"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 20 April 2013

Police stopped meeting in Tasta bydelshus ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች]

አማርኛውን ሪፖርት እና ኖርዌ ስታቫንገር ያለ ጋዜጣ ያወጣውን  ወደ እንግሊዘኛ በመቀያር እንድታዩት አያይዠዋለው።
ከአባይ በፊት የህዝብ ስቃይ ፤እስር ፤ስደት፧ መፈናቀል ፡ይቁም

አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ኢትዮጵያውያን ከኖርዌ ስብሰባ ያባረሯት የወያኔ አምባሳደር "መብራት በየነ አባይ"።

ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ። ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።

 
.The police came out with three cars and six policemen and stopped a meeting of Tasta bydelshus where the atmosphere was becoming so very irritably among the more than 300 attendees.
OFF: toril RisholmPublished: April 20, 2013 7:51 p.m. Updated: April 20, 2013 8:13 p.m.

The 300 attendees were Ethiopian asylum seekers or people with Ethiopian background. The police feared that it would get completely out of control when people in the audience went to the hard verbal confrontation against two representatives from the Ethiopian Embassy in Stockholm who had called for and chaired the meeting.The police gave the first message that all protesters to leave the meeting while the two embassy people and their potential supporters can be seated. This denied the attendees protesters, and several feared it would come to an open confrontation between police and people in the audience. Then, specific efforts manager Øyvind Sveinsvoll of Rogaland police to stop the meeting and clear the room.It was a wise decision, said several of those present protesters. They did not want the two embassy people should be left as "victors" while they were evicted.- Our goal was to stop the meeting.

Wednesday 17 April 2013

“ማሪያም ነኝ” ባዩዋ ተፈረደባት


በአሸናፊ ደምሴ
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በመንቀሳቀስ ሰዎችን በማታለል “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌያለሁ፤ ከሞትም ተነስቻለሁ፤የወለድኳቸውንም ልጆች ያገኘሁት በመንፈስ ነው”
ስትልና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል በሚል የሰዎችን የግል ሀብት ለራሷ ስታደርግ ደርሼባታለሁ ሲል ክስ የመሰርተባት የ34 ዓመቷ ትዕግስት ብርሃኑ ወ/ጊዮርጊስ፤ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል ችሎት ፊት ቀርባ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ በ2 ዓመት
ከ4 ወራት ፅኑ እስራትና በአንድ ሺ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ወሰነ።
እንደአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ከሆነ ግለሰቧ በአራት የተለያዩ ክሶች የተወነጀለች ሲሆን፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
“ለሰው ህይወት ማለፍ ሳቢያ ነች” ሲል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ ያልተሟላ ነው ሲል ውድቅ ሲያደርገው በተቀሩት
ሶስት ክሶች ግን ጥፋተኛ ነች ብሎ እንድትከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር።
ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባለችበት አንደኛ ክስ በየካቲትና በመጋቢት ወራት ውስጥ 1999 ዓ.ም የማይገባትን ጥቅም

ለማግኘት አስባ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 21 ልዩ ቦታው ኪዳነምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ300 በላይ ሰዎችን በመሰብሰብ “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌ፤ ከሞትም ተነስቼያለሁ” የሚል የሀሰት ወሬ በመንዛትና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል ንብረት አያስፈልግም በሚል ያላችሁን ንብረት አምጡ ስትል ከተለያዩ የግል ተበዳዮች ጥሬ ገንዘብና ወርቅ የተቀበለች ሲሆን፤ በአጠቃላይም 40ሺ ብር ለግል ጥቅሟ አውላለች ሲል በክስ መዝገቡ ያስረዳል።
እንደአቃቤ ህግ ቀጣይ ክስ ደግሞ ተከሳሿ በሰኔ 1 ቀን 1999 ዓ.ም በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 16 ልዩ ቦታው ላምበረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 50 የሚደርሱ ሰዎችን በመያዝ ወደደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በመጓዝ ወንጭ ገዳም ተብሎ ወደሚጠራው መንፈሳዊ ቦታ በመውሰድ በፆምና ፀሎት ሰበብ አብረዋት የነበሩት ሰዎች ለአምስት ቀናት ምግብ እንዳይበሉ በማድረግ እንዲዳከሙና ለከፋ ጉዳት እንዲዳረጉ አድርጋለች ሲል በክሱ ያትታል።
በሌላም በኩል ግለሰቧ በጥር 24 ቀን 2003 ዓ.ም በልደታ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 ልዩ ቦታው ተክለሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ወደ 20 የሚጠጉ ህፃናት ልጆችና ሴት ተከታዮቿን በመያዝ፣ “እኔ ማርያም ነኝ፤ ልጆቼን የወለድኳቸውም በመንፈስ ነው እንጂ ከወንድ ጋር ተኝቼ አይደለም” በማለትና ተከታዮቿም እርሷ ማርያም ነች።
ሞታም ተነስታለች እንዲሁም 40 ቀን ያለምግብ ትፆማለች በማለት ሀሰተኛ ወሬዎችን እንዲነዙ በማድረግ ስታስተምር እንደነበር ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ ደርሶኛል ያለው ዐቃቤ ሕግ፤ በዚህም ምክንያት በቤተ-ክርስቲያኗ ቅጥር ግቢ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ምዕመናን “ ሀሰት ነገር አትናገሪ” ሲሉ በመቃወማቸው ወደሁከት ውስጥ እንዲገቡ ያደረገች በመሆኑ በፈፀመችው የሀሰት ወሬዎችን በማውራትና ህዝብን በማነሳሳት ወንጀል ተከሳለች ይላል።
ጉዳዩን ሲመረምረው የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል ችሎትም የዐቃቤ ሕግን ክስ ተከሳሿ ማስተባበል ባለመቻሏ ጥፋተኛ ሆና አግኝቻታለሁ ሲል፤ መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በ2 ዓመት ከ4 ወር ፅኑ እስራትና በ1000 ብር እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል።¾
ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ