"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 6 February 2014

በአዲስ አበባ የ“ዳይመንድ ድራማ” ተጧጡፏል!


ኔትዎርክ ያቆማል የተባለው የ“ማሾ ዳይመንድ” 4ሚ. ብር ተሸጧል
የዳይመንዱን ትክክለኛነት የሚያረጋግጡት “የውጭ ኤክስፐርቶች” ናቸው
ባለሃብቶች የሚጭበረበሩት በሚያውቋቸውና  በቅርብ ባልንጀሮቻቸው ነው
በአዲስ አበባ የሚኖሩት አቶ አየለ ጣፋ እና አቶ ጎሽሜ ሁንያንተ የልብ ጓደኛሞች ሲሆኑ ሁለቱም በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ አቶ ጎሽሜ ለበርካታ አመታት በጣሊያን ኖረው ነው ወደ አገራቸው የተመለሱት፡፡ አቶ አየለ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ከውጭ እያስመጡ የሚሸጡ ሲሆን ልጆቻቸውም በስራቸው ያግዟቸዋል፡፡
ከጥቂት አመታት በፊት አቶ አየለ ሰሚት አካባቢ መኖሪያ ቤት ሲገዙ፣ የልብ ጓደኛቸው አቶ ጐሽሜ አለኝታነታቸውን የገለፁት የ300ሺ ብር ስጦታ በማበርከት ነበር፡፡ ትንሽ ቆይተው ታዲያ ውለታ ጠየቁ - አቶ ጐሽሜ፡፡ በእርግጥ ውለታው ከባድ አልነበረም፡፡ ዘቢደር የተባለች ዘመዳቸው አቶ አየለ ቤት፣ በቤት ሠራተኛነት እንድትቀጠር ነው የፈለጉት፡፡
አቶ አየለም፤ “አንተ ብለህ ነው?” በማለት ዘቢደርን ለሌሎች ሠራተኞቻቸው ከሚከፍሉት ደሞዝ በእጥፍ ቀጠሩላቸው፡፡ 300ሺ ብር በስጦታ ላበረከተ ለጋስ ጓደኛ ይህቺ ምን አላት! አቶ አየለ አንድ ሴራ እየተጐነጐነላቸው መሆኑን ግን አላውቁም፡፡
የአቶ ጐሽሜ ዘመድ ናት የተባለችው ዘቢደር፣በእንክብካቤ አንድም ነገር ሳይጐድልባት አቶ አየለ ቤት ለአንድ ዓመት ቆየች፡፡ ዋና ተልዕኮዋ የሚጀምረውም ከዚህ በኋላ ነው፡፡ አጐቴ የምትላቸው አቶ አጐናፍር (ዋና ስማቸው መኮንን ሃብታሙ) ከገጠር “ሊጠይቋት” ይመጣሉ፡፡ አመጣጣቸው ግን ለሌላ ነበር፡፡