"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 13 July 2012

Ethiopian blogger Eskinder Nega jailed for 18 years


http://m.bbc.co.uk/news/world-africa-18825538
1 hour ago

Eskinder Nega was arrested after publishing a column questioning the arrests of some journalists
A prominent Ethiopian journalist and blogger has been sentenced to 18 years in jail for violating the country's anti-terrorism legislation.

Eskinder Nega and 23 others were found guilty last month.

They were accused of links with US-based opposition group Ginbot Seven, which Ethiopia considers a terrorist organisation.

Opposition activist Andualem Arage was given a life sentence by the court in the capital, Addis Ababa.

In May, Eskinder was awarded the prestigious Pen America's Freedom to Write annual prize for his work.

Human rights groups have criticised Ethiopia's anti-terrorism legislation for being too far-reaching.

Courtroom packed

እግዜር ኢህአዴግ ቢሆን ኖሮ የአቶ መለስን መያዝ አስመልክቶ የሚሰጠው መግለጫ




ከአቤ ቶኪቻው
ዛሬ አዲሳባ ፍትህ ጋዜጣ ላይ የምትወጣ ስለ አቶ መለስ መጥፋት አበክራ የምትጠይቅ እና የምትጨነቅ አንድ ጨዋታ አለችኝ። ለዝች ብሎግ አንባቢዎች ነገ ትለጠፋለች። እስከዛ ይቺን መቆያ እንኩማ፤
ያው ሁላችንም እንደሰማነው አቶ መለስ ተይዘዋል። ስንቱን ሲይዙ የነበሩት ሰውዬ አሁን ግን ራሳቸው በእግዜሩ በሽታ ተይዘዋል። በህመማቸው ሳቢያም ፓርላማው እንኳ ይኸው የ2005 ዓ.ም በጀቱን እስካሁን አላፀደቀም።
እኔ የምለው ግን በቃ አቶ መለስ ከሌሉ ሁሉም ነገር አለቀለት ማለት ነው? የምር ይሄ ነገር በጣም ያሳስባል።
ልክ እንደ አቶ መለስ ሆኖ የሚጫወት “ካስት” እንዴት አይኖርም!? እሳቸው ስለታመሙ እከሌ ወይም እከሊት እንደ አቶ መለስ ሆነው ይጫወቱልናል! መባል የለበትም እንዴ!? የቡድን ስራ ምናምን የሚባል ነገር የለም ማለት ነው…? አይበልባቸውና የሆነ ነገር ቢሆኑ ታድያ ምን ሊውጠን ነው!
ለማንኛውም ይቺን ያኽል ከተንደረደርን ወደ ፉገራችን እንግባ፤
እንግዲህ ይህ ዘገባ የሚተላለፍላችሁ በእግዜር ቁጥጥር ስር በሚገኘው ቴሌቪዥን ነው አሉ። በእግዜር ቁጥጥር ስር የሚገኝ ቴሌቪዥን የቱ ነው? ካሉኝ ህልም መሆኑን እገልፃለሁ። የምር ግን እግዜር ህልምን ያህል ቴሌቪዥን በእያንዳንዳችን ላይ ገጥሞ ሳለ ለገዛ ፕሮፖጋንዳው መጠቀም ሲችል በነፃነት የፈለገንን እንድናይ ማድርጉ ምን ያህል ዲሞክራት ቢሆን ነው ብለው አይደነቁም! በእውነቱ እንደ እግዜር አይነት ነፃነት የሚሰጠንን መንግስት ያምጣልን! እንደርሱ እንኳ የትም አይገኝም ግን ቢያንስ የሚቀራረብ…
ለማንኛውም እግዜር ኢህአዴግ አይደለም እንጂ ቢሆን ኖሮ የአቶ መለስን መያዝ አስመልክቶ በቴሌቪዥኑ እንዲህ ይል ነበር፤ ብለን ብንገምት ምን ይለናል!? በነገራችን ላይ ይህ ዜና ቃል በቃል ከዚህ በፊት እነ እስክንድር ነጋ፣ እነ አንዳለም አራጌ፣ እነ ውብሸት እና ርዮት የተያዙ ጊዜ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ያነበበልን ነው። ልዩነቱ እነ አስክንድርን የያዛቸው ፖሊስ ነው አቶ መለስን ደግሞ በሽታ ነው፤

የወያኔው ካንጋሮ ፍርድ ቤት እስክንድር ነጋ ላይ 18 ዓመት፣ አንዷለም አራጌ ላይ እድሜ ልክ እስራት ፈረደ




(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ አርብ በአዲስ አበባ የተሰየመው የወያኔው ካንጋሮ ፍርድ ቤት በነ አንዷዓለም የክስ መዝገብ ታስረው በሚገኙትና በስደት ላይ ባሉት፤ ጋዜጠኞች፣ ነጻ አሳቢ ዜጎችና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ላይ የፍርድ ውሳኔውን አስተላለፈ። ከገዢው ስርዓት ገለልተኛ ያልሆነው ካንጋሮው ፍርድ ቤት በታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ 18 ዓመት እስራት ፈርዶበታል።
ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ባስተላለፉት ዘገባ መሠረት በሰላማዊ መንገድ በሃገር ቤት እየታገለ የሚገኘው የአንድነት ፓርቲው አቶ አንዷለም አራጌ፣ የግንቦት ሰባት መሪዎች ዶክተር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እና የኢሳት ቴሌቭዥን እና ራዲዮ አዘጋጅ ፋሲል የኔ አለም ላይ በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ የወሰነው የካንጋሮው ፍርድ ቤት፤ አቶ መለስ ዜናዊን በአለም ሕዝብ ፊት አምባገነን መሪ እንደሆኑ ያስታወሳቸውና ያዋረዳቸው ጋዜጠኛ አበበ ገላው 15 ዓመት፣ በዋሽንግተን ዲሲ የአዲስ ድምጽ ራድዮ አዘጋጅ አበበ በለው 15 ዓመት እስራት በሌሉበት ፈርዷል፡፡
በቀድሞዎቹ የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች አብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽ ላይም የ8 ዓመት እስራት የበየነው የካንጋሮው ፍርድ ቤት በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሪ ኦባንግ ሜቶ ላይ 18 ዓመት፣ በአቶ ጸጋ ስላሴ ዘለሌ፣ በአቶ ውቤ ሮቤና በአቶ ናትናኤል መኮንን ላይም የ18 ዓመት እስራት ፈርዷል።
ከፍርዱ በኋላ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ አስተያየቶች እንደሚጠቁሙት “ድሮም ከወያኔ ፍርድ ቤት የሚጠበቅ ፍርድ ነው የተሰጠው። እነዚህን ነጻ አሳቢ ዜጎች መንግስትን ስለተቃወሙ ብቻ አሸባሪ ማለቱ አስነዋሪ ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ፍርድ ተጓደለ ብሎ ሊነሳና ሊሟገትላቸው ይገባል”
ሌላው አስተያየት ሰጪ ደግሞ “እነ እስክንድር ነጋ የሕሊና እስረኞች እንጂ አሸባሪዎች አይደሉም:: ፍርድ ቤቱ ይህን አይን ያወጣ ፍርድ እንደሚሰጥ ቀድሜ አውቄዋለሁ። ለምን እስካሁን ፍርዱን ማጓተት እንዳስፈለገውም አልገባኝም” ብለውናል።



Thursday 12 July 2012

African migrants sailing to Italy ‘die of thirst


BBC
Fifty four people have died while trying to sail from Libya to Italy in an inflatable boat, the United Nations refugee agency has said.
The only survivor, found by Tunisian fishermen, said the others had died of dehydration during a 15-day voyage.
He told UNHCR officials that they nearly reached the Italian coast, but were driven back by strong winds, and the boat then began to deflate.
Most of the passengers are thought to have been from Eritrea.
The survivor, also an Eritrean national, was rescued by fishermen off the Tunisian cost and is now being treated in a Tunisianhospital.
He told the UNHCR that the group of 55 people left Libya towards the end of June.
“He told us that there were immediately problems on the boat, that unfortunately they weren’t even allowed to take a bottle of water and so once they got lost and the voyage went on, people started to feel unwell and die because of the lack of water,” UN spokeswoman Laura Boldrini told Italy’s SkyTG24 TV.
According to the UNHCR, around 170 people have died this year trying to reach Europe from Libya.
An estimated 1,300 have reached Italy by sea since the beginning of 2012.
Many Eritreans attempt risky journeys to reach Europe or Israel in search of better opportunities.
Critics say they are fleeing the country’s repressive government, poverty and national service for men until the age of 40

የታሰሩት የዋልድባ መነኮሳት የት ገቡ!?





በ1998 ዓ.ም አካባቢ ከጓደኞቼ ጋር ሆኜ፤ ለአንድ ስታስቲክሳዊ ስራ ወደ ወደ አርማጭሆ አካባቢ ሄጄ ነበር። በወሬ ደረጃ ስንሰማው የነበረ “አርበኞች ግንባር” በመባል የሚታወቅ የታጠቀ ቡድን እዚህ አካባቢ “በህይወት” መኖሩን ሰማሁ። ለስታስቲክሳዊ ስራው የገጠሩን መንደር መንገድ እንዲመሩን የተመደቡልን የመንግስት ታጣቂዎች ነበሩ። እኔ እና ሌሎች ከአዲሳባ ለስራ ወደ እዚህ የመጣን ልጆች ስለ አርበኞች ግንባር በደንብ ለማወቅ ጉጉት አድሮብናል። ነገር ግን የመንግስት ታጣቂን ስለ ተቃዋሚ ለዛውም ስለ ሸማቂ ሃይል መጠየቅ እየፈራን እየተባን በአካባቢው ስለሚኖሩ ሽፍቶች በመጠየቅ እናሟሙቅ ጀመር።

የታሰሩት የዋልድባ መነኮሳት የት ገቡ!?

“እዚህ አካባቢ ሽፍታ አለ ይባላል እውነት ነው?”  አልነው አጃቢያችንን፤

“እንዴ ጋሼ ሽፍታማ ሃገሩ ነው!” አለን በኩራት። (በነገራችን ላይ አርማጭሆ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ያሉ ክፍለ ሀገሮች ቢሄዱ በእድሜ የሚበልጥዎም ሰው እንኳ “ጋሼ” ብሎ በአክብሮት ነው የሚጠራዎት። እናውቃለን ባክህ… ካሉኝ “እኮ…” ብዬ ቀጥላለሁ!)
ጥያቄያችን ቀጥሏል።
“ሰዉ ምን ሆኖ ነው የሚሸፍተው…?” አልነው።
“ሰበቡማ ብዙ ነው ምሰሌ፤ በመንደር ግጭት የተጠቃ እንደሆነ፤ አኩርፎ ጥቃቱን ለመወጣት ይሸፍትና በዛው ሽፍታ ሆኖ የሚቀር አለ…” ልክ ይህንን ምላሽ እንደሰማሁ፤ መቼም ያን ጊዜ ቀልጣፋ ነበርኩ፤ ለማወቅ ወደፈለግነው ዋና ነጥብ ቀልጠፍ ብዬ ገባሁ፤
?“በመንግስት ላይ አኩርፎ የሚሸፍትስ የለም?” ብዬ ጠየቅሁ…!

ይሄኔ መንገድ መሪያችን የመንግስት ታጣቂ ያነገታትን አሮጌ ክላሽ ከፍ ከፍ እያደረገ፤
“እሱማ ምን ይጠፋል!?” ብሎ በጥርጣሬ እያየን ዋናው ጨዋታችንን በአጭሩ ሊቀጨው ፈለገ። ስለ አርበኞች የማወቅ ጉጉት የሁላችንም ነበርና አንዱ ወዳጃችን፤

“አርበኞች የሸፈቱት በመንግስት ላይ አኩርፈው አይደል እንዴ!?” ብሎ ሌላ ጠቋሚ ጥያቄ አመጣ። በሆዳችን ጎ…በዝ ብለን ወዳጃቸንን አደነቅን!

የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በዝናብ ተጥለቀለቀ


የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ በዝናብ ተጥለቀለቀ

በዝናብ ተጠለቀለቀ

ከፍተኛ ወጭ ተመድቦለት ግንባታውም በዚህ አመት የተጠናቀቀው እና ምርቃቱም በታላላቅ የአፍሪካ መሪዎች ባሉበት ተመርቆ በስራ ላይ የዋለው የአፍሪካ ህብረት ማእከል በትላንትናው እለት ምሽት በጣለው ከፍተኛ ዶፍ ዝናብ የህብረቱ አዳራሽ መጥለቅለቁ የደረሰን ዜና ዘገባ ያመለክታል ። ከ$200፣000 የአሜሪካን ዶላር ያወጣው እና የቀድሞውን ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ሃይለስላሴ ዘ-ኢትዮጵያ መሰረታዊ ታሪክ ያጠፋ ከመሆኑም በላይ በመታሰቢያነት ከታሰበ ሊሰራላቸው ከሚገባቸው የሚገባው ሰዎች መካከል ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ፣የኬንያው ጆሞ ኬኝያታ  እና የግብጹ ጋማል አብዱል ናስር መሆን ሲገባቸው በምትኩ የአፍሪካ የአንድነት ታጋይ ተብለው የተሰየሙት“  በአፍሪካ አንድነት ከፍተኛ ትግል ላደረጉት በዶ/ር  ክዋሚ ኑክሩማህ” ስም ሃውልት ተሰርቶ መታሰቢያ እንዲሆነላቸው የተደረገው ይሄው ሃውልት በቻይናውያን ትብብር ተሰርቶ መጠናቀቁን ባለፈው ጃንዋሪ 28 ቀን 2012 የቻይናው የፖለቲካ አድቫይሰር  ጂያ ቂንጊል   በተገኙበት ተመርቆ ለስራ መብቃቱ ይታወሳል ::

Wednesday 11 July 2012

BERKELEY, CALIFORNIA — Next time I travel to Ethiopia, I may be arrested as a terrorist. Why? Because I have published articles about Ethiopian politics.


Supporting Stability, Abetting Repression

BERKELEY, CALIFORNIA — Next time I travel to Ethiopia, I may be arrested as a terrorist. Why? Because I have published articles about Ethiopian politics.

I wrote a policy report on Ethiopia’s difficulties with federalism. I gave a talk in which I questioned Ethiopia’s May 2010 elections, in which the ruling EPRDF party (Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front) won 545 out of 547 seats in the Parliament. As part of my ongoing research on mass violence in the Somali territories, I interviewed members of the Ogaden National Liberation Front, a separatist rebel group in eastern Ethiopia that the government has designated as a terrorist organization.

In the eyes of the government of Prime Minister Meles Zenawi, my work is tantamount to subversion. Not only do his officials have zero tolerance for criticism, they consider people who either talk to or write about the opposition as abetting terrorists.

ሌላኛዋ ዓለም ደቻሳ በሳዑዲ አረቢያ ፖሊስ ስትሰቃይ፤ እኛ ስንዋረድ የሚያሳይ ቪድዮ ተሰራጨ




Wednesday, July 11th, 2012 | Posted by zehabesha

(ዘ-ሐበሻ) በሊባኖስ ተሰቃይታ ለህልፈተ ሞት የበቃችው የዓለም ደቻሳ ሃዘን ሳይለቀን ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊትን የሳዑዲ አረቢያ ፖሊሶች ሲያሰቃዩአት የሚያሳይ ቪድዮ በዩቲዩብ በኩል ተለቀቀ። ከአሰሪዎቿ ስቃይ አምልጣ ለመሄድ ስትል፤ አሰሪዎቿ ለፖሊስ እንደጠቆሙ የገለጸው ከሳኡዲ የመጣው የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ሪፖርት ፖሊስ ልጅቷን በ እጁ ሲያስገባ ልክ እንደ እንስሳ መኪና ውስጥ ለመጫን ክብሯን በመዳፈር ሲያሰቃዩአት ቪዲዮው ያሳያል። በኃይለ ሥላሴ ዘመን የሳዑዲ መንግስትም ሆነ ሕዝቡ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ክብር እንደነበረው ታሪክ ያወራ ነበር። አሁን ግን ኢትዮጵያውያን በየቦታው እየተዋረዱ ይገኛሉ። በሳዑዲ እስር ቤት ብቻ አልፎልኝ ቤተሰቦቼን አሳልፋለ ብለው ከሃገር የወጡ ኢትዮጵያውያን በሺህዎች ይቆጠራሉ። የአ ዕምሮ በሽተኛ የሆኑ፣ የታመሙ፣ ተገደው የተደፈሩ ሴት እህቶቻችን ቁጥር ብዙ ነው። የሳዑዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያዊቷን ሲያሰቃዩዋት የሚያሳየው ቪድዮ እጃችን ገብቷል። የ እህታችንን ማንነት ዘ-ሐበሻ እያጣራች ነው።
ላልሰማ አሰሙ፤ እንጩህ፣ እንደ ኢትዮጵያዊ ክብራችንን ለማስመለስ እንነሳ!!
>


ወንጀለኛው የመለስ አጃቢ


– (ከኢየሩሳሌም አርአያ)


ከኢትዮ ሚዲያ የምርመራ ዝግጅት ክፍል ጋር በመተባበር ሕወሐት/ኢሕአዴግን የሚመለከቱ መረጃዎች በተከታታይ ይቀርባሉ። የዛሬው ጥንቅር እነሆ፦
አቶ መለስ ዜናዊ በሚደረግላቸው የተጠናከረ ልዩ የጥበቃ እንቅስቃሴ ውስጥ አዘውትሮ የማይጠፋ ሹም አለ። መለስ ከቤተ መንግስት ሲወጡም ሆነ ሲገቡ ከሚንፈላሰሱባቸው አሜሪካ ስሪት ዘመናዊ ካዲላኮች ፊት ለፊት ነጭ የፖሊስ ሞተር ሳይክል መንገዱን እየመራ ይጏዛል። ብዛት ያላቸው ሞተረኞች ከጎንና ጎን ሆነው ይከተላሉ።
መልኩ ጥቁር፣ፀጉሩ ከርዳዳ፣ጥቁር መነፅር የሚያዘወትር፣ፊቱ የማይፈታና አስፈሪ ነው። ሲናገር ቁጡና ድምፀ ጎርናና ነው። ሻምበል ታዬ ኡርጂ ይባላል። በደርግ ዘመን መቶ አለቃ የትራፊክ ፖሊስ ሞተረኞች ዋና አዛዥ፣ በመሆን በሁለቱ ስርአት ሁለቱንም መሪዎች እያገለገለ ይገኛል።
ፈረንሳይ ለጋሲዮን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ጀርባ የገነባው መኖሪያ ቤት ይገኛል። ሰኔ 1990 ዓ .ም ሻምበል ታዬ እስር ቤት እንዲገባ ተደረገ። ከታላቁ ደራሲ በአሉ ግርማ ግድያ ጋ በተያያዘ «እጁ አለበት» ተብሎ ነበር የታሰረው። የደርግ ባለስልጣናትን ጉዳይ ይመለከት በነበረው የስድስት ኪሎ ጠ\ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ተደረገ።
«ቀኑና አመቱን በውል አላስታውሰውም» ሲል ለችሎቱ ንግግር የጀመረው ተከሳሹ፣ የቃሉ አጠቃላይ ጭብጥ ሲጨመቅ ይህን ይመስል ነበር።

Tuesday 10 July 2012

ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?


ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?
ትላንት ሐምሌ 2/ 2004 ዓ.ም ታዋቂው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ኬኒያ በሚገኘው ኤርትራ ኤንባሲ መታየቱን ናይሮቢ የሚገኙ ኤርትራዊ ወዳጆቼ ነገሩኝ። ኃይሌ ገብረስላሴ ኤርትራ ኤንባሲ ምን ይሰራል!?

በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት የጭምጭምታ ወሬዎችን መናቅ አይገባም። ከዚህ በፊት ራሱ ኃይሌ ገብረስላሴን ጨምሮ ሌሎችም ራሳቸውን “ሽማግሌ” ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች ተሰባስበው በቃሊቲው እስር ቤት ሲመላለሱ ነበር። የሚል ጭምጭምታ በሰማን በማግስቱ ነው ነገሩ ሽምግልና መሆኑ የተሰማው። ማን ያውቃል አሁንም ኃይሌ ኤርትራ ኤንባሲ በታየ በነጋታው አቶ ኢሳያስ እና አቶ መለስ ሊሸማገሉ ነው የሚል ዜና እንሰማ ይሆናል።

እንግዲህ ዝርዝሩን ወደፊት የምንሰማው ቢሆንም፤ ለጊዜው ግን እኔ ነገር መደበቅ አይሆንልኝምና እንሆ ሹክ ብያችኋለሁ። ኃይሌ ገብረስላሴ  በኤርትራ ኤንባሲ ትላንት ታይቶ ነበር። መቼም “የኢትዮጵያ ኤምባሲ መስሎኝ ነው” አይለንም። ታድያ እንዴት እዛ ሊገኝ ቻለ?

ይቺን ያህል እኔ ወሬ ካቀበልኩ፤ እንዴት? ለምን? ከየት? ወዴት? የሚሉትን  ጠለቅ ያሉትን ግምቶች ለፕሮፌሽናል ገማቾች እንተዋለን!

ኃይሌ ገብረስላሴስ የተመለከቱት ወዳጆቼ ጠርተው ሰላምታ ሰጥተውት እሱም “ታድያስ ሰላም ናችሁ” ብሎ አፀፋውን የሰጣቸው ሲሆን ከሁለት አማርኛ ተናጋሪ ሰዎች ጋ እንደነበረም ሹክ ብለውኛል!

Breaking News: The real possibility of Zenawi dying from blood cancer and a state of shock and fear ripping through the weyane ruling circles


Ethiopia: The real possibility of Zenawi dying

by K.B

As you know, Meles Zenawi’s days are numbered. His death from blood cancer is becoming more certain day by day. He will soon face his Maker as soon as he steps into eternity. Then, Zenawi is also going to face the music. With no agazi nor federal police behind him. It is going to be one on one with the almighty God. Is he ready for his answer?

As a result, shock and terror is ripping through the ruling Weyane circles especially among those on high profile positions of power in the TPLF hierarchy. It has been reported that quite of a few of them are preparing for the worst scenario of an uprising after Zenawi’s death. Many are already in a rush sending their money overseas in hard currency to the United States, London, and Indonesia. According to reliable sources, exit strategies for families and friends of the ruling weyane circles are already on the works for the last three or four weeks. Some are even selling a few of their properties and investments.

ይዞህ ይሂድ ከመባል ያድናችሁ




ዳኛቸው ቢያድግልኝ

ይህ ጽሁፍ የተንደረደረው ሰሞኑን በተለያዩ ድህረ ገጾች፣ ፓልቶክና ሰሞነኛ የቡና ወሬዎች ላይ የኢትዮጵያ አውራ ነኝ የሚሉትና ፓርቲያቸው እያስገደደ ስልጣን ላይ ያቆያቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ህመም አስከትሎ በሚሰነዘሩ አስተያየቶች መነሻነት ነው። የሰው ልጅ ጥላቻ እዚህ ጥግ ድረስ ደርሶ በእግዜር ይማረው ምትክ ይዞት ይሂድ የሚሉ አስተያየቶች በዝተው ሳይሆን ተትረፍርፈው ማየቴ አሳስቦኝ አብረዋቸው ላሉ ለታመሙና ገና ላልታመሙ ሁሉ ይዞህ/ሽ ይሂድ ከመባል ያድናችሁ በማለት ወገናዊ አሳቤን ማቅረብ ከዝምታ ይሻላል በማለት ነው። እግረመንገዴንም ነገ የሚሆነው እያሳሰበኝ ዛሬን ካላወቃችሁበት ነገ የናንተ አይደለምና ምርጫችሁን አስተካክሉ ለማለት ነው። አባ ጳውሎስ አሉላቸውና የኔ እግዜር ይማሮት ግን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አይጠቅምም። ሰው ናቸውና አፍረውም አንገት ደፍተውም ወደ አፈር መመለሳቸው እውነት ቢሆንም የምትማር ነብስ ካለቻቸው በፈጣሪ ስራ ውስጥ አኔ አልገባም።

የሰው ልጅ ነብሱ ከስጋው የመለየት ምጥ ውስጥ ስትገባ እግዜር ይማረው/ራት ማለት ባሕላችን ነው። ሰብዓዊነት በራሱ ሞትን እንደዚህ አድርገን እንድናየው ያደረገን ህልፈቱ የስጋዊ ማንነት መጨረሻና መመለሻ የሌለው ነገር ስለሆነ ነው። ሟች ቀሪ ቤተሰብና ቤተዘመድ ይኖረዋልና የነርሱንም ጥልቅ ሀዘን በማሰብ ሞት ላይ ጨከን የሚል ጥቂት ነው። ያ ጭካኔ የሚታየው ፍልሚያ ላይ ከሆነ፣ ጦርነት ላይ ከሆነ ነው። ሰው በመሰሪነቱ ረቅቆ፣ በአፍራሽነቱ ልቆ፣ በአስገዳይነቱና በልቅ አንደበቱ ታውቆ በዚህ ምድር ከተመላለሰ የሞተው ከፍጥረቱ በፊት ነውና በስጋ መለየቱ ማንንም አይቆረቁርም። የመለወጥ እንጥፍጣፊ ተስፋ የለውምና እንዲያውም ይዞት ይሂድ ይባላል። እንዲህ የሚባሉ ሰዎች በተለይ መሪዎች እጅግ ብዙ አይደሉም። በዘመናችን እንዲህ ከተባሉ ሰዎች ውስጥ የቅርቡ ሰው ቢኖር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና በዙርያው ያሉ ታማሚዎች ናቸው።

Monday 9 July 2012

ጸሐዬ ዮሐንስ የኢትዮጵያ ባንዲራን ይዞ መድረክ ላይ አለቀሰ



ጸሐዬ ዮሐንስ የኢትዮጵያ ባንዲራን ይዞ መድረክ ላይ አለቀሰ

(ዘ-ሐበሻ) ውድ አንባቢዎች ከዳላስ ያገኘናቸውን መረጃዎች በየሰዓቱ ወደናንተ በቪድዮ እያደረስን ነው። አሁንም አዲስ ነገር አግኝተን ልናካፍላችሁ ነው። ተወዳጁ ድምጻዊ ጸሐዬ ዮሀንስ በዳላስ በተደረገው የኢትዮጵያውያን ስፖርትና ባህል ፌስቲቫል ላይ በመገኘት በሕዝብ ዘንድ ክብርን ከተጎናጸፉ በርካታ አርቲስቶች መካከል አንዱ ነው። ጸሐዬ አርብ እለት በኢትዮጵያን ቀን ላይ እንዲሁም ቅዳሜ በመዝጊያው ምሽት ላይ “እምዬ ኢትዮጵያ እንዲህ ሆና አትቀርም” የሚለውን ዘፈኑን አቅርቦ ነበር። በመዝጊያው ዕለት በተመልካቹ የኢትዮጵያ ባንዲራ ልክ ‘እምዬ ኢትዮጵያ እንዲህ ሆና አትቀርም” የሚለውን ዜማ ሲጫወት ተሰጠው። ጸሀዬ ዘፈኑን እየዘፈነ እምባውን መቆጣጠር አልቻለም። ባንዲራውን በ እጁ ይዞ እያለቀሰ ዘፈኑን ለመጨረስ ተገዷል። በርከት ያሉ ተመልካቾችም ስሜታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ሲያለቅሱ ነበር። የእምዬ ኢትዮጵያ ፍቅር አይደለም እምባ ደም ያስፈስሳል። የጸሐዬን ለባንዲራው ያለውን ፍቅር ብዙዎች በአድናቆት ሲያወሩበት ነበር። ጸሐዬ በኢትዮጵያን ቀን ላይ የዘፈናት “እምዬ ኢትዮጵያ እንዲህ ሆና አትቀርም” ዜማ በዘ-ሐበሻ ቪድዮ ተይዛለች፤ ይመልከቷት። ጸሐዬን እናመሰግናለን።




Ethiopia – Meles Zenawi and his health




Monday, July 9th, 2012 | Posted by zehabesha
Ethiopia – Meles Zenawi and his health
Share

By Yilma Bekele
Ato Meles Zenawi, Chairman of Tigrai People Liberation Front (TPLF) and Prime Minster of the Federal Democratic
Republic of Ethiopia is not in good health. I became aware of that fact after watching the video of a news clip made during his meeting with the President of China at the G8 meeting in Mexico. The last time we saw Ato Meles was during President Obama’s food conference and he was in perfect health. In fact he looked jovial with a new haircut and was dressed in his customary five to ten thousand dollars Italian or English suit. That was until Ato Abebe Gelaw of Ethiopian Satellite Television (ESAT) gave him the scare of his life and he was forced to flee the continent. Things have not been the same ever since.
When he surfaced in Mexico it was obvious he had some medical issues in the interim period. His expensive clothes did not fit him right, his face was ashen and hollow and it was clear he has lost plenty of weight. I was forced to conclude we got a problem. Normally the fate of one individual should not be such a source of drama or wild speculations. But Ato Meles is not just another Ethiopian. He is the Country, Nation and people all rolled in one. The state of his health and well-being is not just idle speculation. His friends, Party or those close to him are not forthcoming with the cause of his illness. We are left to speculate, guess or are being forced to search for a fortuneteller and reduced to read the remains of his coffee cup or consult a palm reader.

እንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስቲያን--ከሰንሰለቶቹ በስተጀርባ


እንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስቲያን--ከሰንሰለቶቹ በስተጀርባ
የአእምሮ ሕሙማኑን ለሁለት ለሁለት እያደረጉ በሰንሰለት አስረው ወደ ፀበሉ ስፍራ ማድረስ የዕለት ተዕለት የማለዳ ሥራቸው ነው፡፡

ለሕሙማኑ ማጠቢያና ምግብ ማብሰያ የሚያገለግለውን ውሃ ከእንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ከሚገኘው ምንጭ በጀሪካን ለመቅዳት ከምሽቱ አራት ሰዓት እስከ እኩለ ሌሊት ባለው ጊዜ መውጣት ደግሞ ሌላው ኃላፊነታቸው ነው፡፡ ሕሙማኑ ራሳቸውን የማያውቁ ከመሆናቸው የተነሣ በቤተ ክርስቲያኒቷ አካባቢ ከተከራዩላቸው ቤት ውስጥ የተፀዳዱትንና ያበላሹትን መጥረግ፣ ሕሙማኑን ማጠብ እንዲሁም የተበላሹ ልብሶቻቸውን ወንዝ ውስጥ ማንጨፍጨፍ የሥራቸው አካል ነው፡፡

ወደ ፀበል ስፍራ ሲሔዱ በአካባቢው ያገኙትን እንዳይመቱ፣ ከተመለሱ በኋላ ደግሞ በተከራዩላቸው ቤቶች አካባቢ የሚገኙትን ሰዎችም ሆነ እንስሳት እንዳይደበድቡና እንዳይጐዱ መቆጣጠርም ይጠበቅባቸዋል፡፡ የሚኖሩበትን ቤት ግድግዳ እንዳይቆፍሩና እንዳይፈነቅሉ መጠበቅም እንዲሁ፡፡ ያም ሆኖ ግን ዶሮ ጠምዝዞ የሚገጽል፣ እንስሳ የሚያሳድድ፣ ሰው የሚደበድብ፣ የያዙትን መንጥቆ የሚያበላሽ ምግብም ከሆነ የሚበላ ውኃም ሆነ ዘይት ድንገት ቀምቶ የሚጠጣ መኖሩ አልቀረም፡፡ የአእምሮ ሕሙማኑ ይህንን ሁሉ የሚያደርጉት በሰንሰለት ባልታሰሩበት ወቅት ነው፡፡ ለሁለት ለሁለት በመሆን እጅና እጃቸው በሰንሰለት የታሰሩት የአእምሮ ሕሙማን እጃቸው ከሰንሰለቱ ከተፈታ ምድር አትበቃቸውም፡፡ በአንድ በኩል ደስታቸውን በሌላ በኩል ጉልበታቸውን ያሳያሉ፡፡

“የኢትዮጵያ አንድነት ለዘላለም ይኖራል”


Sunday, July 8th, 2012 | Posted by zehabesha
“የኢትዮጵያ አንድነት ለዘላለም ይኖራል” – አርቲስት ማህሙድ አህመድ
37
Share
(ዘ-ሐበሻ) የትዝታው ሙዚቃ ንጉሥ ማህሙድ አህመድ በዳላሱ የኢትዮጵያውያን የ እግርኳስ ውድድር ላይ በመገኘት በኢትዮጵያን ቀን ላይም እንደዚሁም በመዝጊያውም እለት ድንቅ ብቃቱን ያስመሰከረበትን የሙዚቃ ሥራዎቹን ለሕዝብ አቅርቧል። በዳላሱ የእውነተኞቹ ኢትዮጵያውያን ስፖርት በዓል ላይ በመገኘትም ከሕዝብ ክብርን አግኝቷል፡፤ ድምዳዊው ዘፈኖቹን አቅርቦ ሲጨርስ የብሄራዊ ስሜትን በሚያነቃቃ መልኩ የተናገራቸው ንግግሮች በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ አድናቆትን አግኝቷል። “ኢትይጵያ ለዘላለም ትኑር፤ የኢትዮጵያ አንድነት ለዘላለም ይኖራል” ሲል ተናግሯል። ቀጣዩ ቪድዮ ይህንን ያሳየናል። ዘፈኑን ዘፍኖ ሲጨርስ ንግግሩን ያድምጡት። ቪድዮውን የቀረጸው የዘ-ሐበሻ ድረገጽ ዋና አዘጋጅ ሔኖክ ዓለማየሁ ነው። መልካም እይታ፡ ማህሙድን ለወርቃማ ቃላቶቹ እናመሰግናለን።




“እናቴ እጄ ላይ ነው በጥይት ተመትታ የሞተችብኝ” ” ” ዝነኛው ተወዛዋዥ አብዮት ደመቀ

(ዘ-ሐበሻ) – ዝነኛው የቀድሞው የሃገር ፍቅር ተወዛዋዥ እና የውዝዋዜ አሰልጣኝ አብዮት ደመቀ ወደ አሜሪካ መጣ። በመጣ በሁለተኛው ቀንም ዳላስ በተደረገው የኢትዮጵያውያን የ እግርኳስ እና የባህል ዝግጅት ላይ ተገኝቶ የኢትዮጵያውያን ቀን አርብ ጁላይ 6 ቀን 2012 ሲከበር ‘ለኢትዮጵያ ሕዝብ የምናገረው አለኝ’ በሚል በእናቱ ላይ የአቶ መለስ ወታደሮች የፈጸሙትን ግድያ በአደባባይ ተናግሯል። “በቅድሚያ ከእናንተ መካከል ዛሬ እንድገኝ ላደረገኝ እግዚአብሄር፤ እመብርሃን ምስጋና ይድረስ።…ካእናቴ በጥይት ተመትታ የሞተችው እጄ ላይ ነው” ሲል አጋልጧል። “የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳም እንደሚባለው” በ1993 ሚያዝያ 10 በአራት ኪሎ አደባባይ በአብዮት እናት ላይ ይህን ድርጊት የፈጸሙ ደም ያለባቸው ሰዎች ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲው የአላሙዲ (ወያኔ) ስፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዲካፈል መጠየቃቸው እንዳስገረመው መድረክ መሪው አበበ በለው ተናግሮ ነበር። እኛ ከምንገልጸው ዘ-ሐበሻ ከስታዲየሙ ውስጥ ሆና የቀረጸችው ቪድዮው ትናገር።



‹‹ይቅርታ›› የኢህአዴግ ቃጭል? ወይስ…



‹‹ ከተመስገን ደሳለኝ


አዲስ አበባ በለውጥ ፍላጐት ከአፍ እስከ ገደቧ ታጥናለች። እዚህም እዚያም የፖለቲካ ወግ ይጠሰቃል። በቡድን ሆነው፣ በስሜት ተውጠው በፖለቲካ ጉዳይ የሚከራከሩ በርክትዋል፡ ፡ ለዓመታት የፖለቲካ ጉዳይ ‹‹ፆም›› የሆነባቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሳይቀሩ ጎራ ለይተው በሚከራከሩ ሠራተኞቻቸው ተፈስገዋል፡፡ ‹‹ቅንጅቱ መንግሥት ለመመስረት የሚያስችል ድምፅ አግኝቷል›› ይላል አንዱ። ‹‹ቢሆንም ኢህአዴግ ይገግማል!›› ሲል ይመልሳል፤ ኢህአዴግ በምርጫ ስልጣን አይለቅም የሚል አቋም ያለው ተከራካሪ፡ ፡
…የጋዜጦች እትሞች ከምርጫው በፊት ከነበረው ቅጂ ከሶስት እስከ አምስት እጥፍ ድረስ ጨምረዋል። ማንበብ የሚችለውም፣ ማንበብ የማይቻለውም ቋሚ የጋዜጣ ሸማች ሆኖአል-እድሜ ለምርጫው። በኢትዮጵያ ‹‹መንግሥት…›› ሲባል የተቃወመውን በሙሉ የሚገድል እንደሆነ ከልምድ የተገነዘቡ ወላጆች ለልጆቻቸው በመስጋታቸው ጭንቀታቸው ጨምሯል፡ ፡ እነዚህ ኩነቶች የድህረ ምርጫ 1998 ዓ.ም. ዋነኛ መገለጫዎች ነበሩ፡፡
እንዲህ ውጥረት በነገሠበት አንድ ቅዳሜ ከቅንጅቱ ዋነኛ አመራሮች አንዳቸውን በአካል ልተዋወቅ ወደ ቀጠሮ ቦታ እየሄድኩ ነው-መስከረም 28 ቀን 1998 ዓ.ም.፡፡ በምርጫው ላይ የጎላ ተሳትፎ የለኝም። የየትኛውም ፓርቲ አባል አይደለሁም። ድምፄንም ለማንም አልሰጠሁም። ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ እልፍ አእላፎችን ከጎኑ ማሰለፍ ከቻለው ‹‹ቅንጅት›› መሪዎች አንዳቸውን ልተዋወቅ ነው። የሚያስተዋውቀኝ ደግሞ በእጅጉ የማከብረውና የማደንቀው የጋራ ወዳጃችን አብይ ተክለማርያም ነው። ያኔ ተወዳጇ አዲስ ነገር ጋዜጣ አልተመሰረተችም። አብይ የሚያዘጋጃት ‹‹መዝናኛ›› የተባለች በድህረ ምርጫ እየገነነች የመጣች ጋዜጣ ግን ነበረች። ቀጠሮአችንም ጋዜጣው ቢሮ ውስጥ ነው። ልተዋወቅ እየሄድኩ ያለሁት የቅንጅቱ ምክትል ሊቀመንበር ሆና ከተመረጠች 14 ቀናት ብቻ ካለፋት ከብርቱካን ሚደቅሳ ጋር ነው፡፡ (እርግጠኛ ባልሆንም ብርቱካን ቀድማኝ የደረሰች መሰለኝ)