news.bbc.co.uk/2/hi/6064638.stm

Dear Norway, please be humble, let more of those in need of protection have become. Keep in mind that many refugees have horrific stories behind them, which drives them to flee.


Nyhet!Logg deg på og klikk på stjernen for å lagre denne oversettelsen i uttrykkslisten din.
http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2013/03/26/refugee-from-ethiopia-sings-in-front-of-parliament-in-oslo/

Refugee from Ethiopia sings in front of Parliament in Oslo

Endal Getaneh, a refugee from Ethiopia sings a hymn of hope in front of Parliament in Oslo.
Norway is the first and only European countries signed an agreement on the return of refugees to the authoritarian regime in Ethiopia. Amnesty International, Human Rights Watch and several other human rights organizations in a strongly critical of the agreement.
Many of the Ethiopian refugees are actively politically in opposition to the Ethiopian regime. They fear for their lives, torture and imprisonment forcibly returned to Ethiopia

Wednesday, 27 March 2013

ማልዶ የወጣ Maldo Yewta


 የዲያቆን አሸናፊ መንን ገጽ

ማንም ሰው ለእግዚአብሔር ኢትዮጵያ ወይም ኬንያ ልወለድ ብሎ አሳብ አላቀረበም፡፡ ሙሉ በሙሉ ፈቃዱ የእግዚአብሔር ሆኖ ራሳችንን በዚህ አገርና በዚህ ቤተሰብ ውስጥ አግኝተነዋል፡፡ የምንኖርበትን አገር፣ የምንወለድበትን ቤተሰብ የመረጠልን ምርጫ አዋቂው እግዚአብሔር ነው፡፡ በእግዚአብሔር የሆነልን ነገር መልካም ነው፡፡ ሰው ሆነን መፈጠራችን፣ መዳናችን፣ ክርስቲያን መሆናችን.. የሆኑልን መልካም ነገሮች ናቸው፡፡ በእግዚአብሔር ወደፊት የሚሆነውም መልካም ነው፡፡ ከእግዚአብሔር እጅ የምንቀበለው ነውር፣ ነቀፋ፣ እንከን፣ ነቁጥ የሌለበት ነው፡፡

ልጆቻችን የወደዱን በብዙ መልካምነታችን ነው፡፡ የትዳር ጓደኞቻችን የመረጡን በቁምነገራችን ነው፡፡ መሥሪያ ቤታችን የተቀበለን በሙያችን ነው፡፡ ወዳጆቻችን የወደዱን በማረካቸው ነገራችን ነው፡፡ ወላጆቻችን የወደዱን የእነርሱ ስለሆንን ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን የወደደን ስለ እኛነታችን ነው፡፡

እኛን ለቤተሰባችን፣ ቤተሰባችንን ለእኛ የሰጠ እግዚአብሔር ነው፡፡ ወላጆቻችን ያዩንና የወደዱን ከተወለድን በኋላ ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ዓለም ሳይፈጠር በአንድ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ዓይቶናል /ኤፌ. 1÷4/፡፡ በማኅፀን ደም አርግቶ፣ አጥንት ሰክቶ ፣ ጅማት አዙሮ፣ ሥጋ አልብሶ፣ እስትንፋስ ዘርቶ ሠርቶናል፡፡ በማኅፀን በስውር የመገበንም እርሱ ነው፡፡ ወላጆቻችን የሚያውቁን ስንወለድ ነው፣ እግዚአብሔር ግን የሚያውቀን ዓለም ሳይፈጠር ነው፡፡ ነቢዩ፡- “ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ” ያለው ለዚህ ነው (መዝ. 138÷ 15-16)፡፡


Saturday, 23 March 2013

የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ - ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን

 



የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ

ተስፋ ባጣ ምድረ በዳ
ያንድ እውነት ይሆናል ዕዳ፡፡
እና ትንፋሼ አልሆነሽም፥ ሆኜብሽ መራር መካሪ
“ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ፣”
እውነት ላንቺ መች ተስፋ ናት፥ ጉስቁል ልሳንሽን ነክሳሽ
ክንድሽን ካዘለ ቅርስሽ፥ መጠላለፍ ሲሆን እጣሽ
ከእንግሊዝ የሞት አማልክት፥ መተናነቅ ሲሆን ድርሻሽ
መልመጥመጡ፥ መሽቆጥቆጡ፥ መስሎሽ ድንገት የሚያዋጣሽ
የኔ እውነት ሆነብሽ ዕዳሽ ፡፡ …..
ወራሪም ፈጣሪን ላያቅ
የጣለውን በስሏል እንጂ፥ ወድቋል ብሎ ግፉ ላያልቅ
መች ትተርፊያለሽ ኢትዮጵያ፥ ሕዋስሽ አብሮኝ ካልሠራ
አንገትሽ ብቻ መቅደላ፥ አፋፍ ወጥታ ብታበራ
የቀረው ሠራ-አከላትሽ፥ በየጥሻው ተዘርሮ
ከአባት በወረሽው ንፍገት፥ ነብዞ ደንዝዞ ተቀብሮ
ባጉል ወጌሻ ታጅሎ
እጅና እግርሽ ታሽቶ ዝሎ
እኔን ለጥንብ አንሳ ጥሎ፤
ከደቀቀ ከደከመ፥ ክንድሽ አልነሣ ካለ
ሞት እንጂ ለኔስ ምን አለ?.....
ሆኖም ጐስቋላ አልምሰልሽ፥ የሚያዝንልኝ አልፈልግም
ጠላትሽን በክንድሽ እንጂ፥ በእንባሽ ወዝ ባላሸንፍም
የልቤን ፍቅር በሰተቀር፥ እማወርስሽም ውል የለኝ
የኮሶ ሻጭ ልጅ ደሃ ነኝ፡፡ …..

ደሞም ያላንቺ የለኝና
ድሌም የተሰፋ ጐሕ ባይሆን፥ ከሞት ጋር ትግል ነውና
ከዚህ ሌላ ትእዝብት ውረሽ፥ ሳይነጋ እንዳስመሸሽብኝ
ጊዜና ትውልድ ይፍረደን፥ ሳልነቃ እንዳስረፈድሽብኝ፡፡
ያም ሆኖ ለራስሽ እንጂ ለኔ ከቶም አታልቅሺ
አንቺ ነሽ እንባ እምትሺ፤ …..
የእምነትሽ መተሣሰሪያ፤ ውልሽ ለተላቀቀብሽ ላንቺ ነው እንባ እሚያሰፈልግሽ፡፡
አዎን፥ ይኽን እወቁልኝ፥ ምስክር ሁኑኝ ሰማዕታት
ለሷ ነው እንባ የሚያስፈልጋት፡፡
ከጠላቶቹ ጭብጥ ውስጥ፥ ትንፋሼን በጄ ስነጥቃት
ሞቴን ከመንጋጋቸው ውስጥ፥ መንጭቄ እኔው ስሞታት
ላገሬ ብድር ልከፍላት
የነፈገቺኝን ፍቅር፥ በራሴ ሞት ልለግሳት!.....ያኔ ነው እንባዋ የሚያጥራት፡፡
ሰለዚህ ለራስሽ እንጂ፥ ልቅሶሽ ለኔ ምን ሊረባ
ብቸኛ ምሬት ነው ኃይሉ፥ ወኔ መሰለቢያው ነው እንባ፡፡
እና ለራስሽ እዘኚ
እንጂ ከቶ ለኔ እትባክኚ፡፡ …..ይልቅስ ተረት ልንገረሽ፥ የተላከ ከእንግሊዝ ዘንድ
እጅህን ስጥ አለኝ ፈረንጅ፥ እጅ ተይዞ ሊወሰድ፥
ምን እጅ አለው የእሳት ሰደድ?አያውቅም ክንዴ እንደሚያነድ፡፡ …..ዳዊት እንዲያ በበገናው፥ ማልቀስ ማላዘን መያዙ
ይኽ የጐልያድ ውላጅ፥ ቢበዛበት ነው መዘዙ
ምንጩ እንደአሽን እየፈላ፥ አገሩን ምድሩን ማንቀዙ
ቸግሮት ነው፥ መጋፈጡ፥ ከስንቱ መወናጨፉ
በባላንጣው ሳቢያ ምክንያት፥ የራሱን ወገን ማርገፉ፡፡ …..ታድያ እንግዲህ አንቺ ኢትዮጵያ፥ እኛስ ልጆችሽ ምንድነን
አመንኩሽ ማለት የማንችል፥ ፍቅራችን የሚያስነውረን
ዕዳችን የሚያስፎክረን
ግፋችን የሚያስከብረን
ቅነነት የሚያሳፍረን፥ ቂማችን የሚያስደስተን
ኧረ ምንድነን? ምንድነን?አሜከላ እሚያብብብን፥
ፍግ እሚለመልምብን፥
ከአረም ጋር ያፈራን ጊንጦች፥ ከእንክርዳድ ያልተለየን ዘር
ግርዱ ከምርቱ ተማጥቆ፥ ከቶ ያልተበራየን መከር
ምንድነን? ምንድነን እኮ?አረጋዊውን ባንቀልባ፥ ከምንሽከም እንኮኮ
ጐልማሳውን ከወኔ ጣር፥ ካልፈታን ከፍርሃት ምርኮ
እንደ ወዶ ገባ ወደል፥ መጠለሉን ከሴት ታኮ …..ካቃተን፥ ምንድነን እኮ?.....አየሽ እንቺ እማማ ኢትዮጵያ፥ አየሽ አንቺ እናት ዓለም
ቃል የእምነት ዕዳ ነው እንጂ፥ ያባት የናት እኮ አይደለም፡፡ …..

ያም ይቅርና መርዶ ላርዳሽ፥ ስሚው እኔ እንደሰማሁት
እርም በልተሽ ከምትቀሪ፥ ስሚው ገብርዬንም ጣሉት፡፡ …..እስቲ እንግዲህ በይ ፍረጂኝ፥ ከእንግዲህ እኔ ፍሬ አላይም?
ዘርቶ መቃም ወልዶ መሳምአባባል ለኔ አይባልም?እስቲ ገብርዬን መሰል ዘር፥ ፍሬው ከቶ አይለመልምም?እኔስ ዘር ዘራሁ አልልም? …..ምነው ፍንጭትክን ገብርዬ፥ ያን ፍንጭትክን አጨለሙት
እንደ ሬት ልግ አከሰሉት
እንደ ኮሶ አስመረሩት? ......ከጡቶችሽ እቅፍ ነጥቀው፥ ከማኅፀንሽ ፍቅር ቆርጠው
እውነትን ሲገሉ እንዲህ ነው፥ ፈገግታውን አጨልመው፡፡
እስቲ እባክህን ገብርዬ፥ የዛሬን እንኳ ስቀህ ሙት
በዕድል ጥቀርሻ እንደአጀሉት
እንደ ወላድ ጣውንት ጡት
አርማ ጉሳ እንደቀለሙት
ፈገግታህን አያጥቁሩት፡፡
እምቢ በላቸው ገብርዬ፥ በአባት ሤራ እንዳስገዘቱት
በመሃላ እንዳሳገዱት
የነፍሰህን ጮራ ብርሃን፥ ከገጽህ እንደቀበሩት
ዘለዓለም ላያጨልሙት
ወንድምዬ እምቢ በላቸው፥ የዛሬን እንኳ ስቀህ ሙት፡፡ …..ያለፈ ጥረታችንን፥ ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ፥ ያልሞከረነው ነው እሚቆጨኝ፡፡
እና በኔ ይሁንብህ፥ መጣሁ፥ ስቀህ ተቀበለኝ
እኔም ላዋይህ አድምጠኝ …..እጅህን ስጥ አለኝ ፈረንጅ፥ እጅ ተይዞ ሊወሰድ
ምን እጅ አለው የእሳት ሰደድ?አያውቅም ክንዴ እንደሚያነድ፡፡ …..


ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እሳት ወይ አበባ

Thursday, 21 March 2013

እንዳይነግርህ አንዳች እውነት !

 /ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
-----------
ደንስ ጎበዝ ! ደንስ ጀግና
ክራቫትህን አውልቅና
ሃሳብህን ልቀቀውና
... ኮትክን ሸሚዝክን ጣልና
ርገጥ ፣ ጨፍር ፣ ደንስ ጀግና !

ያን የሙዚቃህን ናዳ ፣ የኮንትራባሱን መብረቅ
ልቀቀውና ይድብለቅለቅ
ምድር በሆይታ ይጥለቅለቅ !
ምንም-ምንም እንዳታስብ ፣ ሁሉን-ሁሉን እንድትረሳ
ደንስ ! ካካታው ይነሳ
ጨፍር ፣ ወለሉ እስኪበሳ ....

ሃይ-ሃይ ! ዋይ ! ሃይ-ሃይ ! በልበት
የጃዝ ፋንፋር አንኳኳበት
ራስክን እንዳታስብበት ፤
ሆ ! በል እሪ ! በል ምታበት
ፎክርበት ፣ አቅራራበት
አናፋበት ፣ ሸልልበት
የሲቃ ሳቅ አስካካበት
ሆያ-ሆዬ ! በል ጩኽበት
ኡኡታህ መንኮራኩርክን ፣ እስኪያሰጥመው አጓራበት
ጭንቅላትክን ግዘፍበት ፣ ውቀጥበት ፣ ውገርበት ፣ ....
ዝግ ብሎማ ያሰበ እንደሁ ፣ ይነግርሃል አንዳች እውነት !
----------