"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 9 June 2012

“ቬነስ ፕላኔት በአዲስ አበባ ፀሀይን ማቋረጧ የልማቱ ውጤት መሆኑ ተዘገበ!”


“ቬነስ ፕላኔት በአዲስ አበባ ፀሀይን ማቋረጧ የልማቱ ውጤት መሆኑ ተዘገበ!”
Posted by admin on June 6, 20120 Comment
በአቤ ቶኪቻው
ዛሬ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ በአዲስ አበባ ፀሐይ ስር ቬነስ የተባለችው ፕላኔት ስታቋርጥ ለ18 ዲቂቃዎች እንደምትታይ መሰለ ገብረ ህይወት የተባለው የኢቲቪ ዜና አንባቢ ትላንት ማታ በፈገግታ እና በታላቅ ድል ስሜት ታጅቦ ነገሮናል። ከፈገግታውና ከአነጋገሩ እንደተረዳሁት ከሆነ ነገ ይህንኑ ዜና ምን ብሎ ሊነግረን እንደሚችል እንደሚከተለው እገምታለሁ…
ቬነስ ፕላኔት በአዲስ አበባ ሰማይ ስር ማለፏ ያስመዘገብነው ልማት ውጤት መሆኑ፤ የተለያዩ ባለስልጣናትን አነጋግሮ የዘገበው ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ፕላኔቷ በ18 ደቂቃ ቆይታዋ በአገሪቱ መልካም አስተዳደር እና ዴሞክራሲ ሰፍኖ መመልከቷን አያይዞ ዘገቧል።
ለዝርዝሩ… (“ትልና…” አሉ የዞን 9 ልጆች አንዳቸው ወይም ሁለታቸው…! (እዝችጋ አንድ ማስታወቂያ ተናግሬ እቀጥላለሁ ዞን 9 የተባለ ብሎግ መከፈቱን ሰምታችሁ ይሆን? ወደ አስር የሚጠጉ “ጦማሪያን” በአንድ ላይ በመሆን የከፈቱት ይህ “ጦማር” “ስለሚያገባን እንጦምራለን!” በሚል መሪ ቃል የተከፈተ እንደሆነ አናቱ ላይ የተፃፈውን አይቼ ተረድቻለሁ… ጎራ ብላችሁ ብታዩት አሪፍ አሪፍ “ጡመራ” እንደሚኖር ድንጋይ ነክሼ እመሰክራለሁ…!) http://zonenine.wordpress.com/author/zonenine/ ይኸው መግቢያው!
ወደ ዜናችን ስንመለስ…

የታማኝ በየነ ንግግር በደቡብ አፍሪካ፡- “…ስህተቱን አርመን የተሻለች ኢትዮጵያ እናደርጋታለን”




Saturday, June 9th, 2012 | Posted by zehabesha
የታማኝ በየነ ንግግር በደቡብ አፍሪካ፡- “…ስህተቱን አርመን የተሻለች ኢትዮጵያ እናደርጋታለን”
25
Share
(ዘ-ሐበሻ) ታማኝ በየነ ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ የኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ በተደረገበት ወቅት እዚያ ከሚኖረው ሕዝብ የንጉሥ አቀባበል እንደተደረገለትና በአቋሙ ጽናት፣ ለእማማ ኢትዮጵያ ባለው ፍቅር ትልቅ አክብሮትን አግኝቷል። ከታማኝ እኩል አብረው ከሕዝብ ጋር ስለነጻነትና ስለ መብት መከበር ይጮኹ የነበሩ አርቲስቶች ዛሬ ማሊያ ቢቀይሩም ከሕዝብ ዘንድ ያገኙት ንቀት ግን የሕሊና ራስ ምታት ሆኖባቸዋል። እነዚህ ሆዳም አርቲስቶች ታማኝ በደቡብ አፍሪካ የተደረገለትን ንጉሣዊ አቀባበል ሲያዩ ምን እንደሚሉና ምን እንደሚሰማቸው ማሰቡ ቀላል ነው። ታማኝ እንደነገሠ፣ እነርሱም እንደረከሡ ይቀጥላል።
ውድ የድረገጻችን አባቢዎች ታማኝ በደቡብ አፍሪካ ያደረገው ሙሉ ንግግር እስካሁን በቪዲዮ ሙሉ በሙሉ አልወጣም ነበር። ኢሳት ይህንን የተቀናበረውን ቪድዮ ለቆታል፤ እኛም ያላየው ያየው ዘንድ ቪድዮውን ይዘንላችኋል። ይመልከቱት።

The Dictator film banned in Ethiopia‹‹ዘ ዲክታተር›› የተሰኘው ፊል Posted by admin on June 9, ም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታይ ታገደ


The Dictator film banned in Ethiopia
Ethiopia has refused to show the new satirical comedy “The Dictator”. Read the news in Amharic
‹‹ዘ ዲክታተር›› የተሰኘው ፊል                                                             Posted by admin on June 9,
ም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታይ ታገደ
አውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ) – በቅርቡ ለእይታ የበቃውና በመላው አለም አድናቆትን ያተረፈው ‹‹ዘ -ዲክታተር›› ፊልም፤ አዲስ አበባ ውስጥ ኤድናሞል ተብሎ በሚታወቀው ሲኒማ ለእይታ በቀረበ በጥቂት ቀናት ውስጥ በመንግስት ትዕዛዝ እንዲታገድ መደረጉን የአውራምባ ታይምስ መንጮች ገለጹ፡፡

sacha-baron-cohen-the-dictator
በታዋቂው ሳቻ ባሮን ኮኸን ድርሰትና መሪ ተዋናይነት የተሰራውና በላሪ ቻርለስ ዳይሬክት የተደረገው ‹‹ዘ ዲክታተር›› ፊልም በሰሜን አፍሪካ ውስጥ የሚገኝ እራሱን አድሚራል ጄነራል አላዲን ብሎ የሚጠራ አንድ አምባገነን፣ ዴሞክራሲ ወደዚያች አገር እንዳይመጣ እንዴት ሌተቀን እንደሚተጋ የሚያሳይ ኮሜዲ ፊልም ነው፡፡ ለቀድሞው የሰሜን ኮሪያ አምባገነን መሪ ኪም ጆንግ ኢል መታሰቢያ የሚል ስላቃዊ ማስታወሻ የሰፈረበት ይህ ፊልም በጥቂት ሳምንታት ውስጥ በሚሊዮኖች አድናቆት እንደተቸረው ፊልሙን ከሚያከፋፍለው ፓራማውንት ፒክቸርስ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡  ፡                                                                          የራሴን አሳብ ላክልበት፤ልማታዊው የወያኔው ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁ በራሱ ሬዲዮ ፕሮግራም እንዳ ወራው  ፊልሙ ብዙ                       ክስ ስላለበት ለጊዜው ታግዷል አለን።ግን እኔን የሚገርመኝ ቢታይ ነበር  ለምን ቢባ ል እነዴት ዲክታተር ባለበት የዲክታተር ፊልም ሊታይ ይችላል     መለስ ዜናዌ ህዝቡን እንዳያወራ  ፦እንዳ ይሰበሰብ፦ እንዳይጽፍ፦ባጠቃላይ መብቱን ገፎ ባለበት ጊዜ   እነ ሰይፉ ሊነግሩን  ወይም ሊያታልሉን ሲሞክሩ በእውነት በተከፈተ አፍ ባዶ  ጭቅላት  ይታያል  ልበል እና ላቁም 

Friday 8 June 2012

Meles Steps Up Control On Information And Internet


Meles Steps Up Control On Information And Internet
SHARE THIS
       
TAGS

Reporters without Boarders (PARIS, France) — Ethiopia’s only ISP, state-owned Ethio-Telecom, has just installed a system for blocking access to the Tor network, which lets users browse anonymously and access blocked websites. At the same time, the state-owned printing presses are demanding the right to censor the newspapers they print.
Reporters Without Borders is very worried by these attempts to reinforce government control of news and information.

Danger that printers will censor newspaper content

Reporters Without Borders accuses the biggest state printer, Berhanena Selam, which almost has a monopoly on newspaper and magazine printing in Ethiopia, and other state owned printers, of trying to impose political censorship on media content before publication.
In a proposed “standard contract for printing” recently circulated by state printers, they assume the right to vet and reject articles prior to printing.
“This contract could drag Ethiopia back more than two decades as regards media freedom, to the time of Mengistu’s brutal dictatorship in pre 1991 Ethiopia,” Reporters Without Borders said. “Allowing printers to control editorial content is tantamount to give them court powers. On what basis do these state-owned companies assume the right and independence to interpret the law? Does this reflect a government desire to suppress all criticism before it is voiced?
“If this standard contract is adopted, we fear it could lead to widespread self-censorship, which is already very common, and to media subservience towards the government. Criticism, independence and media diversity would all suffer, and the vitality of Ethiopian democracy would suffer as well.”
Article 10 of the proposed contract is evocatively entitled “Declining to print content violating the law.” It saysthe printer has the right to refuse to print any text if he has “adequate reason” to think it breaks the law. It goes on to say that the printer reserves the right to terminate or cancel the contract at any time if he has “adequate reason” to think that the publisher “has a propensity to publish a content which entails liability.”
This article openly contravenes article 29 of the 1994 federal constitution, which guarantees press freedom and bans “censorship in any form.” Reporters Without Borders points out that only an independent and impartial judge should have the power to impose any kind of sanction or prohibition affecting media freedom.
Ethiopia’s privately-owned newspaper and magazine publishers reacted to the proposed contract by addressing a joint petition to Prime Minister Meles Zenawi urging him to recognize that it violates the constitution and to have it withdrawn. The response from a government official was to insist that it was “a strictly business-based decision” and to deny any desire to censor.
The printers are keeping up the pressure on the publishers, saying they will refuse to print any newspapers or magazines and, under an unlawful contract that is an extension of the new press law that has put liabilities on printers for print media content.
“We call on all media professionals – publishers, editors and journalists – to be brought into the process of negotiation and drafting of this printing contract,” Reporters Without Borders said. “The possibility that printers could be held liable for printed content must not be used as grounds for reintroducing prior censorship.”
As it stands, the proposed contract would add to the repressive legislative edifice that the Ethiopian government has built over the past three years. It includes the 2009 anti-terrorism law under which two journalists have been charged and sentenced to long jail terms (http://en.rsf.org/ethiopia-journalists-are-not-terrorists-24-01-2012,41764.html). It is also liable to exacerbate the already poor climate between the privately-owned media and government.
More information about freedom of information in Ethiopia: http://en.rsf.org/report-ethiopia,16.html

Government steps up control of Internet, uses sophisticated technology

Government-owned Internet Service Provider Ethio-Telecom, the country’s only ISP, has for the past two weeks been blocking access to the Tor network, an online tool that allows users to browse anonymously and access blocked websites. To do this kind of selective blocking, Ethio-Telecom must be using Deep Packet Inspection (DPI), an advanced network filtering method.
DPI is widely used by countries that are “Enemies of the Internet” such as China and Iran. Blocking access to porn sites is usually the official reason given for installing and using it, but in practice it allows governments to easily target politically sensitive websites and quickly censor any expression of opposition views.
In installing DPI and blocking access to Tor, the Ethiopian government is probably taking a first step towards installing a sophisticated filtering system that will eventually enable it to intercept emails, messages posted on social networks and Internet voice conversations using Voice over Internet Protocol (VoIP) software such as Skype.
Use of VoIP hardware and software has just been made a crime by the new Ethiopian Telecom Service legislation, which was ratified on 24 May. Anyone violating this provision could be sentenced to up 15 years in prison.
The authorities say the ban was needed on national security grounds and because VoIP posed a threat to the state’s monopoly of telephone communications.
The new law also gives the ministry of communications and information technology the power to supervise and issue licences to all privately-owned companies that import equipment used for the communication of information.
The OpenNet Initiative has already reported cases of Internet censorship in Ethiopia, including the blocking of blogs, news sites and opposition sites. So far there have been relatively few cases, above all because of the low level of Internet use in Ethiopia.
“This new law and the possibility that a Deep Packet Inspection system has been installed mark a turning point in the Ethiopian government’s control of the Internet,” Reporters Without Borders said. “We fear that DPI will be misused for surveillance purposes by a government that already subjects the political opposition and privately-owned media to a great deal of harassment.
“We urge the Ethiopian authorities not to install this filtering system and, as we already said when The Reporter news website was blocked, we share the view of the United Nations special rapporteur for freedom of opinion and expression, Frank La Rue, who recommended in a June 2011 report that restrictions to the flow of information online should be limited to ‘few, exceptional, and limited circumstances prescribed by international human rights law’.”
It should be noted that, a few days after spotting that access to the Tor network was being blocked in Ethiopia, the Tor Project posted a message on its blog explaining how to circumvent the blocking.

ስለ ማሪያም እንደ ማሪያም

ስንቶቻችን ነን  እናታችንን በተለያየ  የዕድሜ  ክልል እያለን  ያጣን    ፩  እኛን   ወለዳ   ሳታየን  ሳናያት ያጣናት   ፪   ጡቷን ጠግበን ሳንጠባ  ያጣናት ፫  እኛን ለቁም ነገር ለማብቃት ደፋ   ቀና ስትል  እሷን እየራባት እኛን ስታጎርስ  እርሧን እየጠማት እኛን  ስታጠጣ መከራን ችገርን በደልን ለልጆቿ  ስትል ተቀብላ  እፎይ  ሳትል   አሁን በቃሽ ደረስኩልሽ አረፍ በይ ሳንላት ያጣናት   ኧዎ ቤቱ ይቁጠረው       ሁል ጊዜ እንደ ድንጋይ ላይ መኝታ የሚቆረቁረን ፨እግዚኦ  እናት አነሰን    ኤሎሄ  ፍርድ ተዛባ ባንተ       ከጎናችን ሁሌ የማትርቅ      እናት ትኑረን እንዳተ   ስለማሪያም  እንዳማሪያም    እስከ አሪያም

እርቃኔን ቅበሩኝ

                     በዕድሜአችን  ምን ያህል  እውነተኛ  ሆነን  እናውቃለን ፡ መልሱን  ለህሊናች ልተወው።

የሰኔ 1 1997 የጭካኔ ተግባር ሁለት ልጆችዋ የተገደሉባት እምዪ

የሰኔ 1 1997  የጭካኔ ተግባር  ሁለት ልጆችዋ የተገደሉባት  እምዪ

የመነን 4ኛ ባል!





የመነን 4ኛ ባል!

        ከብዙ አመታት በፊት ተፈሪ መኮንን የሚባል አንድ ወጣት ደጃዝማች በሃረር አካባቢ ይኖር ነበር። እና ኑሮውን በሰላም በመኖር ላይ ሳለ አንድ ቀን ያልጠበቀው ነገር ገጠመው። ተፈሪ እንደወትሮው ጸሎት ላይ ሳለ ስልክ እንደሚፈልገው ተነገረው። የደወለለት የአጤ ምኒልክ ዙፋን ወራሽ ልጅ እያሱ ነበር። ሰላምታ ከተለዋወጡ በሁዋላ ልጅ እያሱ በቀጥታ ተፈሪን እንዲህ አለው፣
        “ስማ ተፈሪ! የእህቴን ልጅ መነን አስፋውን ልድርልህ ወስኛለሁ። የአንተ አሳብ ምንድነው?”
        ተፈሪ በጣም ደነገጠ።  ምክንያቱም መነን ከሶስተኛ ባሏ ጋር ከተጋባች ገና አንድ አመት እንኳ አልሞላትም ነበር። ከዚያ በፊት ካገባቻቸው ሁለት ባሎች በድምሩ አራት ልጆች መውለዷንም ያውቃል። አራት ልጆች ከወለደች በሁዋላ ሶስተኛ ባል አግብታ በመኖር ላይ ያለችን ሴት፣ “ልዳርልህ” የሚል አሳብ ሲቀርብለት ተፈሪ መደንገጡ የሚጠበቅ ነበር። እና ድንጋጤውን ዋጥ አድርጎ ጥያቄ አቀረበ፣
        “ጌታዬ! ለኔ የምታስብልኝን ሁሉ በደስታ መቀበል ፍላጎቴ ነው። ዳሩ ግን መነን የራስ ልኡልሰገድ ሚስት ናት። እንዴት ሆኖ ነው ለኔ የምትዳረው?”
        ልጅ እያሱ በቁጣ ቃል ምላሽ ሰጠ፣
        “እሱን ለኔ ተወው። አንተ እዚህ ውስጥ መግባት የለብህም። የጠየቅሁህ ‘መነንን ታገባታለህ ወይስ አታገባትም?’ የሚለውን ነው…”
        በዚህ ጊዜ ተፈሪ መኮንን ምላሹን ሰጠ፣
        “እሺ አገባታለሁ”
        “እንግዲያው በ15 ቀናት ውስጥ ሽማግሌ ወደአዲሳባ ላክልን። አንተ አዲሳባ መምጣት አያስፈልግህም። ሽማግሌዎቹ ሚስትህን ይዘውልህ ይመጣሉ።”
        ሁለቱ የባላባት ልጆች በዚህ መልኩ ስለመነን በሚነጋገሩበት ወቅት መነን ከሶስተኛ ባሏ እና ከአራት ልጆቿ ጋር በሰላም በመኖር ላይ ነበረች። ለአራተኛ ጊዜ ለሌላ ባል እዳራለሁ ብላ በህልምዋ እንኳ አሳቡ አልነበራትም። ከሶስተኛ ባሏ ጋር በፍቅርና በደስታ መኖር ጀምራ ነበር።
        ተፈሪ መኮንን ከልጅ እያሱ ጋር የስልክ ንግግሩን ካበቃ በሁዋላ በቀጥታ ወደ ፀሎቱ ነበር የተመለሰው። ፀሎቱን እንዳበቃም ከአባቱ ወዳጆችና ነባር መኳንንቶች ጋር በጉዳዩ ላይ መከሩበት። ጋብቻውን ከመቀበል ውጭ ምርጫ አልነበራቸውም። መነንን እንደ ሙሽራ በማጀብ ወደ አራተኛ ባሏ የሚያመጧትም አራት ሲህ ወታደሮች ወደ አዲስአበባ ተላኩ። ከሞቀ ትዳሯ እና ከሶስተኛ ባሏ ነጥለውም ወደ ሃረር ወስደው ለተፈሪ መኮንን ዳሯት። ወይዘሮ መነን ወደ ተዘጋጀላቸው አራተኛ ባል እንድትሄድ ስትጠየቅ፣ “አምላክ በዚሁ በቃሽ ይበለኝ” ከማለት ሌላ አንዳችም ቃል እንዳልተነፈሰች ይነገራል። በርግጥም አምላክ ፀሎቷን ሰምቶላታል።
        አጤ ሃይለስላሴ ተገደው እቴጌ መነንን ካገቡ በሁዋላ እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ በጋብቻ ኖረዋል። እቴጌ መነንም ከአራተኛ ባላቸው በርካታ ልጆችን ለማፍራት በቅተዋል።
(የትረካ ምንጭ፣ ዘውዴ ረታ – ተፈሪ መኮንን)

Thursday 7 June 2012

አቶ መለስ ዜናዊ የህክምና ምርመራ ለማድረግ ብራሰልስ ገቡ




Thursday, June 7th, 2012 | Posted by zehabesha
አቶ መለስ ዜናዊ የህክምና ምርመራ ለማድረግ ብራሰልስ ገቡ
6
Share

ኢሳት ዜና:-አቶ መለስ ዛሬ በቤልጂየም ዋና ከተማ ብራሰል የተገኙት በህክምና ቀጠሮዋቸው መሰረት ነው። በአእምሮ እጢ በሽታ እንደተጠቁ የሚነገርላቸው አቶ መለስ፣ ብራሰልስ የገቡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ የሆኑትን አቶ ብርሀነ ገብረክርስቶስን አስከትለው መሆኑን ከኢምባሲ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አምባሳደር ብርሀነ ከአቶ መለስ ጋር የመምጣታቸው ምክንያት ቀደም ሲል ለ10 አመታት ብራሰልስ በነበሩበት ወቅት የአቶ መለስን ህክምና ያመቻቹ ስለነበር ቀረቤታ አላቸው በሚል ነው። አቶ ብርሀነ ገብረክርስቶስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኢታ ሆነው ሲመደቡ፣ ዶ/ር ካሱ ኢላላ በእግራቸው እንዲተኩ የተደረጉት ለአቶ መለስ ባላቸው ታማኝነትና ህክምና ለመከታተል በሚመላለሱበት ወቅት ሚስጢር እንደሚጠብቁ ታምኖባቸው ነው።

ከኣዲ ዳኣሮ በሮ በሮ…


ከኣዲ ዳኣሮ በሮ በሮ…

Dawit Abebe - Oslo, Norway
ዳዊት አበበ / ኦስሎ ኖርዌይ
የሚሚ ስብሃቱንና ዉሪዎቿን የጠረቤዛ ዝርጥጫ ዉይይት ካደመጥኩ በኋላ ሁለት ነገሮች ወደ አይምሮዬ  መጡ ፡፡ አንድም የዉሻን ባህሪ መመርመር ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአበበ ገላውን ማንነት መፈተሽ ፡፡
ከውሻ ባህሪ ልነሳ ! ፡፡ ስለዉሻ ባህሪ ይህንን ስፈትሽ አገኘሁ ፡፡
Dogs bond with the person who feeds them & interacts with them most.
“Loyalty” is a human concept. Dogs do not think in terms of “loyalty”….they think in terms of, “Who’s got my food? Who’s going to pet me?” They are opportunistic animals and largely form attachments with people who offer the most “benefit”….be it food, work or attention that they desire.
አዎ ! ታማኝነት ለሰው ልጅ የሚሰጥ ባህሪ ነው ፡፡ ዉሻ ደግሞ ተአማኒነት የሚል የሰው ልጅ ምግባር ሳይሆን ያለው ! የሱ ታማኒነት የሚገለጸው በሆዱ ብቻ ነው ፡፡ ጌታውን የሚያውቀው ፣ ሆዱን እስከሞላለት ድረስ ብቻ ነው ፡፡ ዉሻ የአድርባይነት ባህሪ የተላበሰ ፥ ጥቅሙን እስከ-አሟሉለት ድረስ ብቻ ጭራውን የሚቆላ እንስሣ ነው ፡፡

Wednesday 6 June 2012

የቴዲ አዲስ ክሊፕ “ጥቁር ሰው” ሙገሳም ወቀሳም እየቀረበበት ነው

የቴዲ አዲስ ክሊፕ “ጥቁር ሰው” ሙገሳም ወቀሳም እየቀረበበት ነው
Wednesday, June 6th, 2012 | Posted by zehabesha
(ዘ-ሐበሻ) የቴዲ አፍሮ አዲሱ የሙዚቃ አልበሙ መጠሪያ የሆነው ጥቁር ሰው በቪዲዮ ክሊፕ ወጥቷል። ክሊፑ ከወጣ በኋላ እየተሰጡ ባለው አስተያየት ብዙዎች እንደወደዱት እየገለጹ ቢሆንም አንዳንዶች ደግሞ ቴዲ ራሱን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ተያይዘው ከተሰሩ ፊልሞች ጋር አመሳሰለ እያሉ በመተቸት ላይ ይገኛሉ። በተለይ ድምጻዊው በቪድዮው ላይ ከሰማይ እንደሚመጣ በጉም ውስጥ ሆኖ መቅረቡን ያልወደዱት እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች የርሱ እንደዚህ መሆን ከዘፈኑ ጋር የሚያገናኘው ምንድ ነው? ሲሉም ይጠይቃሉ። ቴዲ አፍሮ ምንም ሠራ ምን የሚጥማቸው አድናቂዎቹ ደግሞ ይህን አይቀበሉም። ከመቼውም ግዜ የበለጠ አሪፍ ክሊፕ ሰርቷል እያሉ ነው። እርስዎ ከየት ወገን ነዎት? ክሊፑን ይመልከቱና አስተያየትዎን ይስጡ።

ፖሊስ አስለቃሽ ጢስ ይዞ ቤተ መቅደስ ገባ


በደብረ ይድራስ ቅ/ጊዮርጊስ ተቃዋሚዎችን ለመበተን
የተሰማራው ፖሊስ
አስለቃሽ ጢስ ይዞ ቤተ መቅደስ ገባ
 በአስለቃሽ ጢሱ ጸሎተ ቅዳሴው ታጉሏል፤ ሕፃናት፣ ምእመናንና አገልጋዮች ታፍነዋል::
 ለውዝግቡ መፍትሔ ያፈላልጋል የተባለ ጥምር ኮሚቴ ተቋቁሟል::
 ከ70 - 80 የሚደርሱ የደብሩ ሠራተኞችና ምእመናን እንደታሰሩ ናቸው::
 ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ ሊቀ ጳጳሱን በስልክ አነጋግረዋል::
(ደጀ ሰላም፤ ግንቦት 29/2004 ዓ.ም፤ ጁን 6/ 2012/ READ THIS ARTICLE IN PDF)፦ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከይዞታ ማስከበር ጋራ በተያያዘ
ትናንት፣ ግንቦት 27 ቀን 2004 ዓ.ም ጠዋት በአጥቢያው ምእመናን መካከል ግጭት ተቀስቅሷል፤ በግጭቱ የአንድ
ፖሊስ ሕይወት አልፏል፤ ስድስት ፖሊሶችና በርካታ ምእመናንም ተጎድተዋል፤ ብዙዎቹን የደብሩ ሰበካ ጉባኤ
አባላትንና ሌሎች ሠራተኞችን ጨምሮ በቁጥር ከ70 - 80 የሚሆኑ የአጥቢያው ወጣት እና አዛውንት ምእመናን
ከየመንደሩ በፌዴራል ፖሊስ አባላት እየተሰበሰቡ መታሰራቸው ነው የተነገረው፡፡
ግጭቱ እየቀጠለ በነበረበት ኹኔታ ለጸሎተ ቅዳሴ የተሰበሰበውን ሕዝብ ለመበተን በሚል ፖሊስ ወደ ቤተ መቅደሱ
ዘልቆ በመግባት አስለቃሽ ጭስ መጠቀሙ ተመልክቷል፤ በዚህም በመካሄድ ላይ የነበረው ጸሎተ ቅዳሴ ታጉሏል፤
ለቍርባን የተዘጋጁ ሕፃናት፣ ሌሎች ምእመናንና አገልጋዮችም በጭስ የመታፈን አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ የሕንጻ ቤተ
ክርስቲያኑ በሮችና መስኰቶች መንሥኤው ለጊዜው ባልታወቀ ኹኔታ የተበሳሱና የተሰባበሩ ሲሆን የደብሩ አስተዳደር
ቢሮዎች፣ የጥምቀተ ክርስትና ቤትና ሌሎችም በሮች “የተደበቁ ሰዎችን ለማሰስ” በሚል መዝጊያዎቻቸው እየተሰበረ
ፍተሻ እንደተካሄደባቸው ተገልጧል፡፡

«Mental tortur»

LIER MOTTAK: - Me kjenner til episodar frå Lier ventemottak som vitnar om rein rasisme frå tilsette og tidlegare leiing, seier leiar for antirasistisk senter, Kari Helene Partapuoli. Senteret åtvara om forholda ved norske ventemottak før opptøyane starta. Foto: Tom Henning Bratlie
                         «Mental tortur                                                                                                             »REPORT:      Conditions on the Lier and Fagerli departure centers are presented in heinous ordlag in a shadow report."The standard of living is low by Norwegian standards. Four grown men sharing a room at 5 times the 6-meter "reads the report. It contains several quotations from residents, who tells people damage themselves, lack of medical care and employees who act unprofessionally. Several places are ventemottaka known as "the center for mental torture" of residents.No political responseThis is some of what comes out of a shadow report on racism and discrimination. Anti Racist Centre has made the report in collaboration with various voluntary organizations Bar Association, Amnesty International and Norwegian People's Aid.- We have not received feedback from politicians on the report. It does not surprise, asylum policy is not a vote winner, says the head of the Anti-Racist Centre, Kari Helene Partapuoli. She delivered the shadow report to the Equality Audun Lysbakken in June this year. Shadow report is made to complement Norway's official report on racism and discrimination. Both reports are sent to the UN racial discrimination

Tuesday 5 June 2012

ትንሽ ቀደዳ፤ ስፖርት ለበስ ፖለቲካ ቀመስ! (አቤ ቶኪቻው)




Tuesday, June 5th, 2012 | Posted by zehabesha
ትንሽ ቀደዳ፤ ስፖርት ለበስ ፖለቲካ ቀመስ! (አቤ ቶኪቻው)
Share

ይህንን ጨዋታ ትላንት ላካፍላችሁ ነበር ያሰብኩት በቴክኒክ ምክንያት ሳይሳካልኝ ቀረና ይኸው ለዛሬ ሆነ!
በአለም ዙሪያ ያላችሁ የዝች ብሎግ አንባቢዎች እንዴት አላችሁልኝ…? ሰንበቶቹ እንዴት አለፉ!? ባመዛኙ አሸወይና እንደነበሩ እገምታለሁ! ከፊል ደመናማ የሆኑ እንደሚኖሩም እጠረጥራለሁ። ስለዚህ በጥቅሉ ደመናው እንዲጠራ፤ አሸወይናው እንዲጠናከር እየተመኘሁ እንደሚከተለው ይቺን ቀደዳ ይዤ ቀርቤያለሁ።
የቃላት መፍቻ
አሸወይና… ማለት አስደሳች፣ ማራኪ እና “ጣመኝ ድገሙኝ” የሚሉት ጊዜ ሲሆን፣
ቀደዳ … ማለት ደግሞ ወሬ፣ ወግ፣ ጨዋታ በማለት የአራዳ ልጆች ይፈቱታል። (እዝችው ጋ አራዳ ማለት ብዬ ደግሞ ልቀጥል እንዴ…? አራዳ ማለት ምን ማለት አንደሆነ የጋሽ ፍቅሩ ኪዳነን የፒያሳ ልጅ መፃፍ ሲያነቡ ወለል ብሎ ይገለጥልዎታል።
ቀደዳችን ተጀመረ፤

Journey of a jazz prodigy


By Liza Power
It is 3:00 am in Addis Ababa and Samuel Yirga is padding around his bedroom listening to Ethiopian folk tunes. The 25-year-old pianist doesn’t keep regular hours. He goes to bed at 8am, when the Ethiopian capital stirs itself for a new day, and spends the witching hours composing music. If his mobile drops out six times during a phone interview, he’s not bothered. He simply picks up mid-thought and speaks of the African mobile network as one might a temperamental acquaintance: ”You just keep going until you get through. This is how it is in Africa.”
It’s a philosophy that might well apply to his music, not only in respect to convincing his father to let him study it – the older man had a career in engineering mapped out for his son – but also in his determination to revisit an era of Ethiopian music few outside his homeland are familiar with: the folk tunes of the country’s central and northern highlands.

Samuel Yirga: "Many great musicians were living outside Ethiopia ... now the energy is coming back."

You’ll find echoes in his work of the ethereal quality that has won his Ethiojazz compatriots, such as Mulatu Astatke, international acclaim. Yet, while Yirga often works in the five-note scale born out of ancient Ethiopian Orthodox Church hymns, he reimagines them in compositions that meld jazz and classical influences.
Advertisement: Story continues below
”I like to experiment and give [old songs] new life,” he says.
They’re not songs from the heady, spirited ”swinging Addis” heyday of the 1960s, music that re-emerged in the 1990s care of the Ethiopiques recordings that won Astatke and his contemporaries a new audience

አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ፤ በአርቲስታ ታማኝ በየነ ዙሪያ ምሬት የተሞላበት ንግግርአደረጉ



አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ፤ በአርቲስታ ታማኝ በየነ ዙሪያ ምሬት የተሞላበት ንግግርአደረጉ
መጋቢት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ፤ በአርቲስታ ታማኝ በየነ ዙሪያ ምሬት የተሞላበት ንግግር አደረጉ።
በደቡብ አፍሪካ ጆሀንስበርግ ተገኝተው ከኢትዮጵያውያን ጋር ታላቅ ስብሰባ ለማድግ ቢያቅዱም፤ በስብሰባው 27 ሰዎች ብቻ በመገኘታቸው፤ በአንፃሩ አርቲስት ታማኝ በየነ እና ዶክተር ብርሀኑ
በቴሌ ኮንፈረንስ በመሩት ስብሰባ ላይ በጆሀንስበርግ የሚኖሩ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን በመሳተፋቸው ክፉኛ የተበሳጩት አቶ ሀይለማርያም፤ “ የኛ ሰዎች የት ገቡ?” በማለት የኢህአዴግ ስብሰባ
አስተባባሪ የሆኑትን ካድሬዎቹን በቁጣ መልክ ሲጠይቁ ተሰምተዋል።
ከዚያም ለሦስት ሰዓታት በቆየው ገለፃቸው፤ በየጊዜው የሚፈጥሩት ሥጋት እየጨመረ የመጣውን እንደ ግንቦት 7 ዓይነቶቹን የተቃዋሚ ድርጅቶች እንቅስቃሴ እንዴት መግታት እንደሚቻል
አብራርተዋል።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አክለውም፦“ደቡብ አፍሪካ፤ ለመንግስታችን ህልውና አስፈላጊና ስትራቴጅክ ጠቀሜታዋ ከፍ ያለ አገር ነች።ግንቦት ሰባት እዚህ መንገዱን እንዲሠራ ልንፈቅድለት አይገባም።
እነሱ፦እዚያው ዋሺንግተን ተወስነው መቅረት አለባቸው” ብለዋል።

ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት


አዬ፤ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
እስከ መቼ ድረስ እንዲህ፤ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን ሰቀቀንዋን፤ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺእኮ ማንም የላት…እና ፈርቼ እንዳልባክን፤ ሲርቀኝ የሃይልሽ ውጋጋን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፤ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፤ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን።
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ ተፈትቶ እንዳልከዳት ሰጋሁ…
ታዲያ ዛሬ ኢትዮጵያ ስትወድቅ፤ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በረኝነት ዕድሜ፤ ዓይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥንብ አንሳ ከንፎ፤ ወርዶ በጭለማ በርኖስ
ባክሽ እመ ብርሃን ይብቃሽ፤ ባክሽ ምስለ ፍቁር ወልዳ
ፅናት ስጪኝ እንድካፈል፤ የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ፤
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ፤ ከነደደችበት እቶን
የሷን ሞት እኔ እንድሞታት፤ ገላዋ ገላዬ እንዲሆን።…
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ።…  አቤቱ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ ሆይ!

ኢትዮጵያዊቷ በኩዌት ጎዳናዎች ራቁቷን ደም በደም ሆና ታየች


ኢትዮጵያዊቷ በኩዌት ጎዳናዎች ራቁቷን ደም በደም ሆና ታየች



SHARE THIS
TAGS
Share in top social networks!

www.maledatimes.com
ኢሳት ዜና:-ደሟን እያዘራች ራቁቷን በኩዌት ጎዳናዎች ላይ ስትሮጥ የነበረች ኢትዮጵያዊት ሴት በፖሊስ ተይዛ -በሳይካትሪስት ምርመራና ህክምና እንዲደረግላት ወደ ሆስፒታል መግባቷን አረብ ታይምስ ዘገበ።
አረብ ታይምስ ፦ “አል ራይ” የተባለውን የአገሪቱን ሳምንታዊ ጋዜጣ ጠቅሶ እንደዘገበው፤ በጎዳና ላይ ሲጓዙ የነበሩ እግረኞች  አፍሪካዊ መልክ ያላት ሴት ራቁቷን ሆና ደም እየፈሰሳት በጎዳና ላይ ስትሮጥ ማየታቸውን ለኩዌት የአገር ውስጥ ሚኒስቴር የኦፕሬሽን ዲፓርትመንት ሪፖርት ያደርጋሉ።
መረጃው የደረሳቸው የኩዌት ደህንነቶችም ወዲያው በመሰማራት  በጎዳና ላይ እርቃኗን ሆና ደሟን የምታዘራውን ሴት ይይዟታል።
በተደረገው ምርመራ ሴቲቱ በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ስትሠራ የነበረች ኢትዮጵያዊት  ሆና መገኘቷን ይፋ ያደረጉት የደህንነት ምንጮች፤ ደም  ሲፈሳት የነበረውም የገዛ እጇን በስለት በማረዷ እንደሆነ   አመልክተዋል።
ለዚህ  የተዳረገችውም ወደ ኩዌት የወሰዳት ስፖንሰሯ ወደ አገሯ ይመልሳት ዘንድ ያቀረበችለትን ጥያቄ ሳይቀበላት በመቅረቱ እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህም ሳቢያ ኢትዮጵያዊቷ እስከ መደባደብ ሳትደርስ እንዳልቀረች የጠቀሰው የኩዌት ፖሊስ፤ የተሟላ መግለጫ ለመስጠት የዶክተሮች ሪፖርት እየተጠበቀ መሆኑን  አስታውቋል።
በተለየ መልኩ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን  በአሠሪዎቻቸውና በስፖንሰሮቻቸው የተለያዩ በደሎች እየተፈፀሙባቸው እንደሚገኙ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።

በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ Coordinating committee of exiled members of Ethiopian Teachers Association የተሰጠ መግለጫ

በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ
Coordinating committee of exiled members of Ethiopian Teachers Association
የተሰጠ መግለጫ                         
                                                             ግንቦት 23 ቀን 2004 ዓ.ም
ለማደናገር ሰይጣንም ከቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳል!!
የሌባ ዓይነደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ!!
ያለንበት ወቅት እንደ አገር፣እንደ ሕዝብ የምንገለጽባቸው እሴቶች ሁሉ ተከልሰው፣ተበርዘው፣ፈር
ስተው እንዲያዘግሙ በሂደትም ከተቻለ ጭራሹን እንዲጠፉ የሚሠራበት ወቅት ነው።ለዚህ ደግሞ የጥፋት
ፊታውራሪው ወያኔ/ኢህአዴግ ነው።ይህ በመንግስት ስም በጫንቃችን ላይ የተጫነ ድርጅት አባላቱ አፋሽ
አጎንባሽ አጫፋሪዎቹ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ለኢትዮጵያዊነት፣ ለሕዝብ ወሳኝነትና ለሰብአዊነትም
እንጥፍጣፊ በጎ አመለካከት በተፈጥሮ ባህርያቸው የለም።
በግለሰብ፣ በቤተሰብ፣ በማህበረሰብ፣ በአገር፣ በአህጉር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቅቡል የሆኑትን
ቁምነገሮች ማለትም ዲሞክራሲ፣ ሰብአዊ መብት፣ ሕግና ፍትህ እያነሱ እየጣሉ መደስኮሩ ላይ ከኛ በላይ ላሳር
ነው የሚሉን።ከውስጥ የሚመነጭ ጽኑ እምነትና ለታይታ የሚነገሩና ወይም የሚሰሩ ግን ለየቅል ናቸው።
እንዲያውም አሁን አሁንማ ወያኔ ማስመሰሉንም እየተወ ባፈጠጠና ባገጠጠ መልኩ በማናአለብኝነት ያሻውን
የሚሰራ እንደሆነ ነው እውነታው የሚያሳየው። ሺህ ዓመታት የቆየውን ታሪካችንን እየሰረዘ እየደለዘ የራሱን
መንደር በቀል ወያኔያዊ ህልም እንደታሪክ ሊያስተምረን ይዳዳዋል።በመፈቃቀድ ላይ የተመሠረተች ኢትዮጵያ
እንፈጥራለን እያለ በማሾፍ በዘር፣ በሃይማኖት……… በመከፋፈል የቻለውን ያህል ጥሯል። ተዋዶ፣ ተዋልዶ፣
በደምም ተዋህዶ ለረዥም ዘመናት በኢትዮጵያዊነት ክር የተሳሰረውና በአብሮነት የቆየው ሕዝብ ይኽን
በክፋትና በዘረኝነት የሰከረው ቡድን የማጥፋት ዕቅዱ ግብ እንዲመታ አልተባበረውም።ይህ እንዳለ ሆኖ2
የትናንቱን ማስታወስ፣ የዛሬውን መረዳት፣ የነገውንም መገመት የተሳናቸው ግለሰቦችና ቡድኖች የቆየውን
የአንድነት ትስስርና ብሔራዊ ማንነት ለማዳከም በመስራት ላይ ይገኛሉ።

Ethiopians in America rally to defend Waldba Monastery




Monday, June 4th, 2012 | Posted by zehabesha
Ethiopians in America rally to defend Waldba Monastery
Share

WASHINGTON, DC – Ethiopians living in the US converged on the nation’s capital on Monday and protested against the state-sponsored destruction of Waldba Monastery, a 5th century sacred site worth declaring “Heritage of Humankind.”
The rally was in response to a call by church leaders who wanted to stop the government from committing a sacrilege of the highest degree. The government has deployed troops to keep the people from defending the holy site that the government has planned to turn it into a sugar plantation.

Monday 4 June 2012

ሁለት ድንቅ የጥበብ ልጆች የደመቁበት ምርጥ ምሽት


ሁለት ድንቅ የጥበብ ልጆች የደመቁበት ምርጥ ምሽት

 ማክሰኞ ምሽት እንዲህ ሆነ፡፡ “የዛሬን ቴአትር በክብር እንግድነት ተገኝተው የሚመርቁልን እጅግ በጣም የምንወዳቸው ጥንዶች ናቸው፡፡ የመጀመሪያውን ላስተዋውቃችሁ…” ማክሰኞ ግንቦት 21 ቀን 2004 ዓ.ም በአዲስ አበባ የቴአትርና ባህል አዳራሽ መድረክ ላይ ተፈራ ወርቁ፤ በአለማየሁ ታደሰ ተደርሶ ስለተዘጋጀው “የብዕር ስም” የተሰኘ ቴአትር እያስተዋወቀን መድረኩን በመምራት ላይ ነው፡፡“የመጀመሪያው እንግዳችን…” ቀጠለ ተፈራ ወርቁ፡፡ “እጅግ የምንወደውና የምናደንቀው ድምፃዊ፣ የግጥምና የዜማ ደራሲ…” ማንን እንደሚያስተዋውቀን ለመስማት ልባችን ቆሟል፡፡ “የዜማ ደራሲ… ቴዲ አፍሮ” ባልተጠበቀው እንግዳ እዚያ መገኘት የቴአትር አዳራሹ በጩኸት ተናወጠ፡፡ “ሁለተኛዋ እንግዳችን ሞዴልዋ…” አስተዋዋቂውን ማንም ሊያስጨርሰው አልቻለም፡፡ ሁሉም የተመካከረ ይመስል ባንድ ድምፅ “ፀባየ ሰናይ” በማለት ሕዝቡ ቀድሞ ተዋወቃት፡ቴዲ አፍሮ እጅግ ውብ ከሆነችው ባለቤቱ ጋር እጅ-ለእጅ ተያይዞ፣ ወደ አዳራሹ ሲገባ በአዳራሽ የተሰበሰበው ህዝብ በሙሉ ከመቀመጫው በመነሳት በጭብጨባና በፉጨት ተቀበለው፡፡

ቴዲም በተለመደው ትህትናው ወገቡ እስኪቀነጠስ አጐንብሶ እጅ በመንሳት፣ አድናቂዎቹን አመሰገነና  ወደተዘጋጀለት መቀመጫ ከባለቤቱ ጋር አመራ፡፡አለማየሁ ታደሰ“ቴአትር ሕይወቴ ካልሆነ ሞት ምርጫዬ ነው” ያለው አርቲስት ማን ነበረ?… አለማየሁን ለመግለፅ ከዚህ የተሻለ አባባል ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ ለትወና የተፈጠረ፣ ድንገት መድረክ ላይ ብቅ ሲል፤ የማይደክመው የማይሰለቸው፤ የሚተውን ብቻ ሳይሆን የሚፅፍና የሚያዘጋጅ፤ በመድረክ ብቻም ሳይሆን በፊልምና በተከታታይ ቲቪና የሬዲዮ ድራማዎች ላይ የማናጣው፣ ከንጉስ እስከ የንጉስ አጫዋች፣ ከጀግና እስከ ፍቅረኛ፣ ከምንጠላው ክፉ ባህሪ እስከምንሳሳለትና የምናለቅስለት ምስኪን ሰው …

የአማራ ተወላጆች እንዲፈናቀሉ ያዘዙትና በሙስና የተወነጀሉት ሽፈራው ሽጉጤ ካናዳ ይመጣሉ (አኢጋን)


የአማራ ተወላጆች እንዲፈናቀሉ ያዘዙትና በሙስና የተወነጀሉት ሽፈራው ሽጉጤ ካናዳ ይመጣሉ (አኢጋን)

June 4th, 2012
ተቃውሞ ፍራቻ ጉዞው በምስጢር አንዲያዝ መመሪያ ተላልፏል

በጉራፋርዳ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች እንዲፈናቀሉ ትዕዛዝ የሰጡትና በከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ በፓርቲያቸው የተበየነባቸው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የሚመሩት ቡድን ካናዳ ለስራ ጉብኝት እንደሚመጣ ተሰማ። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ምንጮች እንዳስታወቁት አቶ ሽፈራውን ተቃውሞ እንዳይገጥማቸው ጉብኝቱ በተለይ በውጪ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች እንዳይሰሙት በምስጢር እንዲያዝ መመሪያ ተሰጥቶ ነበር።

አቶ ሽፈራው ካላቸው የፖለቲካ ሥልጣን በተጨማሪ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሆኑ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት፣ የእርሻ ኮሌጁን ዲንና የተለያዩ ሹመኞችን አስከትለው በካናዳ በሚገኘው የሳስካችዋን ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት ለማድረግ ሰኔ 3ቀን 2004ዓም (ጁን 10 ቀን 2012) ካናዳ ይደርሳሉ፡፡ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከወራት በፊት በጉራፋርዳ ይኖሩ በነበሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ለተፈፀመው ግፍ መሪ ተዋናይ መሆናቸውን በስማቸው ተጽፎ የፈረሙበትን ደብዳቤ ዋቢ በማድረግ የጋራ ንቅናቄያችንን ጨምሮ በርካታ የአገርና የውጪ መገናኛዎች እንደመሰከሩባቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ሠራዊት በኤርትራ ጦር ላይ ጥቃት ፈጸመ


የኢትዮጵያ ሠራዊት በኤርትራ ጦር ላይ ጥቃት ፈጸመ
SHARE THISየ
     
TAGS
EritreaEthio Eritrea WarEthiopiaEUUN



የኢትዮጵያ ሠራዊት ባለፈው ሳምንት ኤርትራ የነፃነት ቀኗን ስታከብር በነበረበት ዕለት፣ ባድመ በሚገኘው የኤርትራ ጦር ላይ ጥቃት ማድረሱ ተገለጸ፡፡ ወታደራዊ ጥቃቱ በትግራይ አካባቢ በቅርቡ በኤርትራ ጦር ታፍነው ለተወሰዱ ኢትዮጵያውያን አጸፋዊ ምላሽ ነው ተብሏል፡፡

ግንቦት 16 ቀን 2004 ዓ.ም. የኤርትራን ድንበር ጥሶ የገባው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባድመ አካባቢ በሰፈረው በአንድ ብርጌድ የኤርትራ ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት ሰንዝሮ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ገልጾአል፡፡

በጥቃቱ በርካታ የኤርትራ ወታደሮች የመቁሰልና የሞት አደጋ የደረሰባቸው መሆኑን፣ እስከ ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው በርካታ የኤርትራ ጦር አመራሮችም እጃቸውን እንደሰጡ ታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከወራት በፊት በተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፣ የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚፈጽመው ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ጦር ሰሞኑን በኤርትራ ላይ የወሰደው ወታደራዊ ጥቃት የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ አካባቢ ለሚፈጽሙት አፈና አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የወሰደውን ዕርምጃ በማስመልከት ከኤርትራ በኩል የተገለጸ ነገር የለም፡፡
(ምንጭ ሪፖርተር)

Share this:

South Africa: The TPLF Inspired National Anthem Heckled By Ethiopians


South Africa: The TPLF Inspired National Anthem Heckled By Ethiopians
SHARE THIS
       
TAGS

The Horn Times News Letter – 4 June 2012
By Getahune Bekele –Rustenburg, South Africa

Soccer match turned in to anti Zenawi uprising.
The TPLF inspired national anthem heckled by Ethiopians.


South Africa: The TPLF inspired national anthem heckled by Ethiopians www.maledatimes.com

More than one thousand flag-waving Ethiopians used the June 3 world cup qualifying soccer match against South Africa at Royal Bofokeng stadium to express their anger towards the brutal iron hand rule of PM Meles Zenawi.

The drama started during the rendition of the national anthem as the vociferous and enthusiastic Ethiopian crowed heckled and jeered the TPLF inspired anthem and loudly sang the patriotic “Ethiopia yegna Memekia.” Much to the confusion of the players.

The Ethiopians then turned their attention towards the less than 30 TPLF cadres who were waving the TPLF flag and the South African security personnel watched in amazement as the marauding anti Zenawi crowed confiscated the flag.

As the match got under way, the TPLF cadres cut a lone figure at the eastern stand of the magnificent world cup stadium.

The match was as dramatic

Spurred on by the patriotic crowed, the Ethiopian national team players dished out one of the most amazing displays of one touch soccer  in a very long time.

Playing as a lone striker, the diminutive and tigerish Saladin Said showed his more illustrious South African internationals how soccer should be played.

On the 27th minute of the first half, Saladin dispossessed Getafe defender Shepo Masilela, turned Totenham Hotspur defender Bongani Kumalo inside out, and hit a screamer past the hapless Bafana goalkeeper Itumeleng Kune

Saladin then run straight to the Ethiopian crowed and celebrated his breath-taking goal in traditional Ethiopian folk dance.

After the goal, Bafana pushed hard for the equalizer but the Ethiopian defense Marshaled by Tafese Tsegaye stood firm.

Young goalkeeper Sisaye Bassa also pulled off some great saves to frustrate the South Africans.

Although Bafana had equalized in the second half, at the final whistle, the South African players were seen rolling on the ground in agony as the Ethiopian national team players celebrated with the anti Zenawi refugees.

በአበበ ገላው ዙሪያ – የግጥም ጦርነት በኢሕአዴጉና በነጻነት ትግሉ ደጋፊ



Sunday, June 3rd, 2012 | Posted by zehabesha
በአበበ ገላው ዙሪያ – የግጥም ጦርነት በኢሕአዴጉና በነጻነት ትግሉ ደጋፊ
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ አበበ ገላው አቶ መለስ ዜናዊን በአደባባይ ካቀለለና ካስኮረፈ በኋላ በርከት ያሉ ግጥሞች ተጽፈዋል። የኢሕአዴግ ደጋፊዎች እንደተበሳጩ፤ የነጻነት ትግሉ ደጋፊዎች እንደተደሰቱ እስከዛሬ ደርሰዋል። በሁለቱም ወገን ያሉት በግጥም የሚያደርጉት መሸናቆጥ ለአንባቢ ቀልብ የሚስብ ቢሆንም በተለይ ከመለስ ዜናዊ ደጋፊዎች ዘንድ የሚሰማው “ደማችሁን ነው የምንመጠው” የንዴት አገላለጽ ትንሽ ይቀፋል። ዛሬ ድረ ገጻችን ከደረሱት በርካታ የድጋፍ ግጥሞችና የተቃውሞ መጣጥፎች መካከል ከኢሕአዴግ ወገን ደጋፊዎችም እንዲሁም ከነጻነት ትጉሉ ጎን ከቆሙት ወገኖች መካከል የአንዱን ልናቀርብ ወደድን።
በኤገን ሚኒሶታ ነዋሪ የሆነው አስመላሽ ሃይሉ የተባለው አፍቃሬ- ሕወሓት አበበ ገላውን በመቃወም “ዘመናይ ሰባኪ” ሲል ግጥም ጽፏል። በአንድ በኩል ደግሞ በዩቲዩብ ስሙን ያልገለጸ ገጣሚ በቪድዮ አቀናብሮ አበበ ገላውን “የጠላት አንገት ይደፋ” ሲል አሞካሽቷል። “የጠላት አንገት ይደፋ” ግጥምን በቅድሚያ ያድምጡና ከዛም የኢሕ አዴጉን ደጋፊ ግጥም ደግሞ ከታች ያንብቡ። በግጥሞቹ ዙሪያ የራሳችሁን አስተያየት መስጠት መታችሁ ነው።


Sunday 3 June 2012

ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ደ. አፍሪካ የሄደው ብሔራዊ ቡድናችን 1 ለ 1 ተለያየ




Sunday, June 3rd, 2012 | Posted by zehabesha
ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ደ. አፍሪካ የሄደው ብሔራዊ ቡድናችን 1 ለ 1 ተለያየ
3
Share

ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ለመጫወት ወደዚያው ያቀናው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካ ጋር በሃገሩ ላይ ነጥብ ተጋርቶ ወጣ። ምንም እንኳ በሮያል ባፎኪንግ ስታዲየም በተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሰላዲን ሰኢድ በ30ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መሪነቱን ቢይዝም በ71ኛው ደቂቃ በተቆጠረበት ግብ አቻ ለመውጣት ግድ ቢሆንበትም ውጤቱ ደቡብ አፍሪካ ካላት ስምና ዝና አንጻር ከበቂ በላይ ነው እየተባለ ነው።
የኢትዮጵያ ቡድን በ72 ደቂቃ አሉላን በአይናለም ሲቀይር ፤የደቡብ አፍሪካ ቡድን በ90 ደቂቃው ጨዋታ ጊዜ ሶስት ተጨዋች ቀይሯል፡፡ማዳካስካራዊው የመሃል ዳኛ ለአበባው ቡጣቆ በ23ኛው፤ለምንያህል ተሸመ 78ኛው፤ለሲሳይ ባጫ85ኛው፤ለአዲስ ህንፃ በ91ኛው ቢጫ ካርድ ሲያሳዩ፤ለደቡብ አፍሪካ ቡድን አንድ ቢጫ ካርድ ሰተዋል፡፡
የኢትየጵያ ቡድን ከሜዳው ውጪ ነጥብ ተጋርቶ መውጣቱ በሜዳውና በደገፊው ፊት ለሚያደርገው የመልስ ጨዋታ ትልቅ ብርታት ይሰጠዋል፡፡
አሰልጣኝ ሰውነት ከመሄዳቸው በፊት በሰጡት መግለጫ ‹‹ የሰላዲን ቡድኑን መቀላቀል ያለብንን ግብ የማስቆጠር ክፍተት ይሞላዋል ››ብለው ነበር፡፡እንዳሉትም ሰላዲን በናይጄሪያ ላይ ያሳየውን የግብ አዳኝነት ብቃት በደቡብ አፍሪካ ላይ በመድገም አሳይቷል፡፡

በነገው ዕለት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ይደረጋል።





Sunday, June 3rd, 2012 | Posted by zehabesha
በርከት ያሉ ምዕመናን በዋልድባ ጉዳይ በሚደረገው ሰልፍ ለመካፈል ወደ ዲሲ እየተመሙ ነው
13
Share
(ዘ-ሐበሻ) በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ መንግስት የዋልድባን ገዳም እየተፈታተነበት ያለውን ድርጊት በመቃወም በነገው ዕለት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ይደረጋል። በዋሽንግተን ዲሲ ለሚደረገው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ለመሳተፍ ከሚኒሶታ ኢትዮጵያውያን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች በመኪና ተጉዘው ዋሽንግተን ዲሲ ገብተዋል።
ትናንት ቅዳሜ ጁን 2 ቀን 2012 ከሚኒሶታ የተነሱት ምዕመናንን ጨምሮ ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የተንቀሳቀሱ ምእመናን በዋሽንግተን ዲሲ ሲደርሱ እዚያ የሚኖረው ምእመናን ደማቅ አቀባበል እንደተደረገለት የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዘጋቢዎች ከስፍራው ተናግረዋል።
ከሚኒሶታ የተንቀሳቀሰው ቡድን 8 የ እንግሊዘኛ እና 8 የአማርኛ መፈክሮችን ይዞ እንደሄደ የታወቀ ሲሆን በአጠቃላይ በዋሽንግተን ዲሲ እንዲሁም በሎስ አንጀለስ ነገ ጠዋት በሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ወደ 40 የሚጠጉ መፈክሮች እንደተዘጋጁ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሎስ አንጀለስና በሌሎች የአለማችን ክፍሎች የሚያዙት 18 የእንግሊዘኛ መፈክሮች የሚከተሉት ናቸው። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያዘውን 18 የ እንግሊዘኛ መፈክሮች PDF ለማየት እዚህ ይጫኑ
ከሚኒሶታ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ የሄዱ ም እመናን የያዟቸው 16 የአማርኛና የ እንግሊዘኛ መፈክሮችን PDF ለማየት እዚህ ይጫኑ
ነገ ጁን 4/2012 በዋሽንግተን ዲሲ የሚደረገውን ሰልፍ ለመዘገብ የዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ሪፖርተርም ዋሽንግተን ዲሲ ገብታለች። ዘገባዎችን እንዳደረሰችን ለድረ ገጻችንን አባቢዎች እንደምናቀርብ ከወዲሁ እንገልጻለን።

በAውራምባ ታይምስ የተቆረጠው የታማኝ ቃለ-መጠይቅ


በAውራምባ ታይምስ የተቆረጠው የታማኝ ቃለ-መጠይቅ
Aርቲስት ታማኝ በየነ ከAውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ጋር የቃለ-ምልልስ  Eንዲያደርግ ከAዘጋጁየ ቀረበለትን
ጥያቄ ተቀብሎ ቃለ-ምልልስ  Aድርጎ ነበር፡፡ ቃለ-ምልልሱ በጋዜጣው ታትሞ ከወጣ በኋላ ግን: ለጋዜጣው
Aዘጋጅ በላከው ደብዳቤ "ቃለ ምልልሱን Aነበብኩት፡፡ ስሜንና ፎቶግረፌን ከመያዙ በቀር የኔ ሀሳብ የምለው
Aንድም በውስጡ ባለመኖሩ በጣም  Aዝኛለሁ፡፡"  ሲል ቅሬታውን ገልጿል፡፡ የAውራምባ ታይምስ  Aዘጋጅ
ቃለ-ምልልሱን  Eንዳለ ቢያወጣው በህይወቱ ላይ  Aደጋ ሊያስከትልበት  Eንደሚችል ገልጾ ሙሉውን
ባለማተሙ ይቅርታ ጠይቋል፡፡   ለAንባቢያን ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ ሙሉውን ቃለ-ምልልስ  Eንደሚከተለው
Aውጥተነዋል፡፡
ከAውራምባ ታይምስ:- Eንግዲህ በAሁኑ ሰዓት ለAገር ለወገን ትልቅ ስራ ሰርተው ያለፉ ታላላቅ
Iትዮጵያወገኖችን በማስታወስ ብዙ  Eንቅስቃሴዎችን በማከናወን ላይ  Eንደምትገኝ ይታወቃል፡፡  Eስኪ
ለAገር ውስጥ Aንባቢ ጠቅለል Aድርገህ ብትገልጽልኝ?

ቴዲ ወይስ ታማኝ


                                                              ቴዲ  ወይስ ታማኝ 


እኔ ለጸብ ለምን እቸኩላለሁ?
ማንምሰው ደግሞ የፖለቲካን ጉዳይ የጠላውን ሰው የሚያወግዝበት፤የወደደውን ሰው
የሚያሞካሽበት የግል መሣሪያ    አይደለም። ከዚህ  Aስተሳሰብ ካልወጣን በጣም ትልቅ
ሆና፣ ፍትህ የነገሠባትን ታላቂቱን ኢIትዮጵያ ለማየት በጣም  አስቸጋሪ    ይሆናል።
ለማንኛውም    በየቦታው    ለነበረው ሁኔታ ጥሩመስተንግዶ    አድርገው    ለተቀበሉን
ኢትዮጵያውያን  ከፍ  ያለ  ምስጋናዬን  አቀርባለሁ።  በተለይ  በተለይ  ደግሞ  እስር
ቤት  ሆኜ  ብዙ  በመጨነቅ፣ በመፀለይ፣  ከዚያም  አልፎ  ሰልፍ  በመውጣት  ብዙ
ስለእኔ    ለከፈሉት    ኢትዮጵያ ውያን    ወገኖቼ    ከፍተኛ   ምስጋናዬን    እያቀረብሁ፤
የፍቅር   ሠራዊት    የሆነውን    ባንዳችንን  (የሙዚቃ   ጓዳችንን)   ይዘን    ገና    ብዙ
ለመሄድ    እንበረታለን    ከእግዚAብሔር    ጋር።    ቴዲ  አፍሮ ይህን ያለው በስዊድን
ከጋዜጠኛ ያሬድ ክንፈ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስነበር። ጋዜጠኛው በኖርዌይ ቴዲ
አፍሮ ቦይኮት  እንዲደረግ ሰዎች ሲያስተባበሩ  እንደነበር ጠቅሶ ቴዲን በጉዳዩ ላይ
ሲጠይቀው ነበር ይህን ያለው።ቴዲ  አፍሮ ከእስር ከተፈታ በኋላ ባደረጋቸው የሙዚቃ
ኮንሰርቶች ‘’ጃ ያስተሰርያል” ከሚለው ዘፈኑ ውስጥ ገዢውን ፓርቲ ይነካል የሚባለው
17 መርፌ የሚለውን ግጥም ቆርጦ ማውጣቱ በብዙዎች ዘንድ ውግዘትን እያስከተለበት
ሲሆን በአንጻሩ ለውግዘት ያልቸኮሉ ወግኖችም ተቀምጠዋል። የዘሐበሻ ጋዜጣ
ካነጋገራቸው  ኧንድ ስማቸውን መጥቅስ ያልፈልጉ ሰው  እንዳሉት  ‘ቴዲን  እኛ
የወደድነው ሄዋን  እንደዋዛን ስለዘፈነ  አይደለም። በድፍረቱና በተለይም ጃ ያስተሰርያል
በሚለው ዘፈኑ Eንጂ። Aሁን ያንን ቆርጦ ከዘፈነው Eውነትም ቴዲ Aልተፈታም ማለት
ነው”  ሲሉ ሌላ  Aስተያየት ሰጪ ደግሞ  ‘ቴዲ የፈለገውን ማድረግ ይችላል  Eኛ
Eንወደዋለን”  ይላሉ። ይህ በEንዲህ  Eንዳለ ቴዲ  Aፍሮ ከEስር ቤት ከወጣ በኋላ
ባደረጋቸው ነገሮች Aሜሪካ የሚገኘው ታማኝ በየነ Eና Aንዳንድ Iትዮጵያዊያን ደስተኛ
Eንዳልሆነ በማስመሰል በIትዮጵያ የሚታተመው Eቴጌ መጽሄትን ጨምሮ በራዲዮ ፋና
ላይ የሚተላለፈው Iትዮፒካ ሊንክ ፕሮግራሞች  ‘የቴዲ  Aፍሮ ወቅታዊ  Aቋም ታማኝን
Aበሳጭቷል"  በሚል በየIንተርኔቱ  Eየተነዙ ያሉት ወሬዎች ሕዝቡን  Eያደናበሩት
መሆኑን የተነገነዘበው የዘሐበሻ ጋዜጣ የጉዳዩን ባለቤት በግልጽ  Aነጋግሮ የተጣራውን
ነገር ሕዝቡ Eንዲያገኝ ያደረገው ጥረት ታማኝን በማግኘት ተሳክቶልናል።
ዘሐበሻ፦ ታማኝ  Aንተ ለመጽሄቱ በቴዲ  Aፍሮ  Aቋም ላይ ደስተኛ  Aይደለሁም ብለህ
ተናግረሃል?

አንገት ሲደፋ ምን ፈሰሰ?


                                                  አንገት ሲደፋ ምን ፈሰሰ?
SHARE THIS
       
TAGS

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

ሰሞኑን አዲስ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፎቶግራፍ በብዛት በያለበት ይታይ ነበር፤ ያዘነ፣ የተከዘና አንገቱን የደፋ መለስ ዜናዊ! እኔን ቀልቤን የሳበው የጠቅላይ ሚኒስትሩን አንገት ሊያስደፋ የቻለው ነገር አይደለም፤ ወይም አበበ ገላው የተናገረው ነገር አይደለም፤ አበበ ገላው የተናገረውን ለመናገር ሙሉ መብት አለው፤ በተባለው ነገር የማይስማማ ሰው በማስረጃም ሆነ ያለማስረጃ የተባለውን ለማስተባበል መሞከር መብቱ ነው፤ የአሜሪካኑን ፕሬዚዳንት፣ ወይም የእንግሊዙን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲህ ያለ ሁኔታ ቢያጋጥማቸው፣ ወይም በጆርጅ ቡሽ ላይ አንዱ ኢራቃዊ እንዳደረገው ጫማውን እያወለቀ ቢወረውርም ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይኖርም፤ በ1928 ነው 29 አጼ ኃይለ ሥላሴ በቀድሞ የዓለም መንግሥታት ማኅበር መድረክ ላይ ሲናገሩ የኢጣሊያ ፋሺስቶች ያሰማሩአቸው ሰዎች ንግግሩን ለማደናቀፍ ጩኸትና ፉጨት ያሰሙ ነበረ፤ አጼ ኃይለ ሥላሴን አንገታቸውን አላስደፋቸውም፤ አበበ ገላው የወረወራቸው ቃላት ናቸው፤ ቃላቱ እውነትን የሚገልጹ ከሆነ በተግባራዊ ማረሚያ ይለወጣሉ፤ ቃላቱ ሐሰትን የሚገልጹ ከሆኑ እውነትን በሚገልጹ ቃላት ይደመሰሳሉ።


                                                      አንገት ሲደፋ ምን ፈሰሰ?

Mesfin Woldemariam (Prof.)

እዚህ ላይ አንድ ሌላ ነገር እናስታውስ፤ በመስከረም ግድም ይመስለኛል አቶ ኢሳይያስ አፈወርቅ በኒውዮርክ ነበረ፤ በዚያን ጊዜ በአንድ ስቴድየም ውስጥ የኤርትራ ተወላጆች ሁሉ (የቀረም ያለ አይመስልም!) በስቴድየሙ ታምቀው የኢሳያስን ዲስኩር ከሰሙ በኋላ አስተያየታቸውን እየሰጡና ጥያቄያቸውንም እየጠየቁ ሲወያዩ ነበር፤ ያስቀኑ ነበር፤ የኤርትራም ማኅበረሰብ እንደኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ውስብስብና ጉራማይሌ ነው፤ መሪው ህዝቡን ሳይፈራ፤ ሕዝቡም መሪን ሳይፈራ ተቀራርበው ለመወያየት መቻላቸው እኛን የትና የት ጥለውን እንደሄዱ አያሳይም የሚል አለ? ይህንን እውነት ቢያንስ የዛሬ አሥራ አምስት ዓመት ግድም ሪፖርተር የመጀመሪያውን መጽሔት ባወጣ ጊዜ ሽፋኑ የኢሳይያስ አፈወርቅ ፎቶግራፍ ነበር፤ የመለስ አልነበረም፤ ለኢሳይያስም ከተደረደሩት የውዳሴ ርእሶች አንዱ ኢሳይያስ ለሕዝብ ቅርብ መሆኑ ነበር፤ በአንፃራዊ ዝምታ መለስን ይጎሽም ነበር፤ ዛሬ በጠብ ላይ በመሆናችን እውነትን የምናይበት ዓይናችን ተቸግሮ ይሆናል፤ ለማናቸውም የሪፖርተርን ዘገባ ያስታወስሁት በኒውዮርክ በተደረገው የኤርትራ ተወላጆች ስብሰባ የተነሣ ነው፤ ለመሆኑ በኒውዮርክ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር ስብሰባ ቢጠራ መጀመሪያ ስንት ሰዎች ይገኛሉ? ከተገኙትስ ጋር የሠለጠነ ውይይት ይደረጋል? ወይስ በፓርላማ እንደተለመደው ያለ ይሆናል? ሳይናናቁ መሪና ሕዝብ ተከባብረው በነፃነት ሀሳባቸውን መለዋወጥ መቻል ትልቅ እርምጃ ነው።
በኒውዮርክ የተሰበሰቡትን የኤርትራ ተወላጆች ቁጥር የሚያህል ኢትዮጵያውያን ተሰብስበው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መወያየት የሚችሉ ቢሆን እንዴት ያኮራኝ ነበር፤ በበኩሌ ባንስማማም እንነጋገር እያልሁ ስጮህ ብዙ ጊዜ ሆነኝ፤ ክርር ምርር ብሎ ከዚህ ፍንክች አልልም፤ ለአጭሩም፣ ለረጅሙም፣ ለወፍራሙም፣ ለቀጭኑም፣ ለክርስቲያኑም ለእስላሙም፣ ለሁላችሁም የሚበጀውን እኔ አውቃለሁ ማለቱ አያቀራርበንም፤ መናናቅ አያቀራርበንም፤ መፈራራት አያቀራርበንም፤ አበበ ገላው የተናገረው እውነት መሆኑንና አለመሆኑን ወደጎን እንተወውና በኢትዮጵያ ውስጥ እነዚያኑ ቃላት፣ በዚያው የጋለ ስሜት ያለፍርሃት በልበ ሙሉነት መግለጽ የሚቻል ቢሆን የአሜሪካው ድራማ አያስፈልግም ነበር፤ ዋጋም የሚሰጠው አይሆንም ነበር፤ በአሜሪካ በድንገትና ዓለም ሁሉ በሚያይበት መድረክ ስለ መለስ ዜናዊ የተባለው ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ተዝናንቶና ኮርቶ ሊያዳምጥ የሚችልበትን መድረክ በሃያ ዓመታት ውስጥ ሳያዘጋጅ መቅረቱ አንገቱን ለማስደፋቱ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በኢትዮጵያ ሳይሆን በአሜሪካ፣ በኢትዮጵያ ፓርላማ ሳይሆን በትልቅ ዓለም-አቀፍ ስብሰባ፣ ጥቂት የአፍሪካ መሪዎች ብቻ በተጋበዙበት ስብሰባ፣ በተለይም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአፍሪካ ተናጋሪ ሆኖ በተጋበዘበት የታላላቅ መሪዎች ስብሰባ ላይ መገኘቱ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ሊያኮራ የሚገባው ነገር ነበር፤ ቢመቸን የሚያኮራን ነበር፤ መኩራቱ ሳይሆንልን ቢቀርም የማናፍርበት በሆነ መልካም ነበር፤ ምስጋናና ከንቱ ውዳሴ እንደጠበል በሚረጭበት ትልቅ ዓለም-አቀፍ ስብሰባ ላይ ዘለፋና ነቀፌታ መስማት አንገትን ያስደፋል፤ ነገር ግን ከመለስ ዜናዊ ጋር ኢትዮጵያ በዚያ ስብሰባ ላይ አንገትዋን አልደፋችም?
በግድም ይሁን በውድ አንድ መሪ አንድ ሕዝብ አናት ላይ ከተቀመጠ፣ ብዙ ነገሮች ያያዝዋቸዋል፤ ከነዚህ ነገሮች አንዱ ክብር– ወይም ውርደት ነው፤ ሕዝብ ተዋርዶ መሪው ክብር አያገኝም፤ መሪው ተዋርዶ ሕዝብ ክብር አያገኝም፤ የአንዱ ውርደት ለሌላው ክብር ሊሆን አይችልም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስብሰባው ላይ የተጋበዘው ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን አህጉርንም ወክሎ ነበር፤ በዚህ ሁኔታ ክብር ቢያገኝ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን በሙሉም ያስከብር ነበር፤ ስለዚህም የዜና ማሰራጫዎች ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲያወድሱ ኢትዮጵያም አፍሪካም አብረው ይወደሱ ነበር፤ አሁን ግን አንገቱን ስለደፋው ሰው ሲናገሩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እያሉ ነው፤ ያኔ እኛም አንገታችንን ባንደፋም ወደግብዣው ቋጥረነው የገባነው ትንሽ ክብር ይደፋብንና ውርደቱ ይሰማናል፤ የሚገዙትን ሕዝብ ሳያከብሩ ማስክበር ያስቸግራል፤ የሚገዙትን ሕዝብ ሳያከብሩ መከበርም ያስቸግራል፤ መሪና ሕዝብ ክብርንና ውርደትን ይወራረሳሉ።
በሃያ ዓመት የመሪነት ቦታ ተቀምጦ አንገቱን ቀና አድርጎ በኩራት የሚወረወርበትን ጉድፍ ሁሉ ለመቀበል የሚችልበትን፣ የሚናገርበት ብቻ ሳይሆን አንገቱን ሳይደፋ ለማዳመጥ የሚችልበትን መድረክ ሳያዘጋጅ በመቅረቱ የደረሰበት ውጤት በዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ አንገት መድፋት ነው።
በስንቱ ነገር ነው አንገታችንን የምንደፋው? በደሀነትና በችጋር፣ በመረጃ ማነቆ፣ በቴሌቪዥን እኛ የምንፈልገውንና የምንመርጠውን ለማየት አንችልም፤ በቴሌቪዥን ፕሮግራም እንኳ አጥፍቶ መጥፋት ሊባል ወደሚችል እልህ ውስጥ ገብተን ከዓለም ጋር ብቻ ሳይሆን ከእውቀት ጥበብ (ከቴክኖሎጂ) ጋር የምንታገል ይመስላል፤ ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ እየተባለ መራራ ኮሶ የሚጋቱበት ዘመን አክትሞአል፤ ዓለም በሙሉ ጎረቤት ሆኖአል፤ በአንዱ አገር ውስጥ የሚሆነው ውቅያኖስንና አህጉሮችን አቋርጦ ይሰማል፤ ይታወቃል፤ ከጎረቤቶቻችን ከአፍሪካ አገሮች ጋር በመረጃ ልውውጥ በጣም ዝቅተኛ ነን፤ በቴሌቪዥን ብቻ ሳይሆን በኢንተርኔት አገልግሎት ችግር ፍዳችንን እየበላን ነው።
ለዚህ ነው አንገታችንን የምንደፋው፤ አንገታችንን ስንደፋ ክብራችን ይፈስብንና ገበናችን ይጋለጣል፤ መከባበሩ የሚበጀው ለዚህ ነው።


ጥሩነሽ ዲባባ በኦሎምፒክ የሚያሳትፋትን ሰአት ከአስደናቂ ብቃት ጋር አስመዘገበች


ጥሩነሽ ዲባባ በኦሎምፒክ የሚያሳትፋትን ሰአት ከአስደናቂ ብቃት ጋር አስመዘገበች (ከፍሰሃ ተገኝ)
SHARE THIS
     
TAGS

(ከፍሰሃ ተገኝ –የቀድሞው የኤፍኤም አዲስ ስፖርት አዘጋጅ) ድንቋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አሜሪካ ዩጂን ውስጥ በተካሄደው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር አንደኛ በመውጣት
አሸንፋ በለንደን ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን በርቀቱ የሚወክሉት ሴት አትሌቶች መሀል አንዷ መሆኗን አረጋግጣለች። 5 ሺህ ሜትር ያህል ርቀት እንደሮጠች መሪነቱን የያዘችው ጥሩነሽ ርቀቱን ሮጣ ለመጨረስ 30 ደቂቃ ከ24.39 ሰከንድ የሆነ ጊዜ የወሰደባት ሲሆን ሰአቱም የአመቱ ፈጣን ሆኖ ተመዝግቧል። ኬኒያዊቷ ፍሎረንስ ኪፕላጋት ሁለተኛ ስትወጣ፤ ሌላዋ ኢትዮጵያዊት በላይነሽ ኦልጅራ የራሷን ምርጥ ሰአት በማስመዝገብና የአለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የኦሎምፒክ መሳተፊያ አንደኛ ደረጃ ሰአት በሚል ካስቀመጠው 31 ደቂቃ ከ45.00 ሰከንድ በፈጠነ 30 ደቂቃ ከ26.70
ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጥናቀቅ ሶስተኛ ሆና ጨርሳለች። ሌሎቹ ኢትዮጵያዊያን ወርቅነሽ ኪዳኔ (30:50.16) እና አበሩ ከበደ (31፡09.28) ከአንደኛ ደረጃው የማለፊያ ሰአት የፈጠነ ሚኒማ በማስመዝገብ አራተኛና አምስተኛ ደረጃን አግኝተው የጨረሱ ሲሆን በኦሎምፒክ አንድ ሀገር በአንድ የውድድር አይነት ቢበዛ ሶስት አትሌቶችን ብቻ የምታሳትፍ በመሆኑና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ይሄንን የዩጂን ውድድር በለንደን ኦሎምፒክ የሚሳተፉ ሶስት ቋሚ አትሌቶችን ለመምረጥ የማጣሪያ ውድድር አድርጎ እንደሚጠቀምበት በማሳወቁ አንጋፋዋ አትሌት ወርቅነሽ ኪዳኔ ቀሪውን ሶስተኛ ቦታ በመያዝ ወደለንደን ትሄዳለች ተብሎ ይጠበቃል። ባለድሏ ጥሩነሽ ዲባባ ከውድድሩ በኋላ በሰጠችው አስተያየት “ውድድሩ ጥሩ ነበር፤ ብዙም አላስቸገረኝም። ነገር ግን ሩጫው ላይ እንዳለሁ መጠነኛ የሆነ የሆድ ህመም ተሰምቶኝ ነበር። ከምንም በላይ ግን በኦሎምፒክ የምሳተፍ መሆኔን በማረጋገጤ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ” ብላለች። በ10 ሺህ እና 5 ሺህ ሜትር ርቀቶች የኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ጥሩነሽ ከቤጂንግ ኦሎምፒክ በኋላ በአብዛኛው በጉዳት ምክንያት ከውድድሮች ርቃ የነበረ ቢሆንም፤ በተሳተፈችባቸው ውድድሮች ግን አስደናቂ ብቃትን በማሳየት ማሸነፏ የተለመደ ክስተት ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና የኬኒያ አትሌትክስ ፌዴሬሽንም የዩጂኑን ውድድር በወንዶች 10 ሺህ ሜትር ሀገሪቷን ለንደን ላይ የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥ እንደማጣሪያ ውድድር የተጠቀመበት ሲሆን ዊልሰን ኪፕሮፕ (27፡01.98)፣ ሞሰስ ማሳይ (27፡02.25) እና ቢታን ካሮኪ (27፡05.50) ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ በማግኘት በአሸናፊነት አጠናቀዋል።

ኪፕሮፕ ከውድድሩ በኋላ በሰጠው አስተያየት “ሩጫው በጣም አስቸጋሪ የነበረ ቢሆንም በደንብ እራሴን አዘጋጅቼ ነበር። እናም በውጤቱ እጅግ በጣም ነው የተደሰትኩት። የወቅቱ የአለም የግማሽ ማራቶን ሻምፒዮን ከመሆኔ በተጨማሪ ሀገሬ ኬኒያን በኦሎምፒክ ለመወከል መቻሌ በህይወቴ የፈጸምኩት ልዩ ተግባር ነው” ብሏል።
                         ጥሩነሽ ዲባባ በኦሎምፒክ የሚያሳትፋትን ሰአት ከአስደናቂ ብቃት ጋር አስመዘገበች (ከፍሰሃ ተገኝ)            www.maledatimes.com