"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 19 July 2012

A new breed of leaders shall come to receive the baton: Bereket Simon


A new breed of leaders shall come to receive the baton: Bereket Simon
Posted by admin on July 19, 20120 Comment
By William Davison
(Bloomberg) — Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi is taking a break to recover from an unspecified and recent illness and will return to duty once he is well, Communications Minister Bereket Simon said. “Given his enormous and herculean task he’s been shouldering for many decades, exhaustion is visible,” Bereket said. “That’s why EPRDF has been saying a new breed of leaders shall come so that they should receive the baton.”
The illness is a recent development and doctors recommended an extended rest from official duties to speed recovery, he said.
Meles has said that he will step down at the end of his term in 2015, and Bereket said “that’s what we’re expecting and that’s what we’re going to pursue in terms of the succession.” Under Meles, Ethiopia’s government has been a U.S. ally in the fight against insurgencies in the Horn of Africa, especially in Somalia, where the military helped remove an Islamist group.

አንድ ብስጭት፤ ኢቲቪ ሀይማኖቱ ምንድነው!?


አንድ ብስጭት፤ ኢቲቪ ሀይማኖቱ ምንድነው!?


እስቲ ቆይ ወደ ርዕሰ ጉዳያችን ከማምራታችን በፊት አንድ ዋዛ ብጤ እናምጣ አሁን በቅርቡ አንድ ወዳጄ አንድ ፈታኝ ጥያቄ ጠይቆኝ ነበር። ምን አለኝ መሰልዎ “አቶ መለስ እና ኢቲቪ ተጣልተዋል እንዴ!?” አለኝ ሲቀጥልም፤ “ያኔ ጋሽ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ገና ትንሽ ሲወራባቸው “ፕሬዘዳንቱ በህክምና ላይ ናቸው አትደናገጡ!” ብሎ የነገረን ቴሌቪዥናችን ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጊዜ ዝም ማለቱ ምን ቢያስቀይሙት ነው!?”  ብሎኛል።
የምር ግን ገቡ የለ ወጡ የለ ሀገር ሁሉ በርሳቸው ጉዳይ ሲጨነቅ ኢቲቪ ፀጥ ማለቱ የምርም ተጣልተው ይሆን እንዴ…? ያሰኛል። ስለ ኮብልስቶን መቀበር እና መቀጥቀጥ ደጋግሞ የሚነግረን ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ህመም ሲቀጠቅጣቸው እና “ቀብራቸው ደረሰ” እያለ ሀገሩ ሲያሟርትባቸው እርሳቸውን ከኮብል ስቶን አሳንሶ አንዳችም ነገር ትንፍሽ አለማለቱ በእውነት የታሪክ ተወቃሽ ያደርገዋል።
የእውነት ግን ወዳደጄ  የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ነገር ስንቱ ተወርቶ ስንቱ ቀርቶ… አይነት ነገር ነው። አሁን መቼለታ የኮምቦልቻ አካባቢ ሙስሊም ነዋሪዎች በአዲሳባ የተቀሰቀሰውን የሙስሊሙን ተቃውሞ አወገዙ ብለው በአወልያ ላለፉት ስድስት ወራት ፍፁም ሰላማዊ ተቃውሞ እያሰሙ የነበሩ ሙስሊሞችን የሚቃወሙ ሰዎች ቃለ ምልልስ አድርገውላቸው ነበር።

አቦይ ስብሐት፤ መለስ ሆስፒታል መሆናቸውን፣ ቢሞቱም ችግር እንደሌለው ተናገሩ!





አቦይ ስብሐት ትላንት ከአሜሪካ ድምፅ ራዲዬ ጋር የአቶ መለስን ጤንነት አስመልክቶ ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር። “መለስ አውሮፓ የሆነው ሀገር በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ተኝተዋል የት ሀገር የት ሆስፒታል እንደሆነ ግን ለግዜው አይታወቅም” አሉን። ው….ይ እኛ ደግሞ ድነው ወይም ተስፋ ቆርጠው የተመለሱ መስሎን እንጂ አውሮፓ እንደሄዱማ እናውቃለን። አቦይ ካልሰሙ እንንገርዎ ቤልጄም ናቸው! ምስኪን መለስ ወዳጆችዎ እንኳ የት እንዳሉ አያውቁም…! ምን ቢበድሏቸው ነው!!!? ብለን ቃል አጋኖን አብዝተን እናዝናለን።
አቶ ስብሐት ነጋ በቀጣይም ሲጠየቁ “ህመማቸው ለምን ይፋ አልተደረገም? በመንግስት ብዙሃን መገናኛ እንዴት አልተነገረም? ህዝቡ ይህንን የማወቅ መብት የለውም ወይ?” ተብለው ነበር። አቦይስ ምን አሉ…? “እኔ እንደሚመስለኝ ቶሎ ድኜ እመለሳለሁ ብሎ ነው እንጂ ህዝቡ የማወቅ መብት አለው!” ብለዋል። ጎሽ አቦይ እንዲህ ነው እንጂ ይህንን ንግግር መንፈስ ቅዱስ እንዳናገርዎት እቆጥረዋለሁ። እኔ የምልዎ… እርሱማ ህመምተኛ ሁሌም ጉጉ ነው! ነገ ድናለሁ ብሎ ተስፋ ማድረጉ አይቀርም። የገረመኝ ግን አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ይሄንን ዜና ለማውጣት አሁንም አቶ መለስ ናቸው የሚያዙት። በአልጋ ላይ ሆነው የዜና ተቋማቱን ሳይቀር የሚያዙ ከሆነ ነገ ህይወታቸው ሲያልፍ ደግሞ ይሄንን ነገር የእርሳቸው መንፈስ ስላልፈቀደ አልተደረገም እንባል ይሆን…!?
አቶ ስብሐት “መለስ ኖረም አልኖረም ኢህአዴግ ኢህአዴግ ነው ይኖራል ምንም የስራ ክፍተት አይፈጠርም” ሲሉ ተናግረዋል።
ለነገሩ ይሄ ንግግራቸው አቶ መለስ ቢሞቱም ይሙቱ የራሳቸው ጉዳይ… የማለት ያኽል መሆን አለበት እንጂ ከላይ እንዳየነው የመለስ መታመም ዜና እንኳን ያልተሰራበት ምክንያት መለስ በቅርቡ እድናለሁ ብሎ ስላሰበ ነው ብለውናል። በዚህም እነ ኢቲቪንም ሆነ እነ አዲስ ዘመንን አሁን እንኳ በአልጋ ላይ ሆነው መለስ እያዘዙ እንደሆነ ያለ እርሳቸው መልካም ፈቃድ ዜና እንኳ የማይሰራ መሆኑን መረዳት ችለናል። (እንደውም ይሄኛው መረዳት የግንዛቤ ሳይሆን የመርዶው ነው…! በእውነት ኢዜአ እና ዋልታ እንኳ ሳኢቀሩ መለስ ይሁን ካላሉ ዜና የማይሰሩ ከሆነ በእውነት መርዶ ነው!)
በነገራችን ላይ አቦይ ስብሐት መለስን መተንኮስ ከጀመሩ ቆይተዋል። አንዳንድ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ያላቸውን ቅያሜ ብዙ ጊዜ የሚወጡት የመለስን ንግግር እና ድርጊት በማጣጣል እየሆነ መጥቷል።
የማስታውሳቸውን አንድ ሁለቱን እንኳ ብንጠቅሳቸው ከዚህ በፊት መለስ ደጋግመው የሚነግሩንን የአውራ ፓርቲ አስፈላጊነት እና የኢህአዴግን አውራነት በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ አቦይ አጣጥለዋል። “እኛ የታገልነው ለዲሞክራሲ እና ለመድብለ ፓርቲ ነው። አውራ ፓርቲ የሚባለውን ነገር እኔ አላውቅም!” ብለው ተናግረው ነበር። እኛም እሰይ የኔ አንበሳ ብለን አድንቀናቸዋል።
በቅርቡ ደግሞ በየ ጎዳናው እና በየ መስሪያ ቤቱ በትልልቅ ወጪ የሚሰራ (እና አንዳዴም የሚሰረቅ ብዬ ልጨምር እንዴ? መቼ እለት ነው… አዋሬ አካባቢ በ35 ሺህ ብር የተሰራ መለስ አባይን ሲደፍሩ የሚያሳይ ቢል ቦርድ ተሰርቆ የለ…? )  እና “መለስ ዜናዊ አባይን የደፈረ መሪ” የሚል ቢል ቦርድ እነ ፖስተር ስራ አስመልክቶ ሲጠየቁ “እንደኔ እምነት አባይን እንኳን መለስ ዜናዊ እና ኢህአዴግም ደፍሮታል ብዬ አላስብም! እንዲህ አይነት የግለሰብ ገፅታ ግንባታ ከድርጅታችን አካሄድ ውጪ ነው” ብለው ተናግረው ነበር። ይሄንን እንኳ ሲናገሩ መለስ በእግዜር እጅ ተይዘው ነበር። ነገር ግን ከዚህ በፊት የተናገሩትን ስናስታውስ እውነትም ተንታኞቻችን እንደሚሉት አቦይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ እንዲህ የሚጨክኑባቸው ከእርሳቸው ጋር እንኳ ፀብ ባይኖራቸው ከወይዘሮ አዜብ ጋር በላው ቁርሾ የተነሳ ሊሆን እንደሚችል መገመት ቀላል ነው።

በሀገራችን ባሀል መሰረት አንድ ሰው የማይተርፍ መሆኑ ሲረጋገጥ “ለማንኛውም ቤቱን አፀዳዱ የሚሆነው አይታወቅም” የሚባል ንግግር አለ።

እንደኔ ግምት ከሆነ የአቶ መለስ መሞት ብዙ ነገር ነው። አቦይ እንዳሉት “መለስ ቢሞትም ችግር የለም” ለማለት የሚያስችል ቁርሾ የለኝም። መለስ ቢሞቱ ችግር አለው። ክፍተት ይፈጠራል። ኢህአዴግ ያለ እርሳቸው የሸዋ ዳቦ ነው። (በነገራችን ላይ ሸዋ ዳቦ አንዷ ብር ከአርባ መግባቷን ነገሬዎታለሁ አይደል። ታድያ ያ ሁሉ ዋጋ የወጣባት ዳቦ እርሾ ንፍት አድርጓት እንጂ ሲነኳት ፍርክስክስ ነው የምትለው… “አንድ ለከንፈር አንድ ላፈር” ሲሏትም ሰምቻለሁ። ፍርክስክስ ማለቷን ያዩ የተናገሩት ነው።
ለነገሩ ብዙዎች ይሄንን ድሮም እናውቀዋለን። እኔ በበኩሌ ገና እምዬ ኢህአዴግ ሲባል ከ አርማው ቀድሞ በአዕምሮዬ የሚመጣው የአቶ መለስ ስዕል ነው። ስለዚህ አቶ መለስ ብሎላቸው ከሞቱ ኢህአዴግ ሲባል በአዕምሮዬ የሚመጣው ባዶ ቤት ይሆናል ማለት ነው…!!! ውይ አረ አያድርገው ሌላው ቢቀር ለእኒያ ወ/ሮ ሲባል ትንሽ ይቆዩላቸው…! እንኳንስ ጥለዋቸው ሞተው ይቅርና እንዲሁም…
እኔ የምለው የአቶ ጁነዲን ሳዶ ባለቤት በቁጥጥር ስር ዋሉ የተባለውን ዜና እንዴት አዩት? ወዳጃችን አርአያ በፌስ ቡክ የሰጠው አስተያየት በጣም አዝናንታኛለች “ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ እንዲሉ አበው አሁንም ባለቤቱን ካልናቁ ሚስቱን አይነቀንቁ!” ነው ነገሩ ብሏል።
እና ታድያ ወ/ሮ አዜብም ባለቤታቸው አንድ ነገር ከሆኑ የሚፈጠረባቸው ነገር ቀላል አይደለም። ለርሳቸው ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የአቶ መለስ ፍፃሜ የሆነ ነገር ይዞ የሚመጣ ይመስላል።
እናም ለማንኛውም የሚሆነው አይታወቅምና ቤቱን አፀዳዱ! ይሄ መልዕክት የአቶ መለስ ነገር ለሚያሳስበው ሁሉ ነው። እደግመዋለሁ፤ የሚሆነው አይታወቅምና ቤቱን አፀዳዱ!

Wednesday 18 July 2012

Meles Zenawi still ‘in hospital’: press conference scheduled for today is postponed


Meles Zenawi still ‘in hospital’: press conference scheduled for today is postponed
Posted by admin on July 18, 20125 Comments
Ethiopia’s government has denied Prime Minister Meles Zenawi is critically ill but says he has been in hospital.
(BBC) – “He is not in a critical state. He is in good condition,” spokesman Bereket Simon told the AFP news agency.
A spokesperson for the Ethiopian embassy in London told the BBC the 57 year old was in a stable condition after hospital treatment.

Saint-Luc University Hospital, Brussels

Speculation about his health began when he missed last weekend’s African Union summit in Addis Ababa.
There were reports that Mr Meles was in hospital in Belgium, suffering from a stomach complaint.
The Ethiopian embassy spokesperson in London said the prime minister had been visited by high-level officials, but did not say where he was being treated.
Diplomatic sources in Brussels told AFP that the Ethiopian leader was in a hospital in the Belgian capital.
“He is in a critical state, his life is in danger,” the agency was told by a diplomat who asked not to be named.
An Ethiopian government press conference about the rumours scheduled for Wednesday morning has been postponed until later this week.
Correspondents say it is believed Mr Meles’s last public appearance was at the G20 talks in Mexico last month.
Mr Meles took power as the leader of a rebel movement which ousted the communist government of Mengistu Haile Mariam in 1991.
He has won several elections since then, but his political opponents have accused him of using repression to retain power

CIA Takes Over As Ethiopian Regime Crumbles: Analyst


US Secretary of State Hillary Clinton shakes hands with Ethiopia’s Prime Minister Meles Zenawi. (file photo)
Hated in his ethnic homeland of Tigray, once his power base, and hated by the Amhara elite, the ethnic minority who previously ruled Ethiopia, Meles has ceded de facto control of his ministries to technocrats from the CIA and US State Department.”
independent journalist Thomas C. Mountain

Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi is turning more and more to the CIA for making his government’s critical decisions as the foundation of his regime crumbles, a political analyst says.
In an article published on Tuesday, independent journalist Thomas C. Mountain said that the isolation surrounding Meles Zenawi grows almost by the day as he faces “more insurgencies, an ongoing economic crisis and calls for regime change from the religious community”

አቶ መለስ መግለጫ ሳይሰጡ ቀሩ።



(ዘ-ሐበሻ) አቶ መለስ ዜናዊ በከፍተኛ ሕመም ላይ መሆናቸውን ሲደብቅ የቆየው የኢትዮጵያ መንግስት ከሰሞኑ በምክትል ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት “አቶ መለስ ህመማቸው የሚያሰጋ አይደለም፤ በጥቂት ጊዜያት ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ” የሚል መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል። ትናንት የመንግስት ባለስልጣናት አቶ መለስ ዜናዊ ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጡ የተገለጸ ቢሆንም ተሰርዟል። የውጭ ሃገር ሚዲያዎች ሳይቀር መለስ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንዳሉ በመዘገብ ላይ ናቸው።
ይህን ተከትሎ የአቶ መለስ ህመም እጅግ አደገኛነቱን ያሳያል የሚሉት ታዛቢዎች እንዳሉ ሆኖ ዛሬ

መለስ ላልተወሰነ ጊዜ ስራ አይጀምሩም፤


በ21 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በጤንነት ችግር በ19ኛው የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባ ላይ ያልተሳተፉት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸው ተሰማ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ የውጭ ሕክምና ክትትላቸውን ጨርሰው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱም ምንጮች ገልጸዋል፡፡
Azeb Mesfin, wife of Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi, leaves the venue of general assembly, Organization of African First Lady against HIV/AIDS meeting,on July 16,2012 during the 19th African Union summit in Addis Ababa. (Photo Getty Images)

ላለፉት አሥር ቀናት አካባቢ ሕክምናቸውን በውጭ ሲከታተሉ የቆዩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ፣ ወደ አገራቸው ሲመለሱም በቶሎ ሥራ እንደማይጀምሩ ታውቋል፡፡ ለ21 ዓመታት ያለዕረፍት ከፍተኛ የአገር ኃላፊነትን ሲወጡ የቆዩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሕመማቸውም ምክንያት ካለባቸው የሥራ ጫና ብዛት የመጣ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተወሰኑ ጊዜያት ካለባቸው ከባድ ኃላፊነት ርቀው ዕረፍት እንዲያደርጉ በሐኪሞቻቸው መመከራቸውን ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕክምናቸውን ሲከታተሉበት የቆዩበት አገር ለደኅንነታቸው ሲባል እንዳይገለጽ የጠየቁት ምንጮች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እሳቸውን ሄደው መጐብኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዳሉም ታውቋል፡፡ ባለፈው እሑድ በይፋ በተከፈተው 19ኛው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ አምባሳደር ብርሃነ ያልተገኙ ሲሆን፣ ኢትዮጵያን የወከሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ዶክተር ተቀዳ ዓለሙ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ልዩ አማካሪ በአቶ ንዋይ ገብረ አብና በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ተከበው ታይተዋል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን የባለቤታቸው ጤንነት እየተሻሻለ በመምጣቱ በመሪዎቹ ስብሰባ ላይ መሳተፍ ችለዋል፡፡ ወይዘሮ አዜብ ከትናንት በስቲያ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባም ላይ ነበሩ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባት እና የፖለቲካው አሰላለፍ


የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲስ አበባ መግባት እና የፖለቲካው አሰላለፍ
ህመማቸው ፀንቶ ቤልጂየም ሀገር በመታከም ላይ ይገኙ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ትላንትና ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል። ሕይወታቸው እንዳለፈ ሲነገር የነበረው አቶ መለስ ወደ ቤተመንግስታቸው የተመለሱት ‹‹ከህመማቸው አገግመው›› ይሁን ወይም ‹‹ከዚህ በኋላ በህክምናው አትድንም ተብለው በተስፋ መቁረጥ›› ይሁን እስከ አሁን ለማረጋገጥ አልቻልኩም። የተረጋገጠው በህይወት መግባታቸው ብቻ ነው፡፡
የአቶ መለስን መታመም ተከትሎ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ አራት ሀይሎች ‹‹በሸዋ ፖለቲካ›› ጥበብ ግብግብ ገጥመዋል። በእርግጥ አንደኛው ሀይል (ቡድን አንድ) የበላይ የመሆን ዕድሉን እያሰፋ ነው።
(እኔ ካገኘሁት መረጃ አንፃር አሸናፊው ቡድን እንዲህ አይነት ገፅታ ሊኖረው ይችላል፡፡ አቀራረቤም በአገኘሁት መረጃ ላይ ተንተርሼ ለመተንተን የሞከርኩት ነው፡፡ መቼም የህወሓት ባህሪ ሊጨበጥ እንደማይችል ሁላችንም እናውቀዋለን)
የኃይል አሰላለፉም እንደሚከተለው ነው፡-
ቡድን-1. የቡድኑ አስተባባሪ አቦይ ስብሃት ነጋ ሲሆኑ የቡድኑ ቁልፍ ሰዎች
1. ስዩም መስፍን
2. ብርሃነ ክርስቶስ
3. አባይ ፀሐዬ
4. አባይ ወልዱ (የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት)
5. ጄኔራል ሳሞራ የኑስን ጨምሮ በርካታ ጄኔራሎች
ይህ ቡድን ካሸነፈ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን አለመመለሳቸውን ካረጋገጠ፡- በጠቅላይ ሚኒስትርነት ኃይለማርያም ደሳለኝን
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ም/ጠ ሚኒስትርነት ደግሞ ብርሃነ ክርስቶስን ለማድረግ ወስኖአል።

ቆንጆዋን ልጅ በተሰበረ መነጽር


 – በልጅግ ዓሊ


በተከታታይ ተመስገን ደሳለኝ በፍትህ ጋዜጣ ላይ የሚያቀርባቸውን ጽሁፎች አነባለሁ። በብዙዎቹ ብስማማም በመሃል ጣልቃ በሚያስገባቸው አንዳንድ ትንታኔዎች ላይ አልስማማም። አለመስማማትም ሳይሆን መታረም አለባቸው የሚል እምነት አለኝ።
ተመስገን <<የኔ ትውልድ>> የሚለውና <<ያ ትውልድ>> የሚለው ነገር አለው። ከብዙ ጽሁፎቹ እንደምንረዳው “የእሱ ትውልድ” ከቀይ ሽብር በኋላ የተፈጠረው ሲሆን፣ “ያ ትውልድ” የሚለው ደግሞ ከቀይ ሽብር በፊት ያለው ይመስላል። ብዙውን ትንታኔው የሚያተኩረው “ያ ትውልድ” ሞኝ፣ ለማይረባ ነገር መስዋትነት የከፈለ፣ ቅራኔዎችን በሚገባ ባለማያዙ የተጋደለ አስመስሎ ያቀርብና . . . የእሱ ትውልድ ግን “አርቆ አሳቢ ፣ በእንቶ ፈንቶ የማይጣላ፣ ቅራኔን በበሰለ ሁኔታ የሚመለከት” አድርጎ ለመሳል ይሞክራል። ይህ የእሱ ትንተና ከእሱ ጽሁፍነት አልፎ እውነት ቢሆን በጣም አስደሳች ነበር። እውነቱ ግን ሌላ ነው።
የተመስገን ትውልድ በአብዛኛው በእኔ ትንታኔ <<የድጋፍ ወረቀት ሠራዊት>>ነው ። ይህ ደግሞ ካለ ምክንያት አይደለም። በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ትግል የግል ጥቅም ከፖለቲካ መድረክ ላይ ማጋበስ የተጀመረውም ከቀይ ሽብር በኋላ ሆኖ እናገኘዋለን። ቀይ ሽብር በኅብረተስብ ውስጥ የፈጠረው ፍርሃት ዜጎች የፖለቲካ ጥያቄ ቢያነሱ ሊደርስባቸው የሚችለው አሰቃቂ ሥቃይ በእውን እንዲያዩት ስለተደረገ ሃገርን ከሚመለከት ማናቸውም ጉዳይ መራቅን የመርጠ ትውልድ ነው። ይህንንም አያይዞ ለግል ጥቅም መሮጥ በሰፊው ተጀመረ። ከቀይ ሽብር በኋላ ለሃገር መሞት ማስከበሩ ቀርቶ፣ የድህንነት ሠራተኛ፣ የአየር በአየር ነጋዴ፣ “የሕዝባዊ ድርጅቶች” (የአኢወማ፣ አኢሴማ ፣ መኢሠማ . . .ወዘተ) መሪ ሆኖ መመረጥ ወይም መሳተፍ ጥቅም እንዳለው እየታወቀ መጣ።

Tuesday 17 July 2012

መድረክ ምሩቃን በኮብልስቶን ሥራ መሰማራታቸው የፖሊሲ ውድቀትን ያሳያል አለ


“አንድ የኢሕአዴግ ባለሥልጣን ልጅ ኮብልስቶን ሲፈልጥ አሳዩንና አሳፍሩን” ዶ/ር መረራ ጉዲና
source reporter 
የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን የኮብልስቶን ሠራተኞች መሆናቸው የአገሪቱን የትምህርት ፖሊሲ ውድቀት የሚያሳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሰፊው የሚጣሱባትና ሠርቶ መኖር እጅግ የከበደባት አገር መሆኗንም ድርጅቱ ገልጿል፡፡
በኢሕአዴግ የሚመራው መንግሥት ትምህርትንና የትምህርት ተቋማቱን የሚጠቀምባቸው ለአገር ዕድገት ከማሰብ አንፃር ሳይሆን፣ ለፖለቲካ ፍጆታና ለቁጥር ማሟያ ለማዋል መሆኑን የጠቆመው መድረክ፣ “በትምህርት ጥራቱ መውደቅ ለዘመናዊ ሳይንስ፣ ለዘመናዊ ቴክኖሎጂና ለዘመናዊ ራዕይ ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍራት የተሳነው የኢሕአዴግ ትምህርት ፖሊሲ፣ ይግረማችሁ ብሎ ተመራቂ ኮብልስቶን ጠራቢዎች እያፈራ መሆኑን በኩራት እየተናገረ ይገኛል፤” ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ ይወቅልኝ ለሠራሁት ፊልም ምንም ክፍያ አላገኘሁም” ፍልፍሉ



(ዘ-ሐበሻ) ኮሜዲያን ፍልፍሉ በዚህ ሳምንት በሰሜን አሜሪካ የተሠራጨውን አዲሱን “የዜግነት ክብር” የኮሜዲ ፊልም “ኢቫንጋዲ ፕሮዳክሽን ለኔ ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይከፍለኝ የወጣ በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅልኝ እፈልጋለሁ። ሕብረተሰቡም ይህንን ሲዲ እንዳይገዛ ጠየቀ። የኢቫንጋዲ ፕሮዳክሽን ባለቤት ዳንኤል ታምሬ በበኩሉ እኛ ሲዲውን የገዛነው ከሌላ ሰው ነው ሲል ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ አስታወቀ።
ኮሜዲያን በረከት በቀለ ወይም እኛ የምናውቀው ስሙ ፍልፍሉ “እኔ ወደ አሜሪካ መምጣቴን ተከትሎ ከ እኔ እውቅና ውጭ ሲዲው ለገበያ መውሉን ሳይ በጣም አዝኛለሁ።” ካለ በኋላ ማህበረሰቡ ይህን ሲዲ ባለመግዛት ይተባበበር ብሏል። ፍልፍሉን በቪዲዮ ቃለ ምልልስ አድርገነዋል ይመልከቱት። ከቪዲዮው ቀጥሎ ደግሞ የኢቫንጋዲ ፕሮዳክሽን ባለቤት የሰጡንን አስተያየት ያንብቡና ፍርዱን እናንተ ስጡ።

ፍልፍሉ ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ብሶቱን ካሰማ በኋላ አሁን ታትሞ የወጣውን “የዜግነት ክብር” ሲዲ ያሳተመው ኢቫንጋዲ ፕሮዳክሽን ባለቤት አቶ ዳንኤል ታምሬ ጋር ወደ አትላንታ ደውለን ነበር። አቶ ዳንኤል በቅድሚያ ፍልፍሉ ለዚህ ሲዲ ክፍያ እንደተሰጠው የሚያረጋግጥ የፊርማ ማስረጃ እንዳለውና ካለማስረጃ ምንም ዓይነት ሥራ እንደማይሰሩ ገለጸ። እኛም “ፍልፍሉ ክፍያ የተፈጸመለትን ማስረጃ ልትሰጠን ትችላልህ ወይ?” ስልነው “በሚገባ ብሎ የውሉን ማስረጃ በኢሜይል እንደሚልክልን ነገረን”። ከደቂቃዎች በኋላ አቶ ዳንኤል ወደ ዘ-ሐበሻ በመደውል “የውሉን ወረቅት ለናንተ መስጠት አልችልም። ጠበቃዬ አትስጥ ብሎኛል” ካለ በኋላ ቀጥሎም “ሲዲውን እኛ የገዛነው አቶ ተስፋዬ ፈጠነ ካሳና እንድሪያስ መኮንን ከተባሉ ሰዎች ነው” ሲል ተናግሯል።
“አቶ ተስፋዬ ፈጠነ እና አቶ እንድሪያስ እነማን ናቸው?” የሚል ጥያቄ አስከተልን ዳንኤልም “እንድሪያስ የፊልሙ ፕሮዲውሰር ነው፤ ፊልሙ ላይም ከፍልፍሉ ጋር ሰርቷል። አቶ ተስፋዬ ደግሞ ከእንድሪያስ ጋር የተዋዋለ ሰው ነው። እኛ ከነሱ በሕጋዊ መንገድ ነው የገዛነው። እነርሱም ለፍልፍሉ እንደከፈሉት ነው የምናውቀው። ምክንያቱም እንዴት አንድ ሰው ምንም ሳይከፈለው ከ30 ደቂቃ በላይ ቪድዮ ሊቀረጽ ይችላል?። ስለዚህ ፊልም ጉዳይ ማስረጃውን ከፈለግክ ወደ አዲስ አበባ አቶ እንድሪያስ እና ተስፋዬ ፈጠነ ጋር መነጋገር ትችላለህ። በኛ በኲል በሕጋዊ መንገድ ፊልሙን የገዛነው ከነሱ ነው” ሲል ተናግሯል።
ለአቶ ተስፋዬ ፈጠነ ና አቶ እንድሪያስ መኮንን ወደ አዲስ አበባ ደውለን ልናገኛቸው አልቻልንም። ሃሳብ ካላቸው ዘ-ሐበሻ ድረ ገጽን በማንኛውም ሰዓት ማስረጃምን ማቅረብ ይቻላል።

Share It

  •  

[ሰበር ዜና] በአዲስ አበባ ሙስሊሞች እየታፈሱ ነው። ኦህዴዶች ጥያቄ አነሱ።



(ዘ-ሐበሻ)፡ በአዲስ አበባ በተለያዩ ወረዳዎች የሙስሊሙን እንስቃሴ እየመሩ ነው ወይንም ይደግፋሉ የተባሉ ወጣቶች በሰፈር ጥቆማ እየታሰሩ መሆኑን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ። የኦሮሞ/ሕወሐት ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) የሙስሊሞቹ ጥያቄ ካልተፈታ በኦሮሚያ ክልሎች የሚፈጠረው ነገር ያሰጋናል፤ መንግስት ባስሸኳይ መላ ያበጅለት የሚል ጥያቄ እያቀረበ መሆኑ ተጠቆመ።

Monday 16 July 2012

“የምንፈራው አስከፊ አደጋ እየመጣ ነው” የሙስሊም አንድነት ኮሚቴ


ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)
ከምን ግዜውም በላይ አስፈላጊ የተባለ የአንድነት ጥሪ ተላለፈ፤
በአዲስ አበባ የተለያዩ አቅጣጫዎች ድንገተኛ ጥሪ “አዛን” ጥሪ የተላለፈላቸው ወገኖች ወደ አወሊያ ሲያመሩ በፌደራል ፖሊስና በመከላከያ ሃይል የሃይል ርምጃ እንደተወሰደባቸው ለማወቅ ተችሏል። ከተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ አወሊያና አንዋር መስጊድ ሲያመሩ በነበሩት የዕምነቱ አባላት ላይ የደረሰውን ጉዳት በዝርዝር ባይገልጹም ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ ተሰምቷል።
“የምንፈራው አስከፊ አደጋ እየመጣ ነው። መንግስት የሙስሊሙን ህዝብ ጥያቄ ለማፈን እየወሰደ ያለው ርምጃ ፈር ለቋል” ሲሉ በአትላንታ ከተማ የሚገኘው የሙስሊም አንድነት ኮሚቴ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ ጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ አስታውቀዋል። ኮሚቴው ለጋራ ንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት እንዳስታወቀው አኢጋን ከቆመለት ዓላማ አንጻር ቀደም ሲል እንደሚያደርገው ሁሉ የአደጋውን አስከፊነት ለህዝብና ለሚመለከታቸው ሁሉ አስቀድሞ ይፋ እንዲያደርግም አመልክቷል።
የዘር፣ የጎሳና የሃይማኖት ልዩነት በመፍጠር በልዩነት የስልጣን እርከኑን ለማስጠበቅ ላፍታም የማይተኛው የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ የፌደራል ፖሊስ ሃይሎች በትናትናው ዕለት ሀምሌ 6 ቀን 2004 ዓ ም በአወሊያ የጁምአ ጸሎት ስርዓት ላይ ለመካፈል በተገኙ የዕምነቱ ተከታዮች ላይ የፈጸሙት ድርጊት የቀሰቀሰው ቁጣ ከወትሮው ሁሉ የተለየ መሆኑን የኮሚቴው አባላት ያስረዳሉ።

የብሎጋችን ሚጢጢ የአቋም መግለጫ፤ “አቲቪ አያጣላንም!”


 አቤ ቶኪቻው


በትላንትናው ሌሊት የመንግስት ታጣቂዎች በአወሊያ ግቢ ባደረሱት የአስለቃሽ ጭስ እና አስለቃሽ ጥይት ጥቃት በአካባቢው የነበሩ ክርስቲያን ወገኖች ለሙስሊም ወንድምናEthiopian Television trying to insist fight between Muslims and Christians እህቶቻቸው ውሃ በማቀበል እና ቤታቸው በማሳደር ያላቸውን ወገናዊነት ሲያሳዩ እንደነበር ተሰምቷል። ይሄ በጣም አስደሳች ነው!
ከዚህ በፊትም እንዳወጋነው ባለፈው ጊዜ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሙስሊሙን፤ “ክርስቲያን መጣብህ!” ክርስቲያኑን ደግሞ “ሙስሊሙ መጣብህ” በማለት አንዱን በአንዱ ላይ የሚያነሳሳ ፕሮግራም ቀደሞ የሰራው በእንዲህ ያለው ጥቃት ጊዜ እርስ በርስ መተባበር እንዳይኖር ለማድረግ አስቦ ነው ሲሉ በርካቶች ይወቅሳሉ… (ለነገሩ በበርካቶች አሳበብኩ እንጂ  አንዱ እና ዋናው ወቃሽ እኔ ነኝ! እንደውም ከትላንትናው እስለቃሽ ጭስ እኩል የኢቲቪ ከፋፋይ ፕሮግራም አስለቅሶኛል! ብዬ ብናገር ግነት አለው ብላችሁ እንዳትጠረጥሩ!)
በነገራችን ላይ “መንግስታችን” በሌሊት እንዲህ አይነት ጥቃት ማድረሱ ደግሞ ለሌላ መከፋት ዳርጎኛል። በጦርነት ህግ እንኳ በሌሊት አንድ አካባቢን መደብደብ የሚቻል አይመስለኝም። እንደዛኛው ሰውዬ “ጦርነት ህግ የለውም!” ብለን ካልተሳለቅን በስተቀረ አግባብ አይደለም።
“ሌሊት ለአራዊት ቀን ለሰራዊት” ከሚለው የመፅሐፍ ቃል ባፈነገጠ መልኩ፤ እንደ አራዊት በለሊት የተደረገውን ወረራ የመጣው ይምጣ ብዬ አወግዛለሁ! ነውር ነው! ብዬም እጨምራለሁ!
አሁንም ጭምር አንዋር መስጊድ ፌደራል ፖሊሶች እና ባለ ቀይ ቆብ ወታደሮች በተለምዶ “አጋዚ” የሚባሉት በብዛት ይታያሉ። በርካታ ሙስሊም ወገኖችም በአንዋር መስጊድ “አሏህ ዋክበር” በማለት ላይ ይገኛሉ!
ከሁሉም በላይ በግሌ ክርስቲያን ወገኖች የሙስሊም ወንድሞቹ ጥያቄ ከአክራሪነት ጋርም ሆነ ከኢስላማዊ መንግስት ጋር ምንም ዝምድና እንደሌለው። ተረድቶ ከወገኖቹ ጋር በመቆሙ ለማመስገን እወዳለሁ!
ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የእኔ እና የወዳጄ ሁሴንን የቆየ ወዳጅነት በ “ዶክመንተሪ ፊልም” ማጠልሸት ይቻላል ብሎ ማመኑ የሚያስቅም የሚያሳቅቅም ነው!
አንድነታችን ለዘላለም ይኑር!

አጭር ወሬ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሌሉበት ፓርላማው በጀት እያፀደቀ ነው!



     

ለወትሮው ሰኔ 30 የሚዘጋውና ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ተራዝሞ የነበረው የፓርላማው በጀት ማፅደቂያ ቀን በዛሬው ዕለት ሐምሌ  9 2004ዓ.ም እየተካሄደ ነው።
በስብሰባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አልተገኙም። ይህንን ወሬ እስካቀብላችሁ ድረስ “ከፓርላማ አባላቱም የት ሄዱብን?” ብሎ የጠየቀ የለም! ከአፈ ጉባኤውም የተሰጠ መግለጫ የለም። እኔማ በሆዴ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፓርላማ አባላቱ ጋር ተጣልተዋል እንዴ!? ብዬ እያሰብኩ ነው።
ቆይ ይቺን መረጃ ብጤ ላድርሳችሁ ብዬ ነው እንጂ! ተመልሼ ስለፓርላማው ስብሰባ ትንሽ የምናወጋው ሊኖረን ይችላል!
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መታመማቸውን እስካሁን ድረስ በየትኛውም የመንግስት ሚዲያ አልተገለፀም።
ወየውላቹ ድነው የመጡለት!
ወዮላችሁ!

Zenawi’s absence at AU Summit raising questions about his health – AP



Zenawi’s absence at AU Summit raising questions about his health – AP

ADDIS ABABA, Ethiopia (Associated Press) — Ethiopia’s longtime ruler and most powerful figure, Prime Minister Meles Zenawi, is not attending an African Union summit that opened Sunday in Ethiopia, which further fueled speculation that he might be seriously ill.
About three dozen African heads of state and government gathered in Addis Ababa on Sunday, but Meles did not attend the meeting — a first since he assumed office in 1991.
Meles was expected to open the New Partnership for Africa’s Development (NEPAD) meeting on Saturday. But Senegalese President Macky Sall opened the gathering instead, telling participants that Meles was unable to be present due “to health conditions.” Sall wished Meles “good health.”
The most recent images of Meles aired by state-run Ethiopian Television showed him noticeably thinner. Opposition websites are claiming that Meles is being treated for a serious illness.
The government declined to comment on the matter.
Ethiopia’s parliament was set to hear from Meles last week when the country’s lawmakers were scheduled to approve Ethiopia’s current fiscal budget, which began July 8, but Meles did not address parliament.
Meles in 2010 promised to step down by 2015. Hailemariam Desalegn was named deputy prime minister. He is also the country’s foreign minister.
Short URL: http://www.zehabesha.com/?p=8686
Posted by zehabesha on Jul 15 2012. Filed under Home. You can follow any responses to this entry through the RSS 2.0. You can skip to the end and leave a response. Pinging is currently not allowed.
Syalk Ayamer