"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 17 January 2013

“ፍቅረኛሞቹ” አዜብና ብርሃነ – (ከኢየሩሳሌም አርአያ



አዜብ መስፍንን ከሱዳን አምጥቶ ሕወሓትን እንዲቀላቀሉ ያደረገ ነው። የፍቅር ግንኙነትም ነበራቸው። ይህ ሰው ብርሃነ ኪዳነማርያም (በቅፅል ስሙ ብርሃነ-ማረት) ነው። አዜብና ብርሃነ ድርጅቱን ሲቀላቀሉ የተቀበሏቸው አቶ አስገደ ገ/ስላሴ (አሁን የአረና አባል) ነበሩ። ጥቂት የበላይ አመራሮች በሁለቱ የፍቅር ግንኙነት ዙሪያ መከሩ። ከዛም የብርሃነና የአዜብ ግንኙነት እንዲቋረጥ በማድረግ ከለያዩዋቸው በኋላ ከመለስ ዜናዊ ጋር አዜብ እንዲጠቃለሉ ሆነ። (በነገራችን ላይ አንዳንድ ወገኖች አዜብና ሟቹ ክንፈ ገ/መድህን በጫካ ግንኙነት እንደነበራቸው ተደርጎ የሚነገረው ከእውነት የራቀ እንደሆነ የቅርብ ታማኝ ምንጮች ይገልፃሉ፤)
ወደ ዋናው ርዕሰ ጉዳይ እናምራ፥ በሕወሓት ውስጥ አድፍጠው መሰሪ ተግባር ከሚፈፅሙት አንዱ ነው ተብሎ በፓርቲው ወገኖች የሚፈረጀው ብርሃነ ኪ/ማርያም (ብርሃነ-ማረት) ማንነትና አደገኛ አካሄድ ምን እንደሚመስል ከላይ የተገለፀውን መንደርደሪያ ያስቀደሙ ታማኝ ምንጮች ተከታዩን ይላሉ።
ፓርቲው ወደ ስልጣን ሲመጣ አቶ ብርሃነ የተመደበው በመቀሌ ማዘጋጃ ሃላፊ ተደርጎ ነበር፤ መንግስት የከተማውን አስፋልት መንገድ ለማሰራት እንዲውል የመደበውን አምስት ሚሊዮን ብር « ቅርጥፍ» ያደርጋል። በወቅቱ የክልሉ ፕ/ት የነበሩት ገብሩ አስራት በወሰዱት እርምጃ ብርሃነ እንዲባረር ሲደረግ፥ ሁለት ግብረ-አበሮች የተባሉ ደግሞ ይታሰራሉ። የተባረረው ብርሃነ አዲስ አበባ ይመጣል። አዜብን ለማግኘት ብዙ ጥረት ካደረገ በኋላ ተሳካለት። ከዚያም አዜብ የቀድሞ « ፍቅረኛቸው»ን ለመታደግ ሲሉ ብርሃነ በሲቪል ሰርቪስ ኰሌጅ እንዲገባ ያደርጋሉ። ለረጅም አመት ድምፁን አጥፍቶ በኰሌጁ ቆየ። የኢትዮ- ኤርትራን ጦርነት ተከትሎ ለብርሃነ «ጥሩ» አጋጣሚ ፈጠረለት። ከቤተ መንግስት የማይጠፋ ሆነ፤ ከመለስ ጋር ቀን-ከሌሊት ምስጢራዊ ምክክሩ ቀጠለ። ታማኝና ቀኝ እጅ መሆኑን ለማሳየት በተግባር ተንቀሳቀሰ።
በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት ከመሰንጠቁና ይፋ ከመውጣቱ በፊት « ጥንስሱን » ያውቁ የነበሩት አቶ መለስና ብርሃነ ነበሩ። ብርሃነ ታህሳስ 1993ዓ.ም ከፍተኛ ባጀት ተመድቦለት ወደ አሜሪካ መጣ፤ በወቅቱ በፓርቲው ውስጥ ገና ክፍፍል አልተፈጠረም፤ በተባራሪዋቹም በኩል የታወቀ ነገር አልነበረም። ብርሃነ በአሜሪካ ፥ ላስቬጋስ፡ ቴክሳስ፡ቦስተን፡ አትላንታ፡ ሲያትል…ከተሞች እየተዘዋወረ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ቅስቀሳ በማካሔድ በሕወሓት መከፋፈል መፈጠሩን በይፋ ለድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች ገለፀ። ጎን ለጎን ሰዎችን በመመልመል ከአቶ መለስ ጎን እንዲቆሙ አደረገ። በኢምባሲ የተመደቡትን ሳይቀር እያስፈራራና እየዛተ ድጋፍ እንዲሰጡ አዘዘ። በቅስቀሳው ላይ የሚባረሩትን፡ የሚታሰሩትን አመራሮች በስም እየጠቀሰና በስድብ እያብጠለጠለ ነበር ቅስቀሳውን ያካሂድ የነበረው። በተለይ የገብሩ አስራትን ስም በማንቑዋሸሽ… ዘመቻ አካሂዶዋል።« ግዳጁን » በአግባቡ በመፈፀሙ…የፓርቲው ማ/ኰሚቴ አባል ተደርጎ የተመረጠው ወዲያው ነበር።
በሙልጌታ አለምሰገድ ይመራ የነበረውንና በፓርቲው መሰንጠቅ ማግስት የተቋቋመው የፌደራል ደህንነት ቢሮን ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አንዱ የሆነው ብርሃነ፥ ተግባሩን ሲጀምር..የአፈናና ስቃይ ሰለባ ያደረጋቸው ከፓርቲው የተወገዱ አመራሮች – ጠባቂዎችን ነበር። የገብሩ አስራትን ጠባቂዎች (ታጋይ የነበሩ) ጨምሮ በጅምላ እንዲታሰሩ አደረገ። ግርማይ (ማንጁስ) ከተባለ የፌዴራል ፖሊስ ኮማንደር ጋር በቅንጅት ሆነው ጠባቂዎቹን በደም እስኪታጠቡ አሰቃዩዋቸው፤ እነ ገ/መስቀል የተባሉ የቀድሞ ታጋዮች እጅና እግራቸው በብረት ሰንሰለት ታስሮ ከተሰቃዩ በኋላ ወደ ትግራይ ተወስደው..በአደገኛ ቦዘኔነት ክስ እንዲመሰረትባቸው አደረጉ። በስቃይ ብዛት ገ/መድህን የተባለ ህይወቱ አለፈ። ለረጅም ወራት ታስረው ከተፈቱ በኋላ በመቀሌና ማይጨው የቁም እስረኛ ተደረጉ። ምንም ስራ መስራት አይችሉም፤ ወደየትም ስፍራ መንቀሳቀስና ሌላ አካባቢ መሄድ አይችሉም፤..ይህ ሁሉ በብርሃነ የተፈፀመ ነበር።
በሌላ በኩል ደግሞ የዚህን ሰው አደገኛና መሰሪ አካሔድና ተግባሩን ከማንም በተሻለ ጠንቅቀው የሚያውቁና የእርሱ ወጥመድ «ሰለባ» የሆኑ የቀድሞ የፓርቲው አመራር አባላት ምንም ትንፍሽ አለማለታቸውና አለማጋለጣቸው አስገራሚ ነው። ምክንያቱም እነዚህ አካላት በአገር ውስጥ እንዴት እንደታፈኑ ብቻ ሳይሆን ..በዚህ ሰው እንዴት እንደተሰቃዩ ያውቁታል፤ ያስታውሱታል…ሲሉ ምንጮቹ ትዝብታቸውን ሳይጠቁሙ አላለፉም።..
በውጭ አገራት የሚኖሩ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች ማንነትና የሚያራምዱት አቋም በተመለከተ መረጃ አለው። በተመሳሳይ በተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ደጋፊዎች ዙሪያ መረጃ ማነፍነፍ የየዕለት ተግባሩ ነው። በተለያዩ አገራት የሚመደቡ አምባሳደራት በዚህ ሰው ጥብቅ ክትትል ይካሄድባቸዋል። ሲፈልግ አምባሰደራቱን በስድብ እያብጠለጠለ ያስፈራራል። አንዳንዶች ደግሞ የፈጣሪያቸው ያክል « ጠብ እርግፍ » እያሉ ይሰግዱለታል። በአውሮፓና አሜሪካ ሲዘዋወር በአስር ሺዎች የሚቆጠር ዩሮና ዶላር ተመድቦለት ነው የሚንቀሳቀሰው።..( በነገራችን ላይ አሜሪካ-ዲሲ የከተሙ የብርሃነ ጋሻ ጃግሬዎች አሉ፤ አንዳንዶቹ በፖለቲካ አሳበው ጥገኝነት የጠየቁ ናቸው። ግን ስራቸው ፓርቲውን በምስጢር ማገልገል፡ በየጊዜው ኢትዮጲያውያንን እየሰለሉ ለብርሃነ መረጃ ማቀበል ነው፤ የአሜሪካ ዜግነት ወስደው ይህን እየሰሩ የሚገኙትን በተመለከተ በቀጣይ እመለስበታለው፤ ማንነታቸው ይጋለጣል።)…
.አደገኛው የፓርቲው ሰላይ ብርሃነ ከወራቶች በፊት በአሜሪካ በተከሰተው ሁኔታ ውስጥ ነበር፤ ይኸውም አቶ መለስ በተገኙበት ስብሰባ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ጠ/ሚ/ሩን ሲቃወም …ብርሃነ በአዳራሹ ነበር። ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ለጠ/ሚ/ሩ አጃቢዎች ትዕዛዝ ይሰጥ ነበር። ..
ከፓርቲው ሊቀመንበር ህልፈት በኋላ፥ ብርሃነ የፓርቲው የጀርባ « አጥንት » በመሆን ማሽከርከሩን ተያይዞታል። በተጨማሪ ከአሁኑ ጠ/ሚ/ር ጀርባ አድፍጦ የመሪነት ሚና መጫወቱን ቀጥሎበታል። በሌላም በኩል ሽማግሌው ስብሃት ነጋ በየመድረኩ የሚፈነጩት ያለምክንያት አይደለም፤ ይህን ሰው ይዘውና ተማምነው ነው። ምስጢሩ ደግሞ ሁለቱ ማለትም ብርሃነና ስብሃት በጋብቻ የተሳሰሩ በመሆናቸው ነው። በተጨማሪ የፌዴራል ደህንነት በፀጋይ በርሔ ነው የሚመራው ይባል እንጂ ከፍተኛ ሚና የሚጫወተው ብርሃነ ነው። ሁለቱም ከስብሃት ጋር በጋብቻ የተሳሰሩ ናቸው። …ሽማግሌው ስብሃት በአዜብ ዙሪያ « መፈንቅለ ኤፈርት » ደግሰው « ጥንስሱን » ተግባራዊ ለማድረግ ሩጫቸውን ገፍተውበታል። ..ብርሃነ በቀድሞ « ፍቅረኛው » ላይ የሽማግሌውን የሴራ በትር ያሳርፋል?…በቀጣይ የሚታይ ይሆናል፤..ብለዋል ምንጮች።
በሚቀጥለው መጣጥፍ.. በ40 ሚሊዮን ብር ህንፃ ስለተገነባለት የአዜብ ውሽማ…የምንለው ይኖራል፤

Wednesday 16 January 2013

Reeyot Alemu: Imprisoned for defending free speech in Ethiopia



  It was only a matter of time before Ethiopian journalist Reeyot Alemu was sent to prison. Her country has become one of the most oppressive in the world for press freedom, with numbers of jailed journalists rising steadily each year.
Alemu was arrested on June 21, 2011, and accused of conspiracy to commit terrorist acts and participation in a terrorist organization under the controversial 2009 Anti-Terrorism Proclamation. Based on no evidence other than her articles criticizing the Ethiopian government, Alemu was sentenced to 14 years in Ethiopia's notoriously ill-maintained Kaliti prison.
Although the U.S. government has expressed concerns about "the extent to which Ethiopians can rely upon their constitutionally guaranteed rights to afford the protection that is a fundamental element of a democratic society", Ethiopia remains a key U.S. ally in its battle against al-Shabaab, al-Qaeda’s Somalia affiliate, which some believe has resulted in an unduly lenient attitude towards Ethiopia's human rights violations.
The arrest of Martin Schibbye and Johan Persson, two Swedish journalists, made evident the damage to its reputation the Ethiopian government was willing to accept in its effort to silence independent reporters. They were picked up after crossing the Somali-Ethiopian border illegally while reporting on ONLF rebels and the humanitarian situation in the closed Ogaden region. The 14-month-long diplomatic tug of war under the watchful eye of the international media ended when Schibbye and Persson were pardoned and released in September 2012 after they admitted guilt and were sentenced to eleven years in prison.
Reeyot Alemu refused to admit guilt in exchange for clemency and has, instead, appealed the verdict. In August 2012, to the surprise of many experts in the diplomatic community, and in part due to the international attention Alemu has received, including winning the 2012 IWMF Courage in Journalism Award, two charges against her were dropped and her sentence was reduced to five years. Alemu hasn't given up – her court dates have been postponed numerous times but there is still a chance that the appeals court will decide to drop the remaining terrorism charges against her on Tuesday, January 8th.
"Reeyot is young and well-educated. She could have easily left her country or chosen a different career - but she loves Ethiopia and her profession. She always held her head high and she gave me strength", Martin Schibbye said in an interview with the IWMF.
The first time he met Reeyot Alemu was on a prison bus from Makelawi, the central police investigation headquarters in Addis Ababa, to the Magistrate's Court where the prosecution repeatedly filed 28-day extensions to keep political prisoners in custody without charge. "What do you do?", Schibbye remembered asking Alemu on their first encounter. "I am a journalist", she replied. They quickly realized that everyone on that bus was a journalist or a politician from the opposition and that they were all charged with a crime they hadn't committed: terrorism. "That was the moment when we realized that we had ended up in a major crackdown against free speech in Ethiopia", Schibbye told the IWMF.

የፖለቲካ እስረኞችን ለማነጋገር ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ያመራው የሽማግሌዎች ቡድን በተቃውሞ ተመለሰ።

 
  • ርዕዮት አለሙን ያነጋገሩት ፓስተር ዳንኤል ‹‹የእስከዛሬው ተግባርህ የሚያስረዳው ኢህአዴግ ጉዳይ አስፈጻሚ ክንፍመሆንህን ነው፡፡ ስለዚህም በምንም አይነት ጉዳይ ላይ ካንተ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ አይደለሁም›› የሚል ያልጠበቁትን መልስ በማግኘታቸው የይቅርታ አጀንዳውን ሳያነሱ ተመልሰዋል፡፡

  • · የሙስሊሙ ማህበረሰብ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በበኩላቸው ፓስተር ዳንኤል እና ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያስ ‹‹ይህንን በጭራሽ አንቀበለውም፣ ጥፋተኛ ነንም አንልም፣ አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› የሚል መልስ ሰጥተዋቸዋል፡፡


  • · እስክንድር ነጋን ሳያነጋግሩት ተመልሰዋል፡፡


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በግል የፌስ ቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረው ማስታወሻእንደሚያስረዳውሀሙስ ጥር 2 ቀን 2005 . በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅ ይመሩ ከነበሩት ሽማግሌዎች ውስጥ የተዘጋጀ ሶስት ሰዎች ያሉት አንድ ቡድን በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝቶ ነበር፡፡ ከቡድኑ አባላት ፓስተር ዳንኤል እና ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያስ ለታሳሪዎቹ ‹‹ጉዳያችሁበፍርድቤትእየታየነው፤ስለዚህምክሱአሁንባለበትደረጃሊቋረጥአይችልም፡፡እናምክርክራችሁንአቋርጡናጥፋተኛነንበሉ፣ከዛምፍርድቤቱከፈረደባችሁበኋላይቅርታጠይቃችሁእናስፈታችኋለን››የሚል መደራደሪያ አቅርቦ ነበር፡፡ ሆኖም የሙስሊሙ መሪዎችይህንን በጭራሽ አንቀበለውም፣ጥፋተኛነኝምአንልም፣አላሁአእለም!ይቅርታአንጠይቅም››ሲሉ በድፍረትና በቁርጠኝነት መልሰውላቸው ወደ እስር ክፍላቸው መመለሳቸውንና በተጠቀሰው ዕለት እስክንድር ነጋ ዘለው አንዱአለም አራጌን ነጥለው ማናገራቸውን የጋዜጠኛ ተመስገን ማስታወሻ ያስረዳል፡፡ ተመስገን ጨምሮ የሽማግሌ ቡድኑ ለሙስሊሙ መሪዎች ‹‹የመጣነው አንዱአለምን ፈልገንነው፣እናንተንእግረመንገዳችንንሰላምእንበላችሁብለንነው››ሲሏቸው፣ ለአንዱአለም ደግሞ የዚህን ግልባጭ ምክንያት መስጠታቸውን አስታውሷል፡፡

በሌላ በኩል ከ5 ቀናት በኋላ ትላንት ጥር 7 2005 ዓ.ም ፓስተር ዳንኤል ገ/ስላሴ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝተው ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን እንዳነጋገሯት ለማወቅ ተችሏል፡፡ በማረሚያ ቤት ያለውን አያያዝ አስመልክቶ አስተያየቷን እንድትሰጣቸው በመጠየቅ ውይይታቸውን የጀመሩት ፓስተር ዳንኤል ከርዕዮት አለሙ ‹‹በቅድሚያ አንተ እኔን የምታየኝ እንደ አሸባሪ ነው ወይስ እንደ ፖለቲካ እስረኛ?›› የሚል አጸፋዊ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡ ፓስተር ዳንኤል በበኩላቸው ጥያቄውን ለመመለስ ብዙ ደቂቃ የፈጁ ቢሆንም ሁሉንም ታራሚ በአንድ አይን ነው የምናየው የሚል የተድበሰበሰ መልስ መስጠታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመልሱ ያልተደሰተችው ርዕዮትም ‹‹ሁሉንም ታራሚ በአንድ አይን የምታይ ከሆነ እኔን ለይተህ ማነጋገር አያስፈልግህም፡፡ መንግስት አሸባሪ ናት ብሎኛል፡፡ እኔ ደግሞ የፖለቲካ እስረኛ ነኝ እያልኩ ነው፤ ህሊናህ የአንዳችንን እውነት እንደተቀበለ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ነገር ግን ልትናገረው ስለማትፈልግ ታድበሰብሰዋለህ፡፡ በቴሌቪዥን እየቀረብክ የኢህአዴግን ጥፋቶች ስታድበሰብስም ብዙ ጊዜ ተመልክቼሀለሁ፡፡ ስለዚህ ስለማረሚያቤቱ አያያዝ የምሰጥህ አስተያየት የለኝም፡፡››በማለት መልሳለች፡፡ ፓስተር ዳንኤልም ይህንን መልስ ሲሰሙ ጥንካሬዋንና ድፍረቷን እንደሚያደንቁ በመግለጽ ‹‹የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቆራርጦ የሚያሳየውን ነገር ተመልክተሸ እንዲህ አይነት ድምዳሜ ላይ መድረስ ትክክል አይደለም›› በማለት ሊሞግቷት የሞከሩ ሲሆን ርዕዮትም ‹‹ስለ ማረሚያ ቤቶች የምትሰጣቸው ምስክርነቶች ተቆራርጠው መቅረባቸውን ተቃውመህ መግለጫ ስትሰጥ አንድም ቀን አልታየም፤ ይህ ብቻ ሳይሆን ከእስከዛሬው አጠቃላይ ተግባርህ የምረዳው የኢህአዴግ ጉዳይ አስፈጻሚ ክንፍ መሆንህን ስለሆነ በምንም ጉዳይ ላይ ካንተ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ ባለመሆኔ አዝናለሁ፡፡››በማለት ወደ ክፍሏ መመለሷን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህ የተነሳም ፓስተሩ ምንም አይነት የይቅርታ አጀንዳ ሳያነሱ ተመልሰዋል፡፡


  1.  


Monday 14 January 2013

አዲስ አበባ ረክሳለች!

ትውልድ አምካኝ ቤቶችን፣ ትውልድ አምካኝ ደላሎችን፣ በህጻናት የወሲብ ንግድ ገንዘብ የሚሰበስቡትን፣ ማጥፋት ቀላል ነው። ግን ተጠቃሚዎቹ ህግ አስከባሪዎቹ፣ ህግ አወጪዎቹና ዋናዎቹ “የአገሪቱ ህዳሴ ባለቤቶች” የሚባሉት በመሆናቸው አይታሰብም። አንዳንድ ዝግ ቤቶች በሲቪል ጠባቂዎች የሚጠበቁ ናቸው። አንዳንዴ ቤተመንግስቱንና ሟቹን የቤተመንግስት ነዋሪ ይጠብቁ የነበሩት በፈረቃ ይታደሙባቸዋል።
ሃኪሞች፣ የህግ ባለሙያዎች፣ አገር የሚመሩት፣ ህግ የሚያስከብሩት፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ አውራ ባለስልጣናት፣ ህዝብ ፊት ቀርበው በልማት ስም የሚምሉት ሃብታም ተብዬዎች፣ የፖሊስ የበላይ አመራሮች፣ የስለላ አውራ ሰዎች፣ አጫፋሪዎች፣ የአቻ ፓርቲ አመራሮችና መካከል ጥቂት የማይባሉ ከዳር እስከዳር መመሸጊያቸው ዝግ ቤቶች ናቸው። አንዳንዴም ከዝግ ቤቶች ፍራሽ ላይ ሆነው የፖለቲካ መመሪያ የሚሰጥበት አጋጣሚ አለ። ይህን አስደንጋጭ እውነት “መርከስ” ነው። አዲስ አበባ ይፋ አደረገችው እንጂ በየክልሉ ከተሞች የሚደረገው ተመሳሳይ ነው።
የሺሻና የጫት በጀት የሚመድቡ ባለስልጣናት አሉ። አስቤዛ ሲደረግ “ሙአሰል” ከህጻናት ዳይፐርና የዱቄት ወተት እኩል የሚመድቡ አሉ። ህጻናትን በመመልመል ሳውና በማስገባት፣ በማሰልጠን፣ ዘመናዊ ልብስ በማልበስ ለገበያ የሚያቀርቡ ብዙ ናቸው። እገሌ ለሚባል አየር መንገድ አስተናጋጅ እንቀጥራለን በሚል ታዳጊዎችን እያንጋጉ በወሲብ የሚነዱና የሚያነዱ ይህን ተግባራቸውን የሚፈጽሙት ማስታወቂያ እያስነገሩ ነው።
ግብረሰዶም የሚያስፋፉ በየሆቴሉ ድሆችን በማደን ማበላሸት ከጀመሩ ቆይተዋል። አሁን አሁን በየጎዳናው ታዳጊዎችን በማታለል ህሊና የሚያስት ኬሚካልና እጽ በመጠቀም ህሊናቸውንና አካላቸውን መስበር ተለምዷል። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው በዚህ የግብረሰዶም ወረራ ውስጥ ተጠቃሚ በመሆን ወንድሞቻቸውን የሚደልሉ መበራከታቸው ነው።
ህጻናትን ለወሲብ የሚያቀርቡ ነፍሰ በላዎች ኢኮኖሚያቸው አድጎ ባለ ዘመናዊ መኪናና ህንጻ መሆናቸው ነው። አዲስ አበባ ባሉ ዝግ ቤቶች ወሲብንና ግብረ ሰዶምን የሚያሻቅጡ ህሊና ቢሶች ጉዳይ ያሳሰበው ቀጭኑ ዘ-ቄራ የሚባለው የአዲስ አበባው አምደኛችን ከወራት በፊት “የሚዘጋባቸው ህጻናት” በሚል ርዕስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጠቁሞ ነበር። (ዕድሜ ለኢንሳና አፈናው ብዕሩ ማዕቀብ ተደርጎበት በተከታታይ ጽሁፎችን ሳያስነብብ ቢቆይም እንዲሁ እንደጠፋ ግን አይቀርም፡፡)