"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 15 September 2012

IMF Urges Ethiopa to slow nile dam project to protect ecomomy


By William Davison – Sep 14, 2012

Ethiopia should slow the construction of Africa’s largest hydropower plant to avoid the dam and other projects starving the rest of the economy of funds, the International Monetary Fund said.

The government began work on the Grand Ethiopian Renaissance Dam, situated on the Blue Nile River near the Sudanese border, in April last year. The 80 billion-birr ($4.5 billion) project that will generate 6,000 megawatts, partly for export to the region, is scheduled to be completed in 2018.

“I think there’s a need to rethink some of those projects a little bit to make sure that they don’t absorb all domestic financing just for that project,” IMF country representative Jan Mikkelsen told reporters yesterday. “If you suck in all domestic financing to just a few projects that money will be used for this and not for normal trade and normal business.”

የሊቀመንበርነት ምርጫው ተጠናቋል አቶ ሃይለማርያም የግንባሩ መሪ ሆኑ




በትላንትናው እለት ተቋርጦ ለሁለተኛ ቀን የተላለፈው የኢህአዴግ የሊቀመንበርነት ምርጫ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል በዚህ ውሎው ስብሰባውን ያካሄደው የኢህአዴግ ሊቀመንበርን የመረጠ ሲሆን ሃይለማርያም ደሳለኝ የሊቀመንበርነቱን ቦታ ተክተው መያዛቸውን የኢህአዴግ የስብሰባ ካውንስል ባደረገው መግለጫ መሰረት የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ ያደረሰን ሪፖርት ያስረዳል።አዲሱ ሊቀመንበር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በአሁኑ ሰአት የጠ/ሚንስትሩን ቦታ ቢቆናጠጡ የተሻለ ነገር ይመጣል ብለው የሚያስቡት የኢትዮጵያ ህዝቦች አይንቸውን ወደ እሳቸው ማዞራቸው ይብልጡኑ ስልጣኑን ሊያሳጣቸው እንደሚችልም አንዳንድ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ይገልጻሉ ምክንያቱንም ሲያስረዱ ወያኔ /ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ህዝብ ተወዳጅ የሆነ ሰው ለድርጅታቸው እንደማያስፈልግ ያስረዳሉ ይሄንንም ጠንቅቀው ያውቁታል ።ለዚህም እንደምሳሌ የምንገልጽላችሁ አቶ አርከበ እቁባይ የከተማችን ከንቲባ በነበሩበት ወቅት በሰሩት ስራ ሲወደሱ እና ሲመሰገኑ መንግስት አንስቶ ወደ ታች አውርዶ ነው የወረወራቸው ስለዚህ አሁንም መጠበቅ አይገባንም ሲሉ አክለዋል። በም/ሊቀመነበርነት የተመረጡት አቶ ደመቀ መኮንን ሲሆኑ በአሁን ሰአት የትምህርት ሚንስትር በመሆን በማገልገል ላይ የሚገኙ ናቸው ።እንደማለዳ ታይምስ ዘጋቢ ከሆነ ወያኔ ኢህአዴግ 180 ካውንስል ያሉት አባላቶቹን በማሰባሰብ ስብሰባውን በትላንትናው እለት ቢጀምርም በአቋም እና በሃሳብ ልዩነት በትላንትናው እለት መበተኑን መዘገባችን ይታወሳል ።ሆኖም ተጀምሮ የነበረውን አጀንዳው የማጽደቁ እቅድ ይቀጥላል በማለት የጀመሩት አባላቶቹ እና የስብሰባው መሪዎች  የድርጅቱን ወስጣዊ እና ውጫዊ ገጽታ ጠንቅቀን ማንጥናት እና በአዲስ መልክ ማዋቀር ግዴታችን ነው ይህም በውስጣችን ለሚገኘው አለመተማመን እና መፍረክረክ ጠቀሜታ ይኖረዋል ሲሉ የድርጅቱ የስብሰባ ካውንስል መሪ የገለጹ መሆኑን የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ አክሎ  ምርጫችን የተሳካ እንዲሆን በቀድሞው የአመራር ህገ ደንብ መሰረት ሁሉንም የመረጥናቸው አባሎቻችን ቃለመሃላቸውን በመፈጸም ወደየስራ ገበታቸው እንዲገቡልን እንፈልጋለን በማለት ግልጦአል ።በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር በኩል ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ስራዎች ስላሉብን እሱን የመጨረስ ግዴታም ሃላፊነትም አለብን በማለት ማሳሰቢያውንም አክሎ ገልጧል ሲል ዘጋቢያችን ከስፍራው አትቷል።


hailemariam dessalegn

የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም!


አሲምባ ርዕሰ አንቀጽ
                                                            ጳጉሜ 3 ቀን 2004 ዓ.ም
የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም!
                                       ፯ኛው ዓመት የቀይ ሽብር ዝክረ ሰማዕታት በአሲምባ የውይይት መድረክ
                                      አሲምባዎች ለምንደር ነው በየዓመቱ የቀይ ሽብርን የሰማዕታት ቀን የምንዘክረው?
ለኢትዮጵያ ህዝብና ለሀገራቸው ባላቸው ፍቅር፤ የጥቂቶች መንደላቀቂያ መንግሥተ ሰማዕት 
ለብዙሃኑ ግን አሣር መቁጠሪያ እሥር ቤት የነበረችውን ኢትዮጵያ የብዙሃኑ ለማድረግ፤ ሕዝባችንን
ከዘመናት የመከራ ማቅ ለአንዴም ለሁሌም ለማላቀቅ፤ የስልጣን ሱስ ካሰከራቸው የሀገር ሀፍረቶች፤
ፋሺሽቶችና ጠባብ ብሔረተኞች ጋር ተናንቀው ሕይወታቸውን በድፍረት መስዋዕትነት ለከፈሉ፤
ሕይወታቸውን ሰጥተው ሕይወት ለሰጡን፤ የጀመሩት ዕውነተኛ የሕዝባዊ ሥርዓት ምሥረታ ትግል
ባግባቡ እንዲቋጭ፤ በአደራም የተቀበልነውና ለሌላም ትውልድ የማንለጋው ኃላፊነት እንደሆነ
በመገንዘብ፤ እኛም ከመቼውም የበለጠ ለመታገል ቃላችንን መልሰን የምናድስበት፣ ታግለው ያታገሉንን
እኒያ የቁርጥዬ ቀን የኢትዮጵያ ጀግኖች፤ ጠላቶቻቸው፤ ታሪካቸውን እንደሚደልዙት ሳይሆን ዕውነተኛ 
ታሪካቸውን በቅርብ ከሚያውቋቸው የምንሰማበት፣ እነሱንም በማሰብ፤ አደራ በላዎች አለመሆናችንን
የምናረጋግጥበትና የምናመሰግናቸው ዕለት እንዲሆን እነሆ ዛሬ ለ፯ተኛ ጊዜ የቀይ ሽብር ሰማዕታትን ቀን
በአሲምባ የውይይት መድረክ ዘክረን እንውላለን።

እኔ የምለው …እዚህ አገር ዘመናዊ ወህኒ ቤቶች የመገንባት እቅድ አለ እንዴ?



 አይገርምም… አንዱ ካድሬ ወዳጄ እኮ ነው ሹክ ያለኝ፡፡ ዘመናዊ ስላችሁ ታዲያ ፍላት ስክሪን ቲቪ ምናምን ያለው
ማለቴ አይደለም፡፡ እንደሱ ከሆነማ እንደ ኮንደሚኒየመ በዕጣ ተከፋፍለነው የወህኒ ቤት እጥረት ተፈጠረ የሚል
ዓለም አቀፍ ዘገባ መሰራጨቱ አይቀርም፡ እናላችሁ … ዘመናዊ ሲባልም “አንፃራዊ” መሆኑ ልብ ይባልልኝ፡፡
እኔን የሚገርመኝ ምን መሰላችሁ? ፈጣሪ ለእነጃፓን ማለቂያ የሌለው የቴክኖሎጂ ፈጠራና ተሰጥኦ ሲያድላቸው ለምንድነው ለእኛ ክፋት፣ መጠላለፍ፣ ጥላቻና ሃሜት ከድርሻችን በላይ ያሻረን? ቀላል ጥያቄ እንዳይመስላችሁ፡መሬት ይቅለላቸውና በምንም ጥያቄ አይበገሩም የሚባሉት ጠ/ሚኒስትራችን እንኳን አቅቷቸው ትተውታል አሉ፡፡
ወደ ቁምነገሩ ስንመጣ… አሁን ጃፓን የሰራችው አዲስ መነፅር የሚበሉትን ምግብ መመጠን እያቃታቸው ከልክ
በላይ ለሆነ ውፍረት (obesity) ለሚጋለጡ ሰዎች ሁነኛ መፍትሄ ነው ተብሏል፡ እንዴት መሰላችሁ? መነፅሩ ትንሿን ምግብ ቆልሎ የሚያሳይ ነው … ስለዚህም ተመጋቢዎቹ ገና ሲያዩት የምግብ ፍላጐታቸው ይቆለፋል፡፡ እንደድሮው
እያግበሰበሱ የስጋ ክምር መስራት ቀረ ማለት ነው፡፡ ችግር ፈቺ መሆን ማለት እንግዲህ ይሄው ነው!
ባይገርማችሁ… ስለዚህ መነፅር ገና እንደሰማሁ ነው ለአገራችን የተመኘሁት፡፡
ለእኛ የሚያስፈልገን መነፅር ግን ትንሽ ለየት ይላል፡፡ ገና በምግብ ራሳችንን ስላልቻልን ከልክ በላይ ውፍረት ለጊዜው
ችግራችን አይደለም፡፡ እኛ የሚያስፈልገን እርስ በርስ የምንተያይበት መነፅር ነው፡፡ እኛ የሚያስፈልገን ዲሞክራሲያችንን አጋንኖ የሚያሳየን መነፅር ነው፡፡ እኛ የሚያስፈልገን የፖለቲካ ምህዳሩን አገር አሳክሎ (ለጥጦ) የሚያሳየን መነፅር
ነው፡፡

የኢህአዴግ ምክርቤት ያለውጤት ተበተነ ፣ስብሰባው ነገም ይቀጥላል


ኢሃዴግ ምክርቤት በዛሬው እለት ባደረገው ስብሰባ ከአራቱ  ድርጅቶች ጋር በመሆን ስብሰባውን ያደረገ ሲሆን  በስብሰባው ላይ የተገኙት  ከደቡብ ህዝቦች (ደህዴግ)  ፣አማራ(ብአዴን) ፣አሮሞ (ኦህዴድ) ትግራይ (ህወሃት)የተውጣጡ የምክር  ቤት አባላት ስብሰባውን የመሩት ሲሆን  ሌሎችም አጋር ድርጅቶች በታዛቢነት ተገኝተዋል ::በስብሰባው መጀመሪያ ላይ በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ  ሞትን አስመልክቶ የህሊና ጸሎት በማድረግ ፣የቀድሞውን መሪያቸውን በታሳቢነት ሲያስታውሷቸው እና በጸሎታቸው ፣ሲወድሷቸው እንደነበር ፣የውስጥ ምንጮቻችን ከስፍራው ዘግበዋል።

በዛሬው እለት የተጀመረው ይኼው ስብሰባ በመላው ሃገሪቱ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ እና ጠቅላይ የአመራሩን አካል ይመርጣል ተብሎ ሲጠበቅ ሳይመርጥ በመቅረቱ ጉዳያቸውን በሌላ አጀንዳ ላይ ለማተኮር ከመቻላቸውም አንጻር የውሎአቸውን ውይይት ቅድመ ከአቶ መለስ ሞት እና እንዲሁም ድህረ አቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሃገሪቱ ላይ ስለነበረው ውስጣዊ እና ውጫዊ እንቅስቃሴ አስመልክቶ ትኩረት በመስጠት ስብሰባቸውን ጀምረዋል።በዚህም ጉዳይ ላይ መንግስት በድርጅቱ አንጻር ያለውን እንቅስቃሴ እና እየሰራ ባለው ሂደት ላይ በተለይም በሌሎች አለማትንም  ጭምር  እየተካሄደ ያለውን ሂደት መገምገማቸው የደረሰን ሪፖርት አጠናቅሯል ።እስከዛሬ ድረስ ጠቅላይ ሚንስትሩ ከስራ ገበታቸው ተሰውረው  ከጠፉም ሆነ እስከ ህልፈተ ሂወታቸውም ድረስ ከዚያም አልፎ  ስርአተ ቀብራቸው ከጠፉ ከዘጠና ቀናት በላይ  ያሳለፉ ሲሆን ፤ እስከ ዛሬ ድረስ ይህ ግምገማ ሳይካሄድ ፣አገሪቱንም የሚመራት አካል ሳይኖር እነሱ እንደፈለጋቸው በደፈናው ሲጨፍሩበት የነበረበት ይህ ድርጅት ዛሬ ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ አይነት ሩጫቸው የሚመርጡትን አካል ለማወቅም ሆነ ለመገምገም እንዳስቸገራቸው ፣የሚገልጽ ነው ከዚያም አልፎ ግራ አጋቢ የሆነ አቅጣጫ እንደ ደረሱ የሚያመላክት ነው ሲል ሪፖርተራችን ከስፍራው አትቷል ።

Freed Swedish journalists say faced mock execution in Ethiopia


STOCKHOLM (Reuters) – Two Swedish journalists pardoned by Ethiopia after spending 11 months in jail for aiding a rebel group said on Friday they had been subjected to a mock execution, and accused the country of using anti-terrorism laws to stifle journalism.
Reporter Martin Schibbye and photographer Johan Persson were arrested in July 2011 after entering the country from neighboring Somalia with fighters from the Ogaden National Liberation Front (ONLF) rebel group.

Swedish journalists Schibbye and Persson arrive at Arlanda airport in Stockholm (SCANPIX SWEDEN, SCANPIX SWEDEN / September 14, 2012)
They said they had wanted to report on the effect of the work of a Swedish oil company on the local population and political situation in Ethiopia’s Ogaden region and that the only way of entering the area was with the rebels’ help. The journalists were pardoned and released on Monday.
Schibbye said Ethiopian security officials had tried to get them to confess to being terrorists after their arrest. He said they were taken into the desert where one official pulled him out of a jeep, told him “No more Mr. Nice Guy” and ordered him to start talking.
“A soldier lifted up his weapon,” Schibbye told a news conference in Stockholm. But instead off shooting him, the soldier shot into a bush beside him, he said.
Persson said he had been taken off in another direction and thought his colleague had been killed.
The men said they had been forced to make an apology on Ethiopian television in order to secure their release. Schibbye said he had not meant what he had said.

Thursday 13 September 2012

Government uses fake video to convict Swedish journalists



Posted by admin on September 12, 201212 Comments
The regime in Ethiopia uses staged fighting as evidence to convict Swedish journalists Schibbye and Persson. The Sweden TV SVT exposed the hoax after the two journalists safely left Ethiopia after they were pardoned on the Ethiopian New Year eve.

Persson and Schibbye
SVT can now reveal that the videos that the Ethiopian government used as evidence of the arrest of the Swedish journalists is staged. Our sources even claim that the video was shot two days after Johan Persson and Martin Schibbye were arrested.
During the trial of Johan Persson and Martin Schibbye autumn 2011 showed prosecutor videos that he meant clearly proven Swedes crimes. Even then questioned a video sequence and the prosecutor was forced to admit that the sound of gunfire was applied retrospectively. But the prosecutor insisted that the films showed the arrest of one authentic way.

ድምጻዊት አቦነሽ አድነው ዘፈን አቁማ ዘማሪ መሆኗን አስታወቀች




(ዘ-ሐበሻ) “ባላገሩ” በተሰኘው አልበሟ የምናውቃት ድምጻዊት አቦነሽ አድነው ሙዚቃ ማቆሟን እና ወደ መንፈሳዊ ዘማሪነት መግባቷን ይፋ አደረገች። ድምጻዊቷ ካሁን በኋላ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት እና ቀኖና መሠረት እግዚአብሄርን አመሰግነዋለውም ብላለች።
“ይህንን ውሳኔ ለመወሰን 5 ዓመታት ያህል ፈጅቶብኛል” ያለችው ድምጻዊቷ “ማታ ማታ ዘፍኜ እቤቴ ስገባ ደስተኛ አልነበርኩም፤ የ እግዚአብሄርን ቃል ሁልጊዜ አስብ ነበር” ብላለች። ድምጻዊቷ በቤተክርስቲያን መድረክ ላይ ቆማ እንደገለጸችው ደግሞ “ማታ ማታ ስዘፍን አድሬ ጠዋት ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ባልደርስም ቢያንስ ቃሉን ሰምቼ እሄድ ነበር።” ካለች በኋላ “በአዲሱ ዓመት አሮጌው ማንነቴን ቀይሮ እዚህ እንድገኝ እግዚአብሔር ስላደረገኝ አመሰግነዋለሁ” በማለት “አበረታኝ ጌታዬ የሚለውን መዝሙር ዘምራለች።
የቀድሞዋን ድምጻዊት አቦነሽ አድነውን ምስክርነት የሚያሳየውን ቪድዮ ይመልከቱ፦
በነገራችን ላይ አቦነሽ አድነው ጁላይ መጨረሻ ላይ በኢትዮጵያን ሄሪቴጅ 2ኛ ዓመት በዓል ላይ በዋሽንግተን ዲሲ በትልቅ መድረክ የዘፈነችው የመጨረሻዋ የሙዚቃዋ መጨረሻ መድረክ ሊባል ይችላል።


ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል መለስ ዜናዊን ይተካሉ ብለን ለምን አልጠረጠርንም?



       

የቀጣዩ የጎልጉል ኦንላይን ጋዜጣ ዘገባ “ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል መለስ ዜናዊን ይተካሉ ብለን ለምን አልጠረጠርንም?” የሚለውን ጥያቄ ያነሳብዎታል። እናካፍልዎ። (ጎልጉል) ሟቹን ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊን ለመተካት የሚደረገው የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻ ኢህአዴግ እንደሚለው “በቀላል ሽግግር” የሚቋጭ እንዳልሆነ የሚጠቁሙ መረጃዎች እየወጡ ነው። መለስን በወኪሏ ወ/ሮ ሱዛን ራይስ አማካይነት በአስከሬን ሽኝቱ ወቅት ያቆለጳጰሰችው አሜሪካ የስልጣን ሽግግሩ ላይ ያላትን የማያወላዳ አቋም ትዕዛዙን ባለመቀበል ከሚመጣው መዘዝ ጋር ማስታወቋም ተሰምቷል።
የጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጮች ከኢህአዴግ ከፍተኛ ደጋፊዎችና የቅርብ ባለሃብቶች እንዳገኙት ገልጸው በላኩት መረጃ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲተኩ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን በቅድሚያ እጩነት መያዛቸውን አመልክተዋል።
መረጃ አቀባዮቻችን ደብረጽዮን ለሹመቱ የታጩበትን ምክንያት ሲያስረዱ መነሻ ያደረጉት በህወሓት ክፍፍል ወቅት የነበራቸውን ልዩ ሚና በማስታወስ ነው። በበረሃው የሽምቅ ውጊያ ወቅት የህወሓትን የሬዲዮ ማሰራጫ ጣቢያ በማቀናበር የሚታወቁት አቶ ደብረጽዮን አቶ መለስን በቅርብ እንደሚዛመዱና ለመለስ ቁልፍ ተግባራትን የሚያከናውኑ ሰው
እንደነበሩ የመረጃው ባለቤቶች በዝርዝር ተናግረዋል።
በዘመነ ህንፍሽፍሽ ህወሓት ለሁለት መሰንጠቁ ይፋ ከመሆኑ በፊት ልዩነቱ ውስጥ ውስጡን በተጋጋመበት ወቅት አቶ ደብረጽዮን ከአቶ መለስ የተቀበሉትን ልዩ ተልዕኮ ለመተግበር ያስችላቸው ዘንድ የሽሬ ምክትል አስተዳዳሪ ተደርገው ተሹመው ነበር። አፈንጋጭ የተባለውን ቡድን ከሚመሩት መካከል ዋና ኃይል አላቸው ተብለው የሚፈሩት አቶ ስዬ በትውልድ መንደራቸው ተምቤን ውስጥ ያላቸውን ሰንሰለት ለመበጣጠስና ለማምከን ልዩ ተልዕኮ ይዘው ወደ ሽሬ ያመሩት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ሃላፊነታቸውን በመወጣት ለመለስ አሸናፊነት ጉልህ ሚና መጫወታቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።

Wednesday 12 September 2012

Ana Gomes decries EU anti-human rights policy on Ethiopia at a European Parliament depat -11 September 2012

Ana Gomes decries EU anti-human rights policy on Ethiopia at a European Parliament depat -11 September 2012                                                                                                                          BRUSSELS - Ana Gomes, member of the European Parliament, censures the EU over its indifference to the appalling human rights conditions in Ethiopia. The Honorable Gomes made the remarks during an end-of-year report of the European Parliament.

Tuesday 11 September 2012

የሳውዲ የሐገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀ







ከነብዩ ሲራክ
በኢትዮጵያ ያለውን እስራትና አለመረጋጋት በጨረፍታ በመጠቆም የኢትዮጵያ ሁኔታ የተረጋጋ ባለመሆኑ የሳውዲ ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ የሳውዲ የሐገር ውስጥ ሚኒስትር ማስጠንው ከትናንት እኩለ ቀን በተንቀሳቃሽ ስልክ በተለቀቀ መልዕክት ሲሆን በዛሬው እለት ሚኒስትርር መስሪያ ቤቱ ያወጣውን ይህን ማስጠንቀቂያ በትናንትናው እለት ደርሶኝ ተመልክቸዋለሁ፡፡ ያም ቢሆን ጉዳዩን እስኪጣራ መረጃውን በአየር ላይ ከማዋል ተቆጥቤ ነበር፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዛሬው ረፋድ የሳውዲ ራዲዮ ዜና እወጃ ይህው ማስጠንቀቂያ ይፋ ሲደረግ በአለም አቀፍ ደረጃ ስርጭት ያላቸው የአልጀዚራ ፤የሸርቅ አላውሰጥና የኦካዝ ጋዜጣ በገጾቻቸው የሚኒስትር መስሪያ ቤቱን መግለጫ አዘግበውበታል፡፡ በሳውዲ መንስግት ስለተወሰደው ይህ እርምጃ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ያነጋገርኳቸው የጅዳው ቆንስል መስሪያ ቤት ሃላፊ አምባሳደር መርዋን በድሪ የጉዳዩን አሳሳቢነት በመጠቆም ጉዳዩ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደረጃ መፍትሄ የሚያሻው ስለሆነ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደረጃ ክትትል እንዲደረግበት የወጡትን ጋዜጦችና መረጃዎች ወደ ዋናው የሪያድ እንባሲ ማስተላለፋቸውን ገልጸውልኛል ፡፡ ለበለጠም መረጃ በቀጣይነት እንደሚሰጡኝ ቃል ገብተውልኛል !
ቸር ያሰማን . . .
Saudi Arabia warns against travel to Ethiopia
Embassy says seven Saudis arrested in Addis Ababa during Ramadan
Manama: Saudi Arabia has warned Saudi citizens of the risks of travel to Ethiopia, citing sporadic clashes between Muslims and the police.
Saudi citizens should avoid going to the African country until the tension is eased and the situation is settled, the interior ministry said, local Arabic daily Okaz reported on Sunday.
The travel warning was issued based on a note from the Saudi ambassador in Addis Ababa, the statement said.

ኢሕአዴግ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሕወሓት ተወካይ ጋር አብረው ሃገር እንዲመሩ ሕግ ሊያጸድቅ ነው




የአዘጋጁ ትዝብት፡ – ኢሕአዴግ አቶ መለስ ስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሙሉ ስልጣኑ በእጃቸው ባለበት ወቅት ለምክትል ጠ/ሚ/ሩ ምንም ዓይነት ስልጣን አልሰጠም ነበር። የወላይታው ተወላጅ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ጠ/ሚ/ርነቱን በሚይዙበት ወቅት ግን ምክትላቸው ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁትና አሁንም እንደምክትል ጠ/ሚ/ርነት እየሰሩ ያሉት ብርሃኔ ገብረክርስቶስን የስልጣኑ ተጋሪ እንዲሆኑ በማሰብ አዲስ ሕግ ያወጣል። አዲስ የሚወጣው ሕግ ሕወሓት ስልጣን እንዳያጣ፤ ሃይለማርያም ደሳለኝንም ነጻ ሆነው እንዳይሰሩ የሚያደርግ ነው። በዚህ ሰሞን የሚደረገው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ኃይለማርያም ደሳለኝን እና ብርሃኔ ገ/ክርስቶስን ዋና እና ምክትል አድርጎ ይመርጣል። ኃይለማርያምም በአቶ ብርሃኔ ሕወሓት ስር ወድቀው ይሰራሉ። የኢሕአዴግ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡትን ቃለ ምልልስ እንደወረደ ያንብቡት።
አዲስ አበባ፡- «በጠቅላይ ሚኒ ስትር መለስ ዜናዊ ግንባር ቀደም መሪነትና ቀያሽነት የኢትዮጵያ ህዝቦች የጀመሩትን የህዳሴ ጉዞ ለማሳካት ኢህአዴግ ከመቼውም ጊዜ በላቀ ፍጥነት ከህዝብ ጋር ይሰራል» በማለት የግንባሩ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አስታወቁ። የኢህአዴግ ሊቀመንበርንና ምክትል ሊቀመንበርን የመምረጥ ጉዳይ ማን የበለጠ መስዋዕትነት ይክፈል የሚለውን የሚያመላክት ብቻ መሆኑን ገለጹ።
የግንባሩ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳለመከቱት፤ ግንባሩና የግንባሩ ሥራ አስፈፃሚ አካላት የአቶ መለስን አደራ ስንቅ በማድረግ የሀገሪቱን ህዳሴ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆነዋል፤ ህዝቡ አቶ መለስ የተዋደቁለትን ዓላማ ለማስቀጠል ያለው መነሳሳትና ቁጭት ከፍተኛ መሆኑንም ሥራ አስፈፃሚው ተገንዝቧል። በዚህም ምክንያት «የግንባሩ ሥራ አስፈፃሚና መላው የኢህአዴግ አባላት የኢትዮጵያ የህዳሴ ጉዞ በስኬትና በስፋት እንዲቀጥል ከፍተኛ ርብርብ ያደርጋሉ» ብለዋል።
ህዝቡ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስና የድርጅታቸውን ዓላማዎች ተገንዝቦ በቁጭት ትግላቸውን ለማሳካት ዝግጁነቱን ሲያረጋግጥ ምንም ጉድለት የለባችሁም ከሚል ስሜት ፀድቶ አለመሆኑን ኢህአዴግ እንደሚገነዘብ ጠቁመው፤ በተለይ ከመልካም አስተዳደር፥ ከአፈፃፀም ቅልጥፍናና ጥራት ጋር የተያያዙ ችግሮችን እንዲሁም የተጀመሩ የፍትህ ሥርዓት ማሻሻያና ሲቪል ሰርቪስ ማሻሻል ተግባሮችን ከተጀመረው ፍጥነት በላይ ለመፍታት ግንባሩ እንደሚረባረብ አስረድተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩንና የሀገሪቱን ራዕይ ለማሳካት ግንባሩ ሙሉ ዝግጅት፥ አቅምና ቁርጠኝነት እንዳለውም ገልጸዋል።
«ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህይወት ዘመናቸው ያለ መታከት ብዙ በመስራት በርካታ ተተኪዎችን አፍርተዋል» ያሉት አቶ ሬድዋን «በኢህአዴግ መበላላት፥ መጎሻሸም፥ መገፋፋት የለም፤ ተተኪን የመምረጡ ጉዳይ ማን ይበልጥ ያስተባብር በሚለው ላይ ያነጣጠረ ነው» ብለዋል። ግንባሩ በስልጠናና ተግባር ልምምድ በታገዙ የእውቀት ሽግግሮች የተገነቡ መሰረታዊ የድርጅቱን እሴቶች የማስቀጠል አቅም እንዳለው ተናግረዋል።
ለግንባሩ የመተካካት ጉዳይ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነትን የመጫንና ማን አስተባብሮ ይሂድ የሚለውን ከመግለፅ ውጪ በድርጅቱ ባህል ስልጣን ምቾትና ድሎት አይደለም » በማለት በአፅንኦት ገልጸዋል።
የድርጅቱንና የኢትዮጵያ ህዝቦችን ጥቅም ከማስጠበቅ አኳያ ግንባሩ የሚጠመዘዝ እጅ እንደሌለው ጠቁመው፤ በማንም ኃይል የማደናቀፍ ተግባር የህዝቡን ፍላጎትና ዓላማ ከማሳካት ወደ ኋላ እንደማይል አስረድተዋል።




Monday 10 September 2012

በአቶ መለስ ሞት ተጋርዶ የነበረው የኃይልዬ ታደሰ አዲሱ አልበም አድማጭ እያገኘ ነው


በአቶ መለስ ሞት ተጋርዶ የነበረው የኃይልዬ ታደሰ አዲሱ አልበም አድማጭ እያገኘ ነው


inShare
Share
(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው ጠ/ሚ/ር አቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት በተነገረበት እለት አዲስ የሙዚቃ አልበሙን አውጥቶ የነበረው ድምጻዊው ኃይልዬ ታደሰ የአቶ መለስን ሞት ተከትሎ የትኛውም ሙዚቃ ቤት ሙዚቃ እንዳይከፍት፣ የናይት ክለቦችም ሙዚቃ ከፈታችሁ ተበለው በመታሸጋቸው፣ እንዲሁም የመንግስት ራድዮና ቴሌቭዥኖች የሃዘን ዋሽንት ሙዚቃና ክላሲካል ዘፈኖችን በማስደመጣቸው አልበሙን ገዝቶ የሚያደምጥ ጠፍቶ ነበር። አልበሙም ከሽያጭ በሃዘኑ ምክንያት ተጋርዶ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ወደ አድማጭ ጆሮ መግባት መጀመሩን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከኢትዮጵያ ዘግበዋል።
ቴዲ አፍሮን ጨምሮ ታላላቅ የሃገራችን ገጣሚያን እና የዜማ ባለሙያዎች የተካፈሉበት የሃይልዬ አዲሱ አልበም የአዲሱን ዓመት በማስመልከት በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እንዳገኘለትም ዘጋቢዎቻችን ጨምረው ገልጸዋል። በተለያዩ ቦታዎችም አልበሙ እየተደመጠለት ይገኛል። ከአዲሱ አልበም ውስጥ አንዱን ዘፈን እንጋብዛችሁ።
ይህ የኃይልዬ አልበም 3ኛው ነው።
 s


አባይ ፀሃዬ የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ እንዲይዙ አሻጥር እየተሰራ ነው ።


አባይ ፀሃዬ የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ እንዲይዙ አሻጥር እየተሰራ ነው ።



የህወሃት ክፍፍል እየተጠናከረ በመጣበት በአሁኑ ሰአት የቀድሞውን ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ከፍተኛውን  ቦታ ለመቆናጠጥ የሚያስችላቸውን  የእዝ ቦታዎች ለመያዝ የህወሃት የበላይ አካሎች አሁንም በከፍተኛ ትግል ላይ ሲሆኑ ፣የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በጠ/ይ ሚንስትርነታቸው የመቀመጥ ጉዳይ በሰፊው አስጊ ነው ።በአሁን ሰአት ከፍተኛ አሻጥር እየተሰራ ያለው አቶ አባይ ጸሃዬን በማምጣት የህወሃት ሊቀመንበር ለማድረግ ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ሲሆን ፣ከፊሎች ደግሞ ይህ እንዳይሆን ትግላቸውን አጠናክረዋል።

በተለይም በአሁን ሰአት የሹም ሽር እየተደረገ ያለው በትግራይ ተወላጆች እና በኤርትራ ተወላጆች ላይ የበላይ ተቆጣጣሪነት ሲሆን ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ ስጋት ላይ እንወድቃለን ብሎ ለእራሱ ሲያለቅስ የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ሳይደርቅ የሚፈጸም ይመስላል ፣ይህንንም ስንል እርስ በራሳቸው ግጭታቸውን አባብሰውት ወደ ግድያ ያመራሉ ተብሎ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ሲሆኑ አራት የህወሃት አባሎች ከሌሎች አምስት  የጦር አዛዦች ጋር ለሚቀጥለው መስከረም አምስት በዚህ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ሚስጥራዊ ስብሰባ ለማካሄድ  ዝግጅታቸውን ማጠናከራቸውን ከውስጣዊ ምንጮች ያገኘነው ዘገባ ሲያመለክት አምስቱም የጦር አዛዦች በተለያዩ የሜካናይዝድ ክፍለጦር በአዛዥነት የሚያገለግሉ የትግራይ ተወላጆች ሲሆኑ በተጠንቀቅ ትእዛዛቸውን ለመፈጸም ያመቻቸው ዘንድ የሚረዳ ስልት የህወሃት አባሎች ሰራዊቱን ከአጠገባቸው ለማቆም ትግል ላይ ናቸው።

በተለይም ከእነአቦይ ሰብሃት በኩል ለመጣው ውጥረት እና እንዲሁም በእነ ጀነራል ሳሞራ በኩል ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው የስልጣን ክፍፍል ከእነ አቶ በረከት እና አዜብ መስፍን በኩል ላለው ልዩ ፍራቻ የሃገሪቱን ውጥረት አሁንም ይበልጥ ያባብሰዋል።በተለይም ከህወሃት አባላት ውጭ ሌላ ሰው ቁንጮ ሆኖ መቀመጥ የለበትም የሚሉት የእነ አዜብ መስፍን እና የአክራሪው ስብሃት ነጋ ቡድን ሁለቱም ፍጥጫቸው በተለያየ መልኩ ሊሄድ ይችላል ነገር ግን ግጭቱ ወደ አንድ አቅጣጫ ያመራቸዋል ሲሉ ፤የግጭቱ መንስዔ ግን የቦታ ይገባኛል እና የሚፈልጉትን ሰው በሚፈልጉት ቦታ የማስቀመጥ ጉዳይ መሆኑ ፣ይበልጥ አሳሳቢ እና ግራ የሚያጋባቸው ሆኖአል ።

በሌላ በኩል ደግሞ የአቶ በረከት የኤርትራ ተወላጆችን ወደ ስልጣን ማምጣት እና እሳቸው በሚያሽከረክሩት አዙሪት ውስጥ ለመጣድ የሚያደርጉት ጥረት ስኬቱ ጎልቶ የሚታይ ባለመሆኑ በኦህዴድ እና ብአዴን ውስጥ ላሉት አመራሮች ፍራቻን ቢጭርባቸውም እስካሁን ድጋፋቸውን ከመስጠት ተቆጥበዋል ፣ሆኖም ግን የኤርትራ ተወላጆች የከበቧት የስልጣን ቦታ ለኤርትርያን ተወላጆች እና እንዲሁም አቶኦ በረከት የበላይ ሆኖ እንዲመራ የሚፈልጉ እንደሌሉ በሁሉም ክልል መንግስታቶች ፍላጎት እንደሌለ እያሳዩ ይገኛሉ ፣ሆኖም ግን ውስጣዊ ፍራቻቸው አይሎ ከወጣ ግጭቱን ሊያሰፋው ይችላል ፣ለዚያም ይመስላል አቶ በረከት ስምኦን  በቀድሞው ጠ/ሚንስትር የተተኩትን ጠ/ሚንስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ቃለ መሃላቸውን ፈጽመው ስራቸውን እንዳይጀምሩ አድርገው ያቆዩአቸው ፡ይርፍላጎታቸው ስኬት ካልተሟላ እንቅልፍ አይተኙም የሚለው የማለዳ ታይምስ ሚስጥራዊ መረጃ ምንጭ ።  የጤና ሚንስትር የሆኑትን ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በጠቅላይ ሚንስትርነት ተሾመዋል  የሚለው ጭምጭምታ የውሸት ሲሆን በአሁን ሰአት ግን ግብግቡን እሳቸውም የቦታው ሽሚያ ላይ ተያይዘውታል ሲል ዘግቦአል።