"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 17 August 2012

ቴዲ አፍሮ የለንደን ከተማን "በጥቁር ፈረሱ" አሟሟቃት



በታምሩ ገዳ
                                                                                                                                                                                                                             እውቁ የሙዚቃ አቀንቃኝ ቴዲ አፍሮ  (ቴድሮስ ካሳሁን )   በረካታ አርቲስቶችን ባሳተፈው    እና በአጭር ቀናት ውስጥ   ገበያውን
በተቆጣጠረበት "ጥቁር ሰው"  አልበሙ  ጨምሮ  በበረካታ ተወዳጅ ዘፈኖቹ  እማካኝነት  በታላቋ ብርታኒያ   ውስጥ ለሚገኙ  የሙዚቃ
አድናቂዎቹ በለንደን ከተማ ወስጥ ታላቅ የሙዚቃ ምሽት አቀረበ ፡፡ በክብር እንግድነት የተጋበዘው አትሌት ሃይሌ ገ|ስላሴ በመድረኩ  ላይ  
ብቅ ሳይል ቀረ፡፡
ባለፈው ቅዳሜ   ሃምሌ 28 2004 አ.ም (ነሃሴ 4 2012  እ.ኤ.አ ) በተደረገው  የሙዚቃ ምሽት ላይ ለመገኘት  ብዛቱ  ከሁለት  ሺህ ሰባት
መቶ በላይ  የሚገመት  የሙዚቃ አፍቃሪ  ወደ  አዳራሹ  ለመግባት  ወረፋ  መያዝ  የጀመረው  ገና  በጊዜ ነበር ፡፡ከአደናቂዎቹ ጋር  
በግንባር ከተገናኘ  ከአመት በላይ ያስቆጠረው  አርቲስት  ቴዲ አፍሮ በመድረኩ ላይ  ከስድስት  በላይ አዳዲስ  ዘፈኖቹን  ጨምሮ  ከሃያ
አንድ በላይ  የተለያዩ  የራሱ እና የሌሎች  ታዋቂ አርቲስቶች   ዘፈኖችን   ለአድናቂዎቹ አቅርቧል፡፡
የለንደን ከተማ የአስራ ሶስተኛው  ኦሎምፒክ  እና ፓራ ኦሎምፒክ (የአካለ ስንኩላን)  ውድድድሮችን በማሰተናገድ በተጠመደችበት ወቅት
ወደ  መዲናይቱ ብቅ ያለው አርቲስት ቴዲ አፍሮ  ለኢትዮጵያ  አትሌቶች ዘወትር ያለውን  እክብሮት እና  መልካም ምኞቱን ሳይገልጽ
አላለፈም ፡፡    በቅርቡ በገበያ ላይ የዋለው አልበሙ    ኢትዮጵያዊያን    በተለይ    በአጼ ምንሊክ    ቆራጥ አመራር   የወራሪው የፋሺስት  
ኢጣሊያን    ሰራዊትን    አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል ያድርጉበትን      ተጋድሎን የሚዘክረው    "ጥቁር ሰው"    የተሰኘው ዘፈኑን   
ለአድናቁዎቹ ሁለት ጊዜ  ያቀነቀነ ሲሆን  በረካታ አደናቂዎቹም   አረንጓዴ ፡ቢጫ እና ቀዩን  የኢትዮጵያ  ሰንድቅ አላማን  በማውልብለብ  
ለአጼ ምኒሌክ ሆነ ለቴዲ  አፍሮ ያላቸውን እክብሮት  እና ፍቅር  ገለጸዋል፡፡

Etiopias statsminister mystisk forsvunnet

Aug.16/2012 የ ኖርዌይ ቁጥር አንድ ጋዜጣ'' Aftenposten'' ስለ አቶ መለስ በ ኖሽክ (ኖርዌጅኛ) የወጣው ጽሁፍ የ እንግሊዝኛ ትርጉም::The 57-year-old Meles has been in power in Ethiopia for 21 years and virtually eliminated the opposition in the country. The usually highly visible prime minister has n

ot been seen in public in two months - last time was during the G20 meeting in Mexico in June.

The absence has led to a reputation floods, both in and outside of Ethiopia, about what has happened to Meles. Power Tool Google Trends shows a huge increase in the number of searches on "Meles Zenawi", especially from computers in Ethiopia.

Diplomatic sources said the news agency AFP that Meles is seriously ill and is in a hospital in Belgium, which the government has denied.

- We are confused

Wednesday tried spokesman Bereket Simon to calm the floods reputation by saying that everything was fine with the Prime Minister.

- He is becoming healthier, resting and exercising his duties as prime minister and head of state, said the spokesman, the country's former information minister.

He did not tell what disease suffering from Meles, his whereabouts or any exact date for when he will appear in public again. The government has stated that he will be back in place before Christmas, which in no way stopped the speculation about what might have happened.

- We are confused, says 30-year Endalk Haile Michael in the capital Addis Ababa to the site CNN.com.

And adds:

- In Ethiopia, we have a tradition of secrecy surrounding our leaders and not to tell where they are located. People are afraid, there is much uncertainty right now. There are many rumors and much that is unclear.

Power Vacuum

One of the main questions now raised is what will happen if Meles does not return to work. After 21 years in power, which he coup in 1991, he has built up a position as sole ruler without significant political rivals.

- If Meles disappears, there is a huge power vacuum in a period. He has been a prominent figure. He is more or less alone on the top, says Stig Jarle Hansen, an associate professor at the University of Life Sciences.

Hansen, who is an expert on the situation in the Horn of Africa, points out that he does not know what rumors Meles that is true or false.

- But it is the incredible number of rumors. Much is about who will eventually take over. Rumour has it that there are many who are positioning themselves now. As far as I can judge, is the army together. The Army is a very important force. As long as it is collected, it means that there will be a civil war if Meles should not return, he said.

http://www.aftenposten.no/
nyheter/uriks/

Etiopias-statsminister-mystisk-
forsvunnet-6966679.html

Thursday 16 August 2012

የአቡነ ጳውሎስ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት አጭር ሪፖርታዥ



by Deje Selam on Thursday, 16 August 2012 at 12:39 ·
. አስከሬናቸው በባልቻ ሆስፒታል ይገኛል፤ ጥቅመኛዋ እጅጋየሁ በየነ “አልሞቱም፤ አስከሬናቸው ይመርመርልኝ” እያለች በማወክ ላይ ትገኛለች::
. ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአድባራትና ገዳማት አለቆች በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጓል::
. የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል::
. ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ይሾማል፤ ከቋሚ ሲኖዶሱም ጋራ እየመከረ ይሠራል:: (ሕገ ቤተ ክርስቲያን)
. “ውሉደ ጳውሎስ” /እነ እጅጋየሁ በየነ/ በፓትርያርኩ ስም “ጳውሎስ ፋውንዴሽን” ለማቋቋም እየተሯሯጡ ነው፤ የሀብት ቅርምቱን ለማመቻቸት ይኾን?
. በፓትርያርኩ በተለያዩ ዘመዶቻቸው ስም በአንድ የመንግሥታዊው ባንክ ቅርንጫፍ ሦስት አካውንቶች ውስጥ ከ22 ሚልዮን ብር በላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል::
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 10/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 16/ 2012/) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ፣ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም፣ ንጋት ላይ በዳጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ፓትርያርኩ ከትናንት በስቲያ፣ ነሐሴ 8 ቀን 2004 ዓ.ም ማምሻውን ወደ ደጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ገብተው ሕመማቸውን ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉላቸው በቆዩት የሆስፒታሉ ዶክተሮች ሕክምና ቢደረግላቸውም በቆየባቸው በሽታ ዛሬ ንጋት 11፡00 ላይ መሞታቸውና አስከሬናቸውም በዚያው እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡ አቡነ ጳውሎስ የምንገኝበትን የፍልሰታ ለማርያም ጾም በድሬዳዋ ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ወቅድስት አርሴማ የሴቶች ገዳም የማሳለፍ ልማድ ቢኖራቸውም በዘንድሮው ሱባኤ ግን መሰንበቻቸውን ያደረጉት የፕትርክናው መንበር በሚገኝበት በአዲስ አበባ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ነበር፡፡
በቀደሙ ዘገባዎቻችን እንደገለጽነውና በሰሞኑ የሱባኤው ቅዳሴ ውሎዎች እንደተረጋገጠው÷ አቡነ ጳውሎስ የጀመሩትን ጸሎተ ቅዳሴ ለመጨረስ ተስኗቸው ቅዳሴው ከሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ውጭ ሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት /እነ ብፁዕ አቡነ ገሪማ/ እየተተኩ እንዲጠናቀቅ ሲደረግ ነበር፡፡ የዐይን እማኞች እንደተናገሩት÷ ፓትርያርኩ በጸሎተ ቅዳሴው መካከል በወንበር ላይ እንደተቀመጡ ሁለት እግራቸውን ፊት ለፊታቸው በሚገኝ ሌላ ወንበር ላይ ሰቅለው ታይተዋል፤ ወደ መኖሪያቸው ሲወጡም ይኹን ሲገቡ ዙሪያቸውን በረዳቶቻቸው ተደግፈው ነው፡፡ ከቆየባቸው የስኳር በሽታና ሌሎችም ሕመሞቻቸው መወሳሰብ ጋራ በተያያዘ ሁለቱም እግሮቻቸው ከአውራ ጣታቸው ጀምሮ እስከ ጉልበታቸው ድረስ በከፍተኛ ደረጃ ተጎድቷል፡፡ እግራቸው እንዲቆረጥ ጤናቸውን በሚከታተሉላቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ሐኪሞች ሲነገራቸውን ቢቆይም ፓትርያርኩ የሐኪሞቹን ምክርና ማሳሰቢያ ችላ ብለው በውጭ ምንዛሬ በሚገዟቸውና በመርፌ በሚወስዷቸው መድኃኒቶች ራሳቸውን ሲያስታምሙ ቆይተዋል፡፡ አቡነ ጳውሎስ ከትናንት በስቲያ ወደ ሆስፒታል የገቡት ታዲያ በዚሁ እግራቸው ላይ በከፍተኛ ጥዝጣዜ እየተሠቃዩ በነበረበት ኹኔታ ነበር፡፡
ሐምሌ 5 ቀን 1984 ዓ.ም የተሾሙትና ለኻያ ዓመታት በፕትርክና የቆዩትን የአቡነ ጳውሎስን የቀብር ሥነ ሥርዐት ለማስፈጸም ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ዛሬ ጠዋት ከመከሩበት በኋላ “የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ” መቋቋሙ ተዘግቧል፡፡ የፓትርያርኩ የሕዝብ ግንኙነት ጽ/ቤትና ፕሮቶኮል ሓላፊዎችም በየአህጉረ ስብከቱ ስልክ በመደወል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳማትና አድባራት አለቆች በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ ጥሪ በማስተላለፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት በርካታ አባቶች፣ አገልጋዮችና ምእመናን በመንበረ ፓትርያርኩ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በመገኘት ኀዘናቸውን እየገለጹ ሲኾን ስለ ጸሎተ ፍትሐቱ እና የቀብር አፈጻጸም መርሐ ግብሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሚያወጣው መግለጫ እየተጠበቀ ነው፡፡

Wednesday 15 August 2012

(ሰበር ዜና) በኩክ የለሽ ማርያም ቤ/ክ አካባቢ በደረሰ ፍንዳታ ምእመናን ሞቱ


Share
(ዘ-ሐበሻ) ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ አሁን ከኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ደብረብርሃን ከተማ አካባቢ በተለምዶ ኩክ የለሽ ማርያም ተብሎ በሚጠራው ቤ/ክ አካባቢ ምንነቱ ባልታወቀ ፍንዳታ ለሱባዔ የገቡ ምዕመናን ሞቱ፤ በርከት ያሉ ሰዎችም እንደቆሰሉ የምንጮቻችን ዘገባ አመለከተ። ምንጮቻችን በኩክ የለሽ ማርያም አካባቢ የፈነዳውን ማን እንዳጠመደው እንዳልታወቀ ገልጸው፤ የሞቱት ሰዎች ቁጥርም እስካሁን እየተጣራ መሆኑም፤ የቆሰሉትም በርካታ እንደሆነ እንጂ ቁጥሩ ለጊዜው እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
የ16 የኪነምህረትን ጾም በማስመልከት በኩክ የለሽ ማርያም ቤ/ክ በርከት ያሉ ምዕምናን ከተለያዩ ቦታዎች በመጓዝ ሱባዔ የሚገቡ ሲሆን ይህ አደጋ መከሰቱ እጅጉን እንዳነጋገረ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ጠቁሟል።
አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች መንግስት ራሱ አፈንድቶ ከሙስሊሞች እንቅስቃሴ ጋር ለማያያዝ ያደረገው ሴራ ሊሆን ይችላል እያሉ ነው።
መረጃውን አጠናቅረን ጠለቅ ያለ ዘገባ ይዘን ለመቅረብ እንሞክራለን።  

ዋልድባ ጉድ እያፈላች ነው፤ አቡነ ጳውሎስም ሆስፒታል ገቡ




Share

(ዘ-ሐበሻ) ዋልድባ ገዳምን የተዳፈሩ ሁሉ እግዚአብሄር እየቀጣቸው እንደሆነ በርከት ያሉ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ያምናሉ። የተከበረውን ገዳም የስኳር ማሳ ለማድረግ የወያኔ ሰዎች ሲንቀሳቀሱ፤ እነ አቡነ ጳውሎስም ገዳሙ አይነካም፤ ልማት ነው እያሉ ሲከራከሩ ነበር። ያን ጊዜም የሚከተለው ግጥም በዘ-ሐበሻ ላይ ቀርቦ ነበር።
እያንገራገረ ህዝቡ እያባባ
አበው እያዘኑ ወጣት እያነባ
እየተቃወሙ እየጮሁ እነ አባ
ዜናው በዓለም ዓቀፍ እየተስተጋባ
ድንገት ሳይታሰብ ስኳር ገዳም ገባ
ከፍ ከፍ ብሎ ለዚያውም ዋልድባ
ሲጠፋ ሲሰወር ሲደበቅ ቆይቶ
በአቋሙ ጠንክሮ በአቋሙ ጸንቶ
አመክሮ ሳይዝ ድንገት ገዳም ገብቶ
ጣፋጭ የነበረው ሊመር ነው ከቶ
ለሱ የሚስማማ ስንት ቦታ ሞልቶ
ስኳር እሳት ሆኖ ከገበያ ጠፍቶ
ሊቀመጥ ነው አሉ መቃብር ቤት ገብቶ
ምን ይውጥሽ ይሆን ከእንግዲህ መርካቶ
አባቶ ች ምን አሉ በዋልድባ ያሉ
በአባቶች አጽም ላይ ሸንኮራን ሲተክሉ
ከተቀበረበት እየፈነቀሉ
በደም የበቀለ ሸንኮራ ሊበሉ
በውሳኔ ጸንቶ
ኸረ እግዚኦ በሉ!
ይሄስ ጥሩ አይደለም
ከአቅም በላይ ሆኖ ህዝቡ ቢበደለም
አባቶች ዝም በሉ ይረሱት ግድ የለም
ዋልድባ በጾሙ ምነው ተፈተነ
በገዳሙ ልማድ ትንሽ ከታዘነ
ጸሎቱ እንደወጉ ከተከናወነ
ውሎ አድሮ ይሟሟል ስኳር ስለሆነ
በዋልድባ 4 የፌደራል ፖሊሶች በጅብ የመበላታቸው ዜና ከዚህ ቀደም ተዘግቧል። ገዳሙን ለመጠበቅ ከሄዱት መካከልም የሚታመሙ ብዙ ናቸው። የአቶ መለስ ዜናዊ ሕመምም እንዲሁ ከዚሁ ዋልድባ ገዳም ጋር ተያያዞ የገዳሙ አባቶች ‹‹እናንተ ምታታሞች [ምትሃተኞች] ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕመም ተጠያቂዎች ናችኹ፡፡›› እየተባሉ ሲዋከቡ ነበር። ዛሬ ደጀሰላም ድረ ገጽ እንደዘገበው ደግሞ ኻያኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸውን ከሐምሌ 5 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ወሩ መገባዳጃ ሲያከበሩ የቆዩት አምስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በጠና ታመው ምሽቱን ወደ ደጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል መግባታቸውን ዘግቧል። ይህን ተከትሎ የዋልድባ አባቶች ጸሎት እየተሰማ ነው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች በየቦታው በርክተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አስተሳሰባችንን በማናወጥ ወንጀል” ሊጠየቁ ይገባል ተባለ!


ይህንን ቃል ለመጀመሪያ ግዜ የሰማሁት ሰፈሬ እንጦጦ ኪዳነምህረት ፀበል ነው። ተጠማቂዎች በአጋንንት እና በሌሎች ርኩስ መናፍስት አይምሯቸው ይናወጥ እና በአስጠማቂዎች ፍዳቸውን ያያሉ። “ያናወጥከውን አዕምሮዋን መልስ…! ልቀቅ…! ውጣ!” ይባላል። ከዛም ወዶ ሳይሆን በግዱ ይለቃል። ያናወጠውን አዕምሮም ይመልሳታል።
ዛሬ ደግሞ ጋዜጣ በማሳተም የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና ከፍ አደርጋለሁ ብሎ መከራውን ሲያይ የነበረው ወዳጃችን ተመስገን ደሳለኝ “የህብረተሰቡን አስተሳሰብ በማናወጥ” ወንጀል ተከሷል።
ይሄንን ነገር እርኩስ መናፍስት ብቻ የሚያደርጉት ሲመስለን የነበርሁ።ን እኛ፤ በነገሩ ግራ ተጋብተን እንዴት አድርጎ አስተሳሰባችንን እንዳናወጠ  አቃቤ ህግ የሚያቀርበውን ማስረጃ ለመስማት ተቻኩለናል። የተሜን የክስ ሂደት አስመልክቶ እየተከታተልኩ የአቅሜን ያህል “አንጀት ላይ ጠብ የሚል” መረጃ ለማቀበል እሞክራለ
አሁን ግን ነገሩን ያነሳሁት “የህብረተሰቡን አሰተሳሰብ ማናወጥ” የሚለው ክስ እኛ ለእርኩስ መናፍስት እንጂ ለምድራዊው ሰው የሚቀርብ ስላልመሰለን ትተነው እንጂ በአሁኑ ግዜ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስተሳሰባችንን ያናወጠ ማን አለ!? ብለው የሚጠይቁ አንዳንድ ወዳጆችን በመስማቴ ነው።

እስከመቼ ከባለድል አትሌቶች ጀርባ ተደብቀው ያጭበረብራሉ?


August 14, 2012


አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ሀላፊዎችና የፕሬስ አታሼ ከባለድል አትሌቶች ጀርባ ተደብቀው እስከመቼ ያጭበረብራሉ?
“ፊሽ – የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ፕሬስ አታሼን አነጋግርና አትሌቶችን ለቃለ መጠይቅ የምናገኝበትን መንገድ እስቲ አመቻች” የሚለው ጥያቄ የመጣው የ2012 የለንደን ኦሎምፒክ ጨዋታዎች የኦሎምፒክ ዜና አገልግሎት (Olympic News Service) ውስጥ በምሰራበት ወቅት የአትሌቲክስ ቡድን ስፖርት ባለሞያ ከሆነው ባልደረባዬ ነበር። የዜና አገልግሎቱ ስራውን ሲጀምር ወደለንደን የሚመጡት የኦሎምፒክ ቡድኖች ህዝብ ግንኙነት ወይም ፕሬስ አታሼ ሀላፊዎች የብሪታኒያ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ቁጥር መረጃ ከሀላፊዎቹ ስም አጠገብ የሰፈረበት የመገናኛ ብዙሀን መመሪያ አነስተኛ መጽሀፍ ተሰጥቶን ነበር። ታዲያ ባልደረቦቼ የእኔን የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪነት እና ቀድሞ ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረኝ የሬድዮ ጋዜጠኝነት ሞያን ከግምት ውስጥ በማስገባት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድንን በተመለከተ መረጃዎችን የማሰባሰብ ሀላፊነቱን ለእኔ ሰጡኝ። ባልደረቦቼ ያላወቁት ነገር ቢኖር ከኢትዮጵያ የመንግስት ድርጅቶች መረጃ ለማግኘት ከመሞከር ይልቅ ነዳጅ ማውጣት የሚቀል መሆኑን ነው።
የመጀመሪያው ስራዬ የነበረው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ፕሬስ አታሼ ማን እንደሆነ መፈለግ ነበር። ከጥቂት አሰሳዎች በኋላ ገበያው ታከለ የሚል ስም የተሰጠን የመገናኛ ብዙሀን የግንኙነት መረጃ መመሪያ ላይ ተጽፎ አየሁ። ገበያው ታከለ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የገንዘብ ያዥ እንደነበሩ ስለማውቅ ‘እውነት ከሰውዬው ጋር ትክክለኛ የሚዲያ ስራ መስራት ይቻላለን?’ የሚል ጥያቄ እንዳነሳ አስገደደኝ። ሌላኛው የአእምሮዬ ክፍል ደግሞ ‘ምንአልባት ነገሮች ተለውጠውና ተሻሽለው ይሆናል’ የሚል ሀሳብ አነሳና በሁለት ሀሳብ ተወጥሬ ለማንኛውም ሰውዬውን ላግኛቸውና የግንኙነት መስመራችንን ላመቻች በሚል ስልክ ለመደወል ስዘጋጅ ከገበያው ታከለ ስም አጠገብ የስልክ ቁጥር እንደሌለ ተገነዘብኩ። ቀጣዩ አማራጭ የነበረው ከሀገርቤት የሚመጡ ጋዜጠኞችን በመገናኘት የአቶ ገበያው ታከለን አድራሻ ለማግኘት መሞከር ቢሆንም የቀድሞ ባልደረቦቼም ተመሳሳይ ችግር እንደገጠማቸው ለማወቅ ሰከንዶች አልወሰደበኝም። በሮች ሁሉ ዝግ የነበሩ ከመሆናቸው በተጨማሪ ከኦሎምፒክ ስታዲዬሙ አጠገብ የሚገኘው የአትሌቶች መለማመጃ ቦታ ላይ ያገኘሁት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ቡድን አባል ስለቡድኑ አንዳንድ ዝግጅቶች እንዲነግረኝ ስጠይቀው “ለቃለምልልስ ከላይ ትእዛዝ ማግኘት አለብኝ” የሚል መልስ ከመስጠቱ በተጨማሪ “የፕሬስ አታሼውን ስልክ ቁጥር ነገ አመጣልሀለሁ” ብሎኝ ከተለያየን በኋላ እንደተደበቀኝ የለንደን ኦሎምፒክ ተጠናቀቀ።
በኦሎምፒኩ የፕሬስ አታሼው ቀዳሚ ስራ ከመገናኛ ብዙሀን ጋር ግንኙነቶችን በመፍጥር ለሚመለከተው አንባቢ፣ ተመልካችና አድማጭ ስለሚፈልጋቸው ሰዎች መረጃዎችን እንዲያገኝ ማስቻል ቢሆንም ገበያው ታከለ ግን አይደለም የኢትዮጵያ አትሌቶችን ሊያገናኝ እራሱም ሳይገናኝ ቀርቷል።

Tuesday 14 August 2012

ቻልኩበት የተሰኘው የኩኩ ሰብስቤ አልበም በሚቀጥለው ሁለት ሳምንት ይለቀቃ


ቻልኩበት የተሰኘው የኩኩ ሰብስቤ አልበም በሚቀጥለው ሁለት ሳምንት ይለቀቃ

በለስላሳ ወይንም ትዝታ እየተባለ በሚታወቀው የሙዚቃ ስልት እና በአዘፋፈኖቿ ቅላጼዎቿ በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነት ያላት የድምጻዊት ኩኩ ሰብስቤ “ቻልኩበት ” የተሰኘው አልበም በሚቀጥለው ሁለት ሳምንታት ለህዝብ በይፋ ይለቀቃል ።በአዲካ አከፋፋይነት የሚለቀቀው ይኽው የሙዚቃ አልበም በአቢይ አረቃ እንደተቀናበረ የደረሰን መረጃ ያመለክታል ። በተለይም ለማለዳ ታይምስ የደረሰው የቅርብ መረጃ እንደሚያመለክተው ከብዙ ልፋት እና ጥረት በሁዋላ አልበሟን ለመልቀቅ ከፍጻሜ እንደደረሰች ተገልጾአል ። በኢትዮጵያ ውስጥ እና በአውሮጳ እና እንዲሁም በሌሎች አገራት በሚከሰተው የሰው ልጅ ስራ ፈጠራ መብትን ገፈፋ ወይንም የኮፒ ራይት ጥሰትን አስመልክቶ ብዙሃኑ ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን ለህዝብ ከማቅረብ ይልቅ ለማፈን ተገደው የነበረ አስታውሰው ፣ከማፈን ምንም ለውጥ እንደሌለ በመረዳት ስራዎቻቸውን ለመልቀቅ መገደዳቸውን ገልጸዋል በዚህ ስድስት ወራት ተከታታይ ከሶስት ያላነሱ የሙዚቃ ስራዎች መለቀቃቸው ይታወቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአሁን ሰአት በመላው አለም የሚከናወነውን የሰዎችን የፈጠራ ስራ የሚያስከብር ማህበር በሰሜን አሜሪካ በቺካጎ አካባቢ ፈቃድ ማግኘቱን እና ስራውን በሰፊው በቅርቡ በመጀመር ዝግጅቱን ያጠናቀቀ እንደሆነ ከድርጅቱ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ይኸው ድርጅት ከአሜሪካ የኮፒራይስ ኦርጋናይዜሽን ጋር ጥምረትን ፈጥሮ በከፍተኛ ደረጃ የሚሰራ ሲሆን ይበልጥ የኢትዮጵያን ኮፒ ራትይ ስራዎችን በሰሜን አሜሪካ ያለማንም ፈቃድ አባዝቶ መሸጥ በስፋት የሚከናወን ሲሆን በተለያዩ የኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ሱቆች ውስጥ እንደሚሸጡ    አጣርቶ መረጃዎቹን የያዘ መሆኑ አክሎ ገልጦአል ። ፈቃዱን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮም ከአሜሪካን ፌደራል ኢንቨስቲጌሽን ቢሮ ጋር በመተባበር ጥናቶቹን እያደረጉ ክሶችን ማዘጋጀትም እንደጀመሩ ተገልጾአል፣ ።በሌላም በኩል በሰሜን አሜሪካ ለሚከናወነው የፈጠራ ስራዎችን መብት የማስከበር ስራን ለመተባበር እያንዳንዱ ደራሲ ፣ሃያዚ ፣ሙዚቀኛም ፣ሆነ የባለቤትነት መብትን ማስከበር የሚፈልግ ማንኛውም ግለሰብ በአፍሪካን አርት ኤንድ ፓተንት ራይት በተሰኘው ድርጅት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ድርጅቱ ጥሪውን ለማለዳ ታይምስ ያስተላለፈ ሲሆን ፤ንበረቶቻቸው የተዘረፉባቸውን ሰዎች በሙሉ በድርጅቱ ጠበቆች አማካይነት ወዲያውኑ ክስ ሊመሰርት እንደሚችል ይገልጻል ።     በቅርቡም በኮሚዲያን ፍልፍሉ ላይ ተፈጽሞብኛል ብሎ በቪድዮ ማስረጃ በዘሃበሻ ጋዜጣ አዘጋጅ ሄኖክ አለማየሁ በኩል የተለቀቀውን የምስል ቅንብር እና የጥያቄና መልስ  በመመልከት ይህንን የመብት ጥሰት ለማስቆም ኮሜዲያኑን ለማነጋገር ጥረት ያደረገ ሲሆን በሚቀጥለው አምስት ቀናት ውስጥ በቺካጎ ውስጥ ለሚያደርገው የመድረክ ዝግጅት ፕሮግራም ላይ ፍልፍሉን ለማነጋገር መዘጋጀቱን እና እንደ አንድ አባልነት እንዲመዘግበው ጥሪ ሊያቀርብለት እንደሚችልም ገልጾአል። በሌላም በኩል የፍልፍሉን የስራ መብት ጥሰት ያደረገውን ግለሰብ አጣርቶ ያወቀው ሲሆን በአትላንታ ከተማ እንደሚኖር እና ከኢትዮጵያ ጀምሮ እስከ አሜሪካ  በዲጄነት እንደሚሰራ ጭምር አክሎ ገልጾአል ሆኖም ግን ስለ ግለሰቡ ማንነት ከፍልፍሉ ውሳኔ በሁዋላ ወደ ፍርድ ቤት በሚያመራበት ወቅት ሊገልጽ እንደሚችል አክሎአል ።  ይህንን ጉዳይ ከፍልፍሉ ከተቀበኩ ክሱን እስከመጨረሻው ድረስ እገፋዋለሁ ያለው ይኸው ድርጅት የመብት ጥሰትን ለማስቆም አንደኛ አላማችን ስራችንን በተግባር መስራት ነው ብሎአል ። የዚህ ድርጅትን የንግድ ፈቃድ ምዝገባ ቁጥርንም አያይዞ እንዲገለጽለት አመክሮ ጠቁሞአል.8467233  ኢልኖይ ሲሆን ለምዝገባው በቅርቡ በማለዳ ታይምስ እና እንዲሁም በኮንስትራክሽን ላይ ባለው ዌብሳይት ላይ እንደሚለቅ ተገልጾአል   ።


አቦይ ስብሐት “አዲስ አድማስ ጋዜጣ ውሸቱን ነው መለስ በቤታቸው የሉም” አሉ



ስለ አቶ መለስ ዜናዊ ማውራት ደክሞኝ ነበር። ሳስበው ሳስበው እርሳቸው የሆኑትን ሆነው ደከመኝ ሳይሉ እኔ እንዴት ደከመኝ እላለሁ ብዬ ተፀፅቻለሁ። መቅደላዊት የተባለች ወዳጄም ከሪያድ በሰደደችልኝ አስተያየት ሀዘኑን እንረሳው ዘንድ ስለርሳቸው መጨዋወታችንን እንቀጥል እንጂ ድንኳን ሳይነሳ የምን ዝም ዝም ነው የሚል ወቀሳ ሰንዝራልኛለች። እኔም በሆዴ የምን ሀዘን ብዬ ሳበቃ  “እውነት ግን ምን ነካኝ…!” ብዬ ሂሴን ውጫለሁ!


                                 አቦይ ስብሐት “አዲስ አድማስ ጋዜጣ ውሸቱን ነው መለስ በቤታቸው የሉም” አሉ

አሁን በቅርቡ ከኔ በላይ ውስጥ አዋቂ ላሳር ያለው አዲስ አድማስ ጋዜጣ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በቤተ መንግስት እያገገሙ ነው” በሚል ርዕስ ባሰፈረው ዘገባ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራት ባለስልጣናት ጋር እየተመካከሩ በቤታቸው ውስጥ የጠቅላይነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው የሚል ሀተታ አቅርቦልን ነበር።

እርግጥ ነው በርካታ የአራዳ ልጆች የጋዜጣውን ዘገባ በጥርጣሬ ነበር የተመለከቱት። አንዳንዶቹም “ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቤተ መንግስት እየገገሙ ነው ወይስ እያገገሙ!?” ሲሉ ጠይቀው ነበር። በአራዶች ቋንቋ “መገገም” ማለት እምቢኝ አልተውም፣ የመጣው ቢመጣ ዘወር አልልም፣ የያዝኩትን ከምለቅ ወገቤ ይላቀቅ ወዘተ. የሚል ትርጉም ቢሰጠው ብዙ አራዶች ይስማሙበታል። በዚህ የትርጉም አግባብ ታድያ አቶ መለስ በቤተ መንገስቱ እውነትም እየገገሙ ከሆነ ሞተውም ሆነ ድነው አይለቁንም ማለት ነው።

የሆነው ሆኖ ትላንት ለኢሳት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) (እናንተዬ ኢሳት እና ኢቲቪ ስማቸው እየተመሳሰለ ያለበትን ሁኔታ ልብ አላችሁልኝ!?) እና አቦይ ስብሀት ለኢሳት ሲናገሩ አዲስ አድማስ ጋዜጣ መለስ ቤተ መንግስት ውስጥ ናቸው ያለው ውሸቱን መሆኑን ተናግረዋል!  አቦይ ስብሀትን አመስግነን አዲስ አድማስን “ሼ” ብለን ስለጠቅላይ ሚኒስትራችን ጉዳይ ዳግም ለማውራት ተነሳሽነታችን እንደመጣ በይፋ እንናገራለን!

በርሰቸው ጉዳይ ሌላም ጨዋታ አለኝ

US official: United States has been in contact with several Ethiopian officials since Meles‘ disappearance


US official: United States has been in contact with several Ethiopian officials since Meles‘ disappearance
Posted by admin on August 14, 20128 Comments
A note from Awramba Times Editor: As the current Ethiopian political structure is a monolithic party-state on the shoulders of Meles, his  disappearance from the public eye for the last 53 days is sill a hot issue. Washington Times became the first paper to break the silence among US Medias on the whereabouts of Meles. A spokesman in the U.S. Bureau of African Affairs told Washington Times that the United States has been in contact with several Ethiopian officials since Meles‘ disappearance but would not speculate on what changes might occur should the prime minister not return to his duties. Please read Ioannis Gatsiounis’ analysis on the Washington Times.

Where in the world is Ethiopia’s prime minister?
By Ioannis Gatsiounis
(The Washington Times) – The question is not a geographical brain teaser but a concerned query about the well-being of Prime Minister Meles Zenawi, who has not been seen in public for two months, and about Ethiopia’s commitment to U.S. counterterrorism efforts in neighboring Somalia.

U.S. Secretary of State Hillary Clinton with Hailemariam Desalegn and Birhane Gebrekrstos, in Addis Ababa, June 14, 2011 (Photo Reuters)
Ethiopian officials say Mr. Meles, 57, is recovering from an undisclosed illness, but he has not been seen or heard from since he attended the Group of 20 summit in Mexico in mid-June.
In his absence, the government has continued to brook little dissent from the media, activists and members of opposition parties. It also has announced that Ethiopian troops will remain in Somalia to help defeat al-Shabab, the al Qaeda-linked Islamist militant group that has ruled large areas of the Horn of Africa nation.
What’s more, government insiders say Mr. Meles has been grooming his deputy, Foreign Affairs Minister Hailemariam Desalegne, to succeed him.

Monday 13 August 2012

Mystery of ethiopia,s missing prime minister


Ethiopia’s missing prime minister has been taking part in diplomatic efforts to resolve the Sudan crisis from his sick bed, according to African Union officials.
Meles Zenawi, Ethiopia’s normally highly visible premier, has not been seen in public since June, and his government has refused to release any details of his condition.
His disappearance saw opposition groups claim that the 57-year-old had died, while there are unconfirmed reports that he has been treated for a brain tumour.
His absence became more apparent as Ethiopia hosted an important African Union summit in the capital, Addis Ababa, where Mr Meles would have expected to lead efforts to defuse the crisis in DR Congo and the simmering dispute between Sudan and newly independent South Sudan.
Despite his failure to appear at the summit – where his wife played host to African leaders – the AU say he has been in regular contact with the their chief mediator in the Sudans’ dispute, the former South African president Thabo Mbeki.
Mr Meles was understood last month to be being treated in a hospital in the Belgian capital, Brussels, but Ethiopian officials insist he has since returned to Addis Ababa. The influential information minister, Simon Berekat, a close ally of Mr Meles said he expected him to return to work “soon” and that he had taken “sick leave”.

የግፍና የሰቆቃ እስር በኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ቀጥሏል


e
የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ መሆን ኦነግ መሆን አይደለም። ወያኔ ግን ንጹሐንን ኦነግና አሸባሪ በማለት ያስራል። ከላይ የምታዩአዋቸው በ እስር ቤት ከሚገኙ የኦሮሚያ ተወላጆች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።
ኢህአዴግ እስር ቤቶቹን “ማረሚያ ቤቶች” እያለ ቢጠራቸውም፣ መጠሪያው እውነተኛውን የእስር ቤቱን ገጽታ ስለማይገልፀው እንደ ቀድሞ ስሙ “ወህኒ ቤት” ተብሎ ቢጠራ የተሻለ ይመስለኛል፡፡ የኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ከዚህ በፊት ከነበሩት የከፉ ናቸው ለማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም የግፍና የሰቆቃ እስሩ እጅግ ሰብአዊነት በጐደለው ሁኔታ በፖለቲካ አስተሳሰብና በዘር ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ነው፡፡ ቃሊቲ ወህኒ ቤት እስር ቤት ብቻ ሳይሆን የመረጃ ማዕከልም ነው፡፡ የመላው አገሪቱ የዕለት ተዕለት መረጃ በትኩሱ በቅብብል ይደርሳል፡፡ በመላው የኢትዮጵያ እስር ቤቶች ያለው ሁኔታም በየዕለቱ ይሰማል፡፡
ባለፈው ጽሁፌ ራሴን ለማስተዋወቅ እንደሞከርኩት በዚህ የዘረኞች ወህኒ ቤት 19 ዓመት ከ8 ወር ቆይቼአለሁ፡፡ እኔ ከዚህ ሳልወጣ አራትና አምስት ጊዜ ተመላልሶ የታሰረ እስረኛ አጋጥሞኛል፡፡ የሸዋሮቢት፣ የዝዋይና በቅርቡ ሥራውን የጀመረው የቂሊንጦ ከፍተኛ ወህኒ ቤት በመረጃ ደረጃ የሁለት የጐረቤታሞች ያህል መረጃ እንለዋወጣለን፡፡ በዚሁ መሠረት ዛሬ ህዝብ ስለማያውቃቸው ድብቅ እስር ቤቶችና በየድብቅ እስር ቤቶቹ ስለሚፈፀሙ ግፈኛ ድርጊቶች ላውጋችሁ፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግ “በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካና የህሊና እስረኛ የለም” ይለናል፡፡ ምንም እንኳን መኖሪያ ቤታችን ቃሊቲ ቢሆንም የመንግስትን መረጃ በተሟላ ሁኔታ እንከታተላለን፡፡ ሬዲዮ ከተከለከልን ሦስት ዓመት ቢልፈንም፣ በቃሊቲ ኢቴቪ 24 ሰዓት ይሰራል፡፡ የውጭ ሚዲያዎች የሚያወሩትን ውጭ ካለው በበለጠ እንሰማለን፡፡ በተጨማሪም ጠያቂዎቻችን ሁሉንም ነገር ይነግሩናል፡፡

Sunday 12 August 2012

አብዮታዊ ዴሞክራሲ ልጆቿን እየበላች ነውን!?


ይህ ጨዋታ ለዚህ ሳምንት ፍትህ ጋዜጣ የተላከ ነበር። ነገር ግን ፍትህ አሁንም በሀገሪቱ እንድትኖር ሰዎቻችን አልፈቀዱም። በፍርድ ቤት የታዘዘው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት “መጀመሪያ ሌላ ቦታ አሳትሙና በሚቀጥለው ሳምንት እኔ አትምላችኋለው” ብሎ መልስ ሰጠ ሲባል ሰማሁኝ። ይሄ በጣም አስቂኝ ነው…! ሌላ ማተሚያ ቤት እኮ የለም። አንድ ቦሌ ማተሚያ ቤት ነበረ እርሱም ደንበኛችን ስላልሆናችሁ አናትምላችሁም ብሏል። ወደየት እየተገፋን እንደሆነ እግዜር ይወቀው!

እስቲ ለማንኛውም ወጋችን ይጀምር…

ሰላም ወዳጄ እንዴት ሰነበቱልኝ? ፍትህ ጋዜጣ በፍትህ ችግር ታግታ ሰነበተችና ተጠፋፋን አይደል!? ጉልቤው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ያለ ምንም ህጋዊ አግባብ የእናንተን ጋዜጣ አላትምም ብሎ ደጅ ሲያስጠናን ቆይቶ ይኸው ዛሬ “የተከበረው” ፍርድ ተቆጥቶልን ለመገናኘት በቅተናል።

ብዬ ነበር የጀመርኩት… እኔማ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማክበር የሁላችንም ግዴታ መስሎኝ ነበር። ለካስ ፍርድ ቤቱን ማክበር የአንዳንዶቻችን ብቻ ነው…! አንድ ቀን አንዳንድ ከመሆን ተላቀን አንድ እንሆን ይሆናል! ብቻ ግን አስቲ ወጋችን ይቀጥል…

ፍርድ ቤት ካልኩኝ አይቀር፤ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላትን “ክቡር” ፍርድ ቤቱ “ኑ እንመካከር” ብሎ ጠርቷቸው ሲያበቃ ምንም ባልተከሰሱበት እና ባልተከራከሩበት ችሎት ገትሮ እያደረጋችሁ ያላችሁትን እናውቃለን ነገረ ስራችሁ በሙሉ ጥፋት ነውና እና “ወዮላችሁ” ሲል ማስጠንቀቂያ ሰጣቸው አይደለም እንዴ!?

ነገሩ እንዲህ ነው፤ የፓርቲው አመራር አባላት በትግል አጋሮቻቸው “እነ አንዷለም አራጌ    እንዲሁም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ የተፈረደው ፍርድ አግባብ አይደለም” ብለው በየ ሚዲያው ተቃውሞ ሲያሰሙ ነበር፤ ታድያ ፍርድ ቤት ሆዬ “ይሄማ እልም ያለ ጥፋት፤ ጭልጥ ያለ ወንጀል ነው።” ብሎ ጠርቶ ማስጠንቀቂያ ሰጣቸው። በነገራችን ላይ ለአንድነት ፓርቲ ፍርድ ቤቱ የላከው ደብዳቤ ላይ ተከሳሽ ማን እንደሚል ያውቃሉ…? “አቃቤ ህግ!”  ነው የሚለው። ወይ ጉድ! እናንተዬ አንዳንዴ ይሄ የኮምፒውተር ታይፕ መንፈስ ቅዱስ ያናግረዋል እንበል እንዴ!? የሆነ ሆኖ አቃቤ ህግ “ተከሳሽ” ተብሎ በተፃፈበት የመጥሪያ ወረቀት አንድነቶች ትህትና ይዟቸው ሄዱ… ከዛም ጥፋተኛ ናችሁ ተባሉ።

እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ፍርድ ቤት ሰዎችን ጥፋተኛ ለማለት ችሎት አቁሞ ሰዎቹ ተከራክረው ዳኞች ግራ ቀኙን አይተው ነበር ጥፋተኛ የሚሉት…! ወይስ ይሄ ነገር ዘወትር ማክሰኞ ማታ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ ብቻ ነው…!? ብዬ ልሳለቅ አማረኝና ግዜው የልማት እንጂ የስላቅ ነውን…!? ስል ራሴ ላይ ክልከላ አድርጌያለሁ።

እኔ የምለው ወዳጄ ልማቱ እንዴት ይዞታል!? ማለቴ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በኋላም እየተቀላጠፈ ነው ወይስ እየተንቀራፈፈ ነው? አይ እርሳቸው እንደው ሜዳ ላይ በትነውን እልም አሉ እኮ! አንዳንድ የፌስ ቡክ አሽሟጣጮች “አባይን የደፈሩ መሪ ሞትንም ደፈሩት!” እያሉ ሲናገሩ ሰምቻለሁ። እንዴት ነው ነገሩ በቃ ቁርጡ ታወቀ እንዴ!? በእርግጥ እዚህ ውጪው ሀገር የሚገኙ መገናኛ ብዙሃኖች መርዶውን ካረዱን ቆይተዋል። የሀገር ውስጥ ዘጋቢዎቻችን ግን አንዴ ገቡ፣ አንዴ ወጡ፣ አንዴ አረፉ፣ አንዴ አገገሙ እያሉ እያምታቱን ነው።

በዛ ሰሞን ፋና ኤፍ ኤም ራዲዮን “ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንድ ነገር ቢሆኑ ማን ይተካቸዋል!?” የሚል የህግ ውይይት ማድረጉን ስሰማ ይሄ ነገር በቃ ለይቶለታል ማለት ነው…? መቼም እዚህ አገር “ደግ አይበረክትም” ብዬ ተንሰቅስቄ ነው ያለቀስኩት። አሁን በቅርቡም ለጠቅላይ ሚኒስትራችን የስጋ ዝምድና እንዳላቸው የሚነገርላቸው እሜቴ ሚሚ ስባቱ ራዲዮ ላይ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢያርፉ እንኳ ሀገሪቷ በአንድ ሰው መሞትና አለመሞት ላይ የሚመጣ ለውጥ የለም” የሚል እጅግ ጨካኝ የሆነ አስተያየት ሰማሁኝ! በእውኑ ጠቅላይ ሚኒስትራችን አንድ ሰው የሚባሉ ናቸውን…? ለነገሩ ባለፈው ጊዜም እኚያ አቦይ ስብሀት “ፋጢመት ሞተች አልሞተች ዘሪሁን ሞተ አልሞተ መለስ ሞተ አልሞተ እኛ ምን አገባን” አይነት ነገር ሲናገሩ በሰማሁ ጊዜ በእውነቱ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ከእኛ በቀር አንድ እንኳ አሳቢ ሰው እንደሌላቸው ተረድቻለሁ።

ኧረ ስለ እትዬ ሚሚ ካነሳን አይቀር የምንቀደው አለን…

እማማ ሚሚ በኤፍ ኤም ራዲዮናቸው ላይ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሞቱም ግዴየለም” ከሚለው ጨካኝ ንግግር ጋር አብረው የዘመድ አንጀት ሆኖባቸው ነው መሰል “ደግሞም ሀገር ውስጥ ያለው ህዝብ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጤና እየፀለየላቸው ነው!” ብለው ሆድ አስብሰውኛል።  እሜቴ ሚሚ ልብ አላሉም እንጂ በውጪ ያለውም ኢትዮጵያዊ እንዴት በአንድ በአንድ እግሩ ቆሞ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚፀልይ ቢመለከቱ ይደነቁ ነበር። የምሬን ነው የምልዎት በርካታ በውጪ ሀገር የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ትልቅ ፀሎት እያደረገ ነው። እርግጥ ነው የአብዛኛው ሰው ፀሎት እርሳቸው ድነው የበደሉትን ይቅርታ እንዲጠይቁ እና ለንስሀ ሞት እንዲበቁ መሆኑን ሰምቻለሁ። (እኔ እንደሆንኩ  የሰማሁትን መደበቅ አይሆንልኝም።)

ወደ እትዬ ሚሚ ስንመለስ “ክብ ጠረቤዛ” የሚል አንድ ፕሮግራም አላቸው። እርሱን ፕሮግራም አልፎ አልፎ ለማዳመጥ እድሉ ገጥሞኛል። አንድ ግዜ ቁጭ ብዬ ስሰማ አንዱ ወዳጄ ሰማኝና ምን አለኝ መሰልዎ… ይሄ ፕሮግራም “በማሽካካት እና በጫጫታ የተሞላ በመሆኑ አንዳንድ ጊዜ ክብ ጠረቤዛ ነው ክብ ባንኮኒ ብዬ እጠራጠራለሁ።” ብሎኛል የምር ግን እኔ ራሴ ፕሮግራሙን ሳዳምጥ በተለይ አንዳንድ ጊዜ በገደል ማሚቶ የታጀበ ሳቅ እና ሁካታውን ሳዳምጥ ይሄንን ሰፈር የት ነበር የማውቀው…? ብዬ አይኔን ጨፈን አድርጌ አስባለሁ… ትዝ ሲለኝ ለካስ ቺቺኒያ እና ካዛንቺስ ነው….! የብርጭቆው ኳኳታ የለም እንጂ በእውነት “መሸታ” ቤቶቻችንን ትውስ ያደርጋል!

በነገራችን ላይ እነ እማማ ሚሚ ሲበሳጩ የሚናገሩትን አያውቁትም እየተባሉ ይታማሉ። ባለፈው ጊዜ ሙስሊም ወንድምና እህቶቻችን ላይ ሲያደርጉ የነበረው ዘለፋ እና ስድብ የቀለጠው መንድር ድራማ ላይ እንኳ የለም።

ብዙ ግዜ ሚዲያ ላይ ያለ ሰው ለብዙሃኑ ህብረተሰብ ስሜት እና እምነት ይጠነቀቃል። ማህበረሰቡ ውስጥ የአመለካከት ችግር አለ ብሎ እንኳ ቢያምን የሚሰራውን “ስህተት” ቀስ ብሎ በተለያዩ የኪነጥበብ ዘዴዎች እና ለዛ ባላቸው አቀራረቦች ለማረቅ ይሞከራል እንጂ እንደነ እትዬ ሚሚ “የጉራንጉር ሰፈር ስድብ” እየተሳደቡ መውረግረግ እንኳንስ ሚዲያ ላይ እና ሜዳ ላይም ቢሆን ከጨዋ ልጅ የማይጠበቅ ነውር ነው።