"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 19 December 2013

ምስጋና ለአያሌው ጎበዜ – አክባሪዎ አቢሲኒያዊ

አያሌው-ጎበዜእርስዎ ብዐዴን/ህወሀትን ወክለው የአማራን ህዝብ ሲመሩ መቆየትዎ ይታወቃል በዚህም የክልሉ ህዝብ ኤያሌው ጎበዜ     ለዘላለም ይኑር እያለ እንዲኖር ማድረግዎትን
                                                                                                                  የሚያስታውሱት ነው   ደመቀ መሬቱን ድንጋይ ያድርግለት እና በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ይገባሻል ብሎ መለስም ብራቮ እንዲህ ነው እንጂ ተላላኪ ብሎ ትምህርት ሚኒሰቴር ሲያደርገው ለእርስዎ ግን ቅንጣት ታህል አለመስጠቱ ሱዳኖች እንኴን እንዲታዘቡት አድርጔል፡፡
እርስዎም ደመቀ ምክትል ጠ/ሚኒስቴር ሲሆን ቅናት ቢጤ አድርዎቦት ከሳምንታት በፊት 40 ካ.ሜ ወደ ኢትዮጵያ ገብተው የሀገሮትን መሬት ለሱዳን ማስረከብዎን ሰምቼ ድሮስ የጎበዤ ልጅ ከማን ያንሳል ብዬ ኮራሁ፡፡ በነገራችን ላይ ሰሞኑን መሬታችን ለሱዳን መሰጠቱን ተከትሎ የእርስዎ የቅርብ ዘመዶች ቤታቸው የተሸጠው መሬት ላይ በመገኘቱ ሱዳን ለዘላለም ትኑር አባይ የሱዳን ነው እያሉ መዘመራቸውን ሱዳን የሚገኝ ወዳጄ ሹክ ብሎኛል፡፡
እናማ ይሄውልዎ ተሰናባች አያሌው የእርስዎ ክልል ግዞት የሆነው የአማራ ህዝብ ብዙ እየሰማ እና እየተሰማው ሲኖር አንድም ቀን ተናግርዎት አያውቅም ለምን መሰለዎት ምን አልባት ነጋዴው ክልሉን ለሱዳን ሸጠው ከመለስ ዜናዊ አገዛዝ ነፃ ያወጡናል ብሎ ስላሰበ ይሆናል፡፡ የአማራ ክልል ህዝብ ለእርስዎ ያላቸውን ፍቅር የተረዳሁት ጉራፈርዳ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ጉራፈርዳ በቃን አያሌው ጎበዜ ናፈቀን ብለው ቢለመኑ እምቢኝ ብለው እርስዎ ክልል ሲመጡ ነው፡፡
እናም በመጨረሻም እንኩ ምስጋናዬን ተቀበሉ
1.   ሰፊውን መሬታችንን ሽጠው ጠጋ ጠጋ ብለን በመኖር ማህበራዊ ህይወታችን እንዲጠናከር በማድረግዎ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
2.   እንደ መለስ ዜናዊ ስልጣን ላይ ሳይሞቱ በመልቀቅዎ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
3.   በ1998 በኮምቦልቻ፣ በ1999 በደሴ፣ በ2000፣ በ2003 የጎንደር እና የጎጃም ህዝብን በወያኔ ወታደሮች በጥይት አስገድለው ከዘንድሮው የኑሮ ውድነት እንዲያመልጡ ስላደረጉ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
አክባሪዎ ሁኔ አቢሲኒያዊ
ከፒተርቦሮው ዩ.

Saturday 12 October 2013

“አውጣኝ ያለም ወጣ አብላኝ ያለም በላ፣ምስኪኑ ጥንቸል ግን ተኝቶ ተበላ”

 
(ቴዲ - ዘአትላንታ)
ዕውቀት ጥራዝ ነጠቅ ከሆነ አስቸጋሪ ነው። ከጥራዝ ነጠቅ ሰው ጋር መከራከርም አይቻልም፣ ለሱ እሱ ልክ ነው፣ ምክንያት አምጥቶ፣ ብልት አውጥቶ አይከራከርም - የሚያውቀው ትችት ብቻ ነው። ጥራዝ ነጠቅነት ከስሜታዊነት ጋርም ይያያዛል። እንዲህ አይነት ሰዎች ፌስ ቡክ ላይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ቦታ አሉ - ይኖራሉም።

ሰሞኑን ከዚሁ ዓይነት ጥራዝ ነጠቅነት የመጣው ሃሳብ “ለኢትዮጵያ ለምን ይጸለያል - ናይጄሪያም እኮ አምላክ አለው” የሚል ነው። እንዲህ ዓይነት አስተሳስብ ጥራዝ ነጠቅነት ይባላል - አንዲት ነገር ፣ በአንዲት ጎን እና በአንድ መነጽር ብቻ አይቶ የሚሰጥ ጭፍን ድምዳሜ ነው።
...
ስለኢትዮጵያ ማሸነፍ መጸለይ ፣ ከናይጄሪያ መጸለይ አለመጸለይ ጋር ምን ያገናኘዋል? አንድ ሰው ሎተሪ ቆርጦ አንደኛው ዕጣ እንዲደርሰኝ እርዳኝ ብሎ ቢጸልይ ፣ አይይ .. ብዙ ሰው ቆርጧልና ለሌላው አይድረስ ለኔ ብቻ ይድረስ ማለት ስለሆነ አትጸልይ ሊባል ነው? አንድ ሥራ ቦታ የተወዳደረ ሰው "እግዜር ይህን ሥራ እንዳገኝ ርዳኝ" ብሎ ቢጸልይ .. አይይ ብዙ ሰው ተወዳድሯልና ለኔ ብቻ ብለህ አትጸልይ! .. ሊባል ነው? ሁሉም የሚጸልየው እኮ ለራሱ ነው።

እኛ እንደኢትዮጵያዊ፣ ለኢትዮጵያ እንጸልያለን፣ ናይጄሪያኖችም ለራሳቸው ይጸልዩ .. እግዜር ደግሞ የፈቀደውን ይስማ። አንድ ታሪክ ጣል ላድርግ … አንድ አንበሳ ተራበና .. እባክህ አብላኝ አብላኝ እያለ ወደ ፈጣሪው ጸለየ ….. ጸሎቱን እንደጨረሰ ቀና ሲል አንዲት ሚዳቆ አየ። “አይ ፈጣሪ! ጸሎት እንዲህ ፈጥነህ የምትሰማ ተመስገን .. አለና ሊያዛት ሲሮጥ .. እሷም በበኩሏ ወደ ፈጣሪዋ “አውጣኝ፣ አውጣኝ፣ አድነኝ” እያለች በመጸለይ መሮጥ ጀመረች። እግዜር ማንን ይስማ? (ናይጄሪያም ይጸልያል፣ ኢትዮጵያም ትጸልያለች .. እግዜር ማንን ይስማ? ስለዚህ አንጸልይ ለሚሉት ነው ..) .. ታሪኩ ይቀጥላል .
…. አንበሳው ሲከተል፣ ሚዳቆም ስትሮጥ ቆዩ። መጨረሻ ላይ ሚዳቆ አመለጠች፣ አንበሳም ደክሞት እንደተራበ አረፍ ለማለት ሲሞክር ሳይጸልይ ተኝቶ የሚያንኮራፋ ጥንቸል አገኘ። “ተመስገን - ሚዳቆ ብትነሳኝ ጥንቸል ሰጠኸኝ” በማለት ምሳ አደረገው።
ያን ጊዜ እንዲህ ተባለና ተገጠመ
“አውጣኝ ያለም ወጣ አብላኝ ያለም በላ፣
ምስኪኑ ጥንቸል ግን ተኝቶ ተበላ”

እናም ጸሎት ምን ይሰራል፣ ተኙ የሚሉ ጥራዝ ነጠቆች “የ7 ቢሊዮን ሰው ጸሎት በአንድ ሰከንድ መስማት የሚችልን እግዜር ፣ ግራ አታጋቡት ሊሉ ይሞክራሉ። የሱን ጥበብ ማን ያውቃል? ናይጄሪያና ኢትይጵያ ቢሸናነፉ እንኳን ሌሎች አገሮች በተለያየ ምክንያት “ዲስኳሊፋይ” ተደርገው ሁለቱም ሊያልፉ ይችላሉ እኮ! .. የኛ ድርሻ መጸለይ ነው፣ ጸሎታችንን መስማት አለመስማት የእግዜር ነው። ከጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ይሰውረን!!

Thursday 3 October 2013

A MIRACLE IN SYRIA


In December 2004 a Saudi Arabian man, a Moslem, appeared before several news agencies to relate the following incredible event he experienced and which changed his life (this story appeared on TV, the Internet, radio, and was circulated in newspapers, magazines, and pamphlets throughout Saudi Arbia, Syria, Palestine, and evidently in all neighboring countries.Some years ago, this man married a Moslem woman who was very rich, but sterile. As the years passed, and despite all their efforts and significant medical expenses with many doctors, they remained childless. The man's parents suggested to him that he marry a second woman, while upholding his initial marriage (as the local laws permits up to four concurrent marriages).

Saturday 28 September 2013

የሞት “ድግስ”



መስከረም 4 ቀን 1996ዓ.ም ለኢትኦጵ ጋዜጠኛ የስልክ ጥሪ ይደርሰዋል። “ በነገው እለት ከቀኑ 6ሰአት መስቀል አደባባይ በሚገኘው የትግራይ ልማት ዋና ቢሮ 4ኛፎቅ እንድትገኝ” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪ ነበር የደረሰው። ከዛ በፊት ለስድስት ወር የአየር መንገድ የደህንነት ሃላፊ ሃይሌ ጋዜጠኛውን ሲያስጨንቀው፣ የተለያዩ የማግባቢያ ወይም መደለያ ሃሳቦችን ሲያቀርብለት ቆይቷል።                                                                                                        መስከረም 2 ቀን ደግሞ በቀበሌ 06/07 መ/ር ቢሮ እንዲገኝ የሚገልፅ መጥሪያ ቢደርሰውም በአጋጣሚ ጋዜጠኛው ስላልተመቸው አልሄደም። በማግስቱ የቀበሌውን ሊ/መ አቶ ቢሻው አበጋዝን ያገኘውና     « ትላንት ፈልጋችሁኝ ነበር፤ ለምን ነበር?» ሲል ይጠይቀዋል፤ ቢሻውም « እኛ አይደለንም የፈለግንህ፤ ከደህንነት ቢሮ የመጡ ሰዎች ናቸው የፈለጉህ፤ ባለመምጣትህ ተናደው ነው የሄዱት፤ ለምን እንደፈለጉህ አልነገሩንም፤» በማለት መለሰ። …ከዛ በኋላ ነው - የመስከረም 4 ጥሪ የደረሰው፤ በማግስቱ በተባለው ቢሮ ተገኘ። ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ የማህበሩ ዳይሬክተር « ከሚፈልጉህ የበላይ አካላት ጋር አገናኝሃለሁ» በማለት ለጋዜጠኛው ተናግሮ በሚያሽከረክራት ኒሳን መኪና ተያይዘው ቦሌ በሚገኘው የደህንነት ቢሮ አመሩ።..               ከአንድ ግዙፍና አስፈሪ ገፅታ ካለው ሰው ጋር ጋዜጠኛውን አገኛኝቶት ወጥቶ ሄደ። ..« እሺ ኢየሩሳሌም አርአያ..» አለ ንቀት በተሞላበት ሁኔታ፤ አስከተለና፥ « ወ/ስላሴ እባላለሁ፤ ....ከእኛ ባልደረባ ጋር ስትገኛኝ ነበር፤ መንግስት ብዙ አማራጮችን አቅርቦልህ..አንተ ግን አሻፈረኝ ብለሃል። ለመሆኑ የምታወጣቸው መረጃዎች ተፅፈው ነው የሚሰጡህ?...ለምንድነው መረጃ የሚሰጡህን የሕወሐት ሰዎች የማትነግረን?..የምናስራቸው፣ የምንጠይቃቸው መስሎህ ነው?...» ሲል ሹሙ ሲናገር፣ ጋዜጠኛው ግን የቀረቡትን መደራደሪያዎች እንደማይቀበል ተናገረ። ለሁለት ሰአት ተኩል ከደህንነት ሃላፊው ጋር ውዝግብ የተቀላቀለበት ቃላት ተለዋወጡ። በተለይ የደህንነት ሹሙ « ..የትግራይ ተወላጅ ያውም ቤተሰብህ አድዋ ሆነው..እንዴት ፀረ-ሕወሐት ትሆናለህ?..ከጠላቶቻችን አንዱ ከሆነው ኢትኦጵ ጋዜጣ ጋር እንዴት ትሰራለህ?..» እያለ ከመናገሩ በተጨማሪ « እንዳንተ የተለማመጥነውና የታገስነው የለም። ብንገድልህስ?..» ሲል በንቀት ሲጠይቅ፣ ጋዜጠኛውም « ምንም ጥያቄና መልስ አያስፈልገውም፤ አሁኑኑ ሽጉጥህን መዘህ ልታደርገው ትችላለህ። እኔ ብእር እንጂ የያዝኩት - ከጀርባዬ ያሰለፍኩት ሰራዊትና መሳሪያ የለም። ..ደግሞም ለስልጣን ያበቋችሁን 36ሺህ ታጋዮች ላይ ምን እንደፈፀማችሁ ስለማውቅ..» አላስጨረሰውም፤ ..« እሱ አይመለከትህም፤ ከማን ጋር ምን እያወራህ እንዳለህ እወቅ!?..ከዚህ በኋላ እንድታስብበት የ15 ቀን ጊዜ ብቻ ሰጥተንሃል። በነዚህ ቀናት አቋምህን አስተካክለህ፣ የተባልከውን ካልፈፀምክ ግን…እንገድልሃለን!! ማንም አያድንህም!! ጨርሻለሁ።» በማለት አምባረቀበትና አሰናበተው። ..ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ረቡዕ መስከረም 20 ቀን 1996ዓ.ም ከምሽቱ 3፡30 ሰአት ገደማ በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ወ/ስላሴ ያሰማራቸው ሰባት የፌደራል ፖሊስ አባላት “አቦ ድልድይ” አቅራቢያ ጋዜጠኛውን ጥብቀው በያዙት ዱላ የቻሉትን ያክል ቀጥቅጠውና ከፍተኛ ጉዳት አድርሰው ወደ ድልድዩ ወረወሩት። ሶስት ጥርሱ ተሰበረ፣ ጭንቅላቱ 5 ቦታ ተፈነካከተ፤ ሁለቱ እጆቹ፣ ግራ እግሩ፣ ወገቡ፣..አጠቃላይ አካሉ ተጎዳ። ...እነ ወ/ስላሴ ከድርጊቱ በኋላ ለጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና 5 ጊዜ ስልክ ደውለው « የኢየሩሳሌምን ሬሳ ሂድና ከምኒሊክ ሆስፒታል ውሰድ..» ሲሉ ተሳለቁ።…ከጨካኞች፣ ገዳዮችና አምባገነኖች ..የሚጠብቅ ፈጣሪ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባትን የጋዜጠኛውን ነፍስ በኪነ-ጥበቡ ታደጋት። እነሆ ከአስር አመት በኋላ የቀድሞ የደህንነት ሹም ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል እስር ቤት ሲወረወር፥ በእርሱ “ሞት የተደገሰላት” የጋዜጠኛው ነፍስ በህይወት ቆይታ ለማየት በቃች። ሁሉም የዘራውን ሊያጭድ ግድ ነው!! …ይህ ታሪክ የእኔ ነው። (በምስሉ የሚታየው ለስድስት ወር ያልጋ ቁራኛ የዳረገኝ የግድያ ሙከራ ከተፈፀመብኝ በኋላ፣ )


Monday 19 August 2013

BEWKET SEYUM sele EYOB MEKONENE



                                                                      ከጥቂት አመታት በፊት ባንድ የበጎ አድራጎት ትርኢት ላይ ለመሳተፍ፣ከዘፋኞች ጋር ወደ ደሴ ተጉዠ ነበር፡፡የተሣፈርንበት አውቶብስ ጉንጫቸውን በጫት አሎሎ በወጠሩ ዘፋኖች ተሞልቷል፡፡ ዘፋኞቹ ሲሻቸው ይተራረባሉ፣ ሲሻቸው ይጮሃሉ፣ይጨፍራሉ፡፡የአውቶብሳችን ሽማግሌ ሹፌር ሳይቀር፣ አልፎ አልፎ መሪውን እየለቀቀ በማጨብጨብ በ‹‹ቅወጣ›› ከዘፋኞች እንዳማያንስ በማሳየት ላይ ነበር፡፡በጫቱም፣ በጭፈራውም የሌለበት ድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ብቻ እንደሆነ ተመለከትሁ፡፡ በርጋታ ተቀምጦ፣ ባውቶብሱ መስኮት አሻግሮ፣ የሚሮጡ የግራር ዛፎችን ይመለከታል፡፡ልዩነቱ ግልጽ ነበር፡፡
ድሮ ድሮ፣ኢዮብ መኮንን አቤሴሎም የሚዘናፈል ረጅም ጸጉር ያለው ጎልማሳ ነበር፡፡ድንገት ጸጉሩን ተሸለተ፡ከጸጉሩ ጋር የጥንት ባህርይውን አራገፈ፡፡ጭምት መንፈሳዊና በመጽሐፍ ቅዱስ ፍቅር የነደደ ምእመን ሆነ፡፡
በተገናኘን ቁጥር፣ኢዮብ ስለ ስለ እምነት እንድንወያይ ይፈልጋል፡፡ብዙ ጊዜ እምነት የሚያጠብቅ ሰው አንዳች ችግር ይኖርበታል ብየ አስብ ነበር፡፡ኢዮብ ግን እጅግ መልካም ሊባል በሚችል ሕይወቱ ይሄንን አመለካከቴን ውድቅ አድርጎብኛል፡፡
የዛሬ ሳምንት ገደማ ኢዮብ ዘፈን በመሥራት ላይ ነበር፡፡እና ላንድ ዜማው ግጥም እንደሠራለት ጋበዘኝ፡፡ከዚህ በፊት የሞርኳቸው የዘፈን ግጥሞች ስለከሸፉብኝ ግብዣውን ለመቀበል አመነታሁ፡፡ግን ደሞ ወድያው፣ በኢዮብ ድምጽ ግጥሜን ተዘፍኖልኝ ለማየት ጓጉዋሁ፡፡ውሀ ልማት አካባቢ፣ ሌክስፕላዛ ሕንጻ ሥር መኪናው ውስጥ ቁጭ ብለን ዜማዎችን ማድመጥ ጀመርን፡፡ዘፈኑ ውስጥ ያሉት ሐሳቦች አብዛኞቹ ወደ መዝሙር ያዘነብላሉ፡፡ ኢዮብ ዘፈኑን ለፈንጠዝያ ሳይሆን ለስነምግባር ግንባታ ሊጠቀምበት ፈልጓል፡፡አንድ በጣም ልብ የሚበላ የሶ...ማሌ ዘፈን አስደመጠኝ፡፡
‹‹ሶማሊኛ ትችላለህ እንዴ?>>
‹‹አዎ፣ትግርኛም አውቃለሁ!››
‹‹የት ተማርከው?>>
‹‹አስመራ፣የወታደር ልጅ መሆኔን አትርሳ››
ከዘፈን ውጭ ምን ታደርጋለህ?
‹‹ኦን ላይን፣ ጊታር እየተማርሁ ነው፡፡ቆይ ላሳይህ››…ላፕቶፑን ለኮሰና ጥቂት አስጎበኘኝ፡፡ከዛ ከመኪናው ስወርድ የመኪናው እጀታ ስለማይሠራ ወርዶ ከውጭ ከፈተልኝ፡፡ኢዮብ ብዙ ብሮችን መቆጠር የሚችል ልጅ እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ይሁን እንጂ እንኳን መኪናውን የመኪናውን እጀታ ማስቀየር አልፈለገም፡፡ምናልባት፣ዓመት በአልን ጠብቆ ልብስ የሚቀይር ብዙ ሰው ባለበት አገር ውስጥ፣ መኪና መቀያየሩን እንደ ኃጢአት ቆጥሮት ይሆናል፡፡
ከጥቂት ቀናት በኋላ ልኡል የተባለ ዘፋኛ ጓደኛየ የኢዮብን በድንገት መውደቅ ሲነግረኝ ወደ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ሄድኩ፡፡ዘፋኞችና አዘጋጆች መጠበቂያው ክፍል ላይ ተደርድረው ይተክዛሉ፡፡ዘሪቱ፣ዳግማዊ አሊ፣እቁባይ በርሄ፣አጃቸውን አገጫቸው ላይ ጭነው፣ተቀምጠዋል፡፡የኢዮብ ባለቤት ወድያ ወዲህ እየተንቆራጠጠች ታነባለች፡፡
ዛሬ ደግሞ ይሄው ሞቱን ሰማሁ፡፡ለካ፣ወደ ደሴ የሚሄደውም አውቶብስም ሆነ፣ሌክስ ፕላዛ ሕንጻ ስር፣ የቆመው ቪታራ መኪናው መዳረሻቸው አንድ ነው፡፡መቃብር!!
ኢዮብ!!! በጠፈሩ ውስጥ፣ ያለ ግብ ከሚዞሩ ኮረቶች፣ያለ ምክንያት ከሚበሩ ኮከቦች በቀር ምንም የለም ብየ እንደማምን ታውቃለህ፡፡ይሁን እንጂ ለዛሬ እንኳ፣ የኔ እምነት ከሽፎ ያንተ እምነት እውነት እንዲሆን እመኛለሁ፡፡በምድር ለገጠመህ መራራ እጣ ሰማያዊ ካሳ(ጉማ) እንድታገኝ እመኛለ



Tuesday 6 August 2013

ለእግዜር የተላከ ደብዳቤ[ ስሙ ለጊዜው ካልታወቀ ገጣሚ)

ማታ ልተኛ ስል አንድ ጓደኛየ ይሄን ግጥም ላከልኝ ባጭሩ መተኛቴን ተውኩት!!!! ከፍ ካለ ይቅርታ ጋር የገጣሚውን ስም ማግኘት አልቻልኩም (የምታውቁት ካላችሁ እባካችሁ ስሙን አካፍሉን ....... እንደተላከችልኝ ይሄው .....ገጣሚውን እጁ ይባረክ እያልኩ ....ኡፉፉፉፉ እንዴት ደስ ይላል!!

ለእግዜር የተላከ ደብዳቤ
(ስሙ ለጊዜው ካልታወቀ ገጣሚ)

እንደምነህ እግዜር
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ ምነው ........?

... እኛማ.....
ለእልፍ አላፍ አለቃ
ማመልከቻ ፅፈን
ለወፈ ሰማይ ህዝብ
መድረክ ላይ ለፍፈን
ፆለት ቤታችንን
እኛው ላይ ቆልፈን
የምድር አተካራ
ህግጋቱን አልፈን ደብዳቤ ላክንልህ ...........

አይንህን ካየነው
ሁለት ሽ ዘመን
እንደቀልድ አለፈ
የመምጣትህ ተስፋ እየኮሰመነ
መቅረትህ ገዘፈ....

እንደውም እንደውም.....
‹‹በእመጣለሁ ተስፋ
ሁለት ሽ ዘመን
ቀጥሮን ከጠፋ
በቀጠሮው ሰአት
መምጣት ከተሳነው
እግዜር አበሻ ነው ›› እያሉ ያሙሃል

እኔ ምን አውቃለሁ ....
አመስግነው ሲሉ እልልታ የማቀልጥ
ቃሉን ስማ ሲሉኝ .....ሰባኪው እግር ስር በደስታ እምቀመጥ
እግዚ...ኦ በሉ ሲባል ....እንባየን የማፈስ
ሃሌ ሉያ ሲሉኝ .....በሳቅ ልቤ እሚፈርስ
ምናምኒት እውቀት ውስጤ ያልፀደቀ
እንበረከክበት ጉልበቴ ያለቀ
እኔ ምን አውቃለሁ......

Tuesday 2 July 2013

‹‹ሥልጣን ልቀቁ?››


ዳንኤል ክብረት 

click here for pdf
ኢትዮጵያ ከቦትስዋና ጋር ስትጫወት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋች አሰልፋችኋልና ሦስት ነጥብ ታጣላችሁ ብሎ ፊፋ የሚባል ቡዳ አገሩን ቀወጠው፡፡ እንደ አውነቱ ከሆነ እንዲህ ዓይነት ነገር ማድረግ የሌለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ፊፋ ከአድኅሮት ኃይሎች ጋር ካልተሰለፈ በቀር ሌላ ምክንያት ሰጥቶ ኢትዮጵያን መጣል ይችል ነበር፡፡ ለኛ የኢትዮጵያ ነጥብ መቀነስ አይደለም ችግራችን፤ ነጥቡ መቀነሱን ሕዝቡ መስማቱ ነው፡፡ እኛኮ ቀስ አድርገን ‹ኪራይ ሰብሳቢዎች የሀገራችንን የስፖርት ራእይ ለማደናቀፍ ከፀረ ሕዝብ ኃይሎች ጋር በመሆን የደቀኑብን ሤራ ነው› ብለን ሕዝቡን ማሳመን እንችል ነበር፡፡
መጀመሪያ ከበላዮቻችን ጋር እንነጋገራለን፤ ሂስ ከተሰጠንም ሂሳችንን እንውጣለን፣ ግምገማችንንም እንቀበላለን፣ ዋናው ይሄ አይደለም፤ አንዴት አድርገን ለሕዝቡ እንንገረው? የሚለው ነው፡፡ ሕዝብ እንደነገርከው ነው፡፡ እንደ አሰማሙ ነው፡፡ አቀናብረን ከነገርነው አቀናብሮ ይሰማል፡፡ ግን ምን ያደርጋል፣ ፊፋ የሚባል ቡዳ ለሕዝብ መነገር የሌለበትን ለሕዝብ ተናገረና መከራ አሳየን፡፡
አሁን አዳሜ ዕድል ስታገኝ ጊዜ ‹ለምን ሥልጣን አትለቁም› ትላለች፡፡ 
 እስኪ ተዪው አሉኝ ያልደረሰባቸው
እንዲህ በቀላሉ የሚተው መስሏቸው
አለች የሀገሬ ዘፋኝ፡፡ ሥልጣን እንዲህ በቀላሉ የሚተው መስሏቸዋል፡፡ እኛ በቀጣዩ ምርጫ እንዴት አድርገን ተመልሰን እንደምንመጣ እያሰብን እነርሱ ሥልጣን ልቀቁ ይሉናል፡፡ ‹ከአንድ ሙዚቃ በኋላ ተመልሰን እንገናኛለን› አሉ የኤፍ ኤም ጋዜጠኞች፡፡
ስለ ሥልጣን መልቀቅ እዚህ ሀገር የሚያስብ ሰው ካለ የመጨረሻው ጅል እርሱ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ስለ ሥልጣን አያውቅምና፡፡ ‹‹አቤቱ የሚናገሩትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው››፡፡ እነዚህ ሰዎች ሥልጣንን ያልቀመሷት ሰዎች ናቸው፡፡ ቢቀምሷት ኖሮ ‹አጥብቃችሁ ያዟት› ይላሉ እንጂ ‹ልቀቋት› አይሉም ነበር፡፡ መንፈሳውያን ነን፣ ዓለምን ንቀናል የሚሉት አባቶች እንኳን ለሥልጣን በሚታገሉባት ሀገር እኛን ዓለማውያኑን ‹ሥልጣን ልቀቁ› እንደማለት ያለ የዓመቱ ምርጥ ቀልድ የለም፡፡
ጎበዝ እዚህ ሀገር ባለ ሥልጣን ማለትኮ ትንሽ ፈጣሪ መሆን ማለት ነው፡፡ ሰው የሚሰግድልህ ሥልጣን ሲኖርህ ነው እንጂ ዕውቀት ሲኖርህ አይደለም፣ ሰው የሚኮራብህ ሥልጣን ሲኖርህ እንጂ ችሎታ ሲኖርህ አይደለም፡፡ እስቲ የትኛው የአክስትህ ልጅ ነው እገሌ የተባለው ሳይንቲስትኮ ዘመዴ ነው ብሎ የሚኮራው? የባለሥልጣን ግን እንኳን ዘመዱ ድመቱም አረማመዱ የተለየ ነው፡፡ ጅል- ሥልጣን ልቀቁ ይላል እንዴ፡፡ ሥልጣን የሻሂ ቤት ወንበር መሰላችሁ እንዴ፡፡

Saturday 29 June 2013

ተመስገን ደሳለኝ ለማን ደስ ይበለው ብሎ ጠፋ!?

ባለፈው ጊዜ አንድ ወዳጄ ጋር አዲሳባ ስልክ ደውዬ ሳናግረው በአካባቢው ከእርሱ ድምጽ ጎልቶ የሚሰማ የመኪና ጥሩንባ ሰማሁና ይሄ ሁሉ የመኪና ጥሩምባ ምንድነው… ብዬ ጠየኩት፡፡
ሃይለማሪያም ደሳለኝ እየገቡ ወይም እየወጡ ነው መሰለኝ መንገድ ተዘጋግቷል፡፡ አለኝ፡፡
ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤  እንደ ሀቁ ቢሆን ኖሮ መንገድ መዘጋጋት የነበረበት ለሀይለማሪያም ደሳለኝ ሳይሆን ለተመስገን ደሳለኝ ነበር… አለኝና በቁጭት፤ ይሄው የሚያጅቡትን አያቀውቁምና… እልኩ እያታዘብኩ ነው…! ሲል አወጋኝ!
ተመስገን ደሳለኝ ገዢውም ተገዢውም ፓርቲ ሊያመሰግነው የሚገባ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ነገር ግን ገዢዎቻችን ማመስገን የሚቆጥር ይመስል ሰውን ማመስገን አይወዱም፡፡  ስለዚህ ተሜንም በማመስገን ፈንታ ከሰሱት፡፡ ጎሽ በማለት ፈንታ እንደ ጎሽ ሊወጉት ቀንዳቸውን አሾሉበት፡፡ እሰይ በማለት ምትክ ሰይ ባንከረባብት ብለው ለሁለቱም አሰቡት፡፡ (ለማሰርም ለማሰደድም) (ሰይ ባንከረባብት በልጅነታችን ብይ ጨዋታ ላይ ተወርዋሪዋ ብይ ጉድጓዳ ውስጥ ብትገባም የተቃራኒውን ብይ ብትመታም ነጥቡ እንዲያዝልን ውል የምንገባባት ቃል ነበረች፡፡)
ተመስገን ደሳለኝ እንዲሰደድ መንግስት ከፀሎት ጀምሮ ሁሉንም አይነት የትግል ስልቶችን እንደተጠቀመበት ትዝ ይለኛል፡፡ ለምሳሌ ባለፈው ጊዜ ምንም የቀጠሮ ወረቀት ወይም መጥሪያ ሳይሰጠው በራዲዮን፤ “ተመስገን ደሳለኝ በሌለበት የፍርድ ሂደቱ ታየ ለሚቀጥለው ጊዜ ፖሊስ ይዞ እንዲያቀርበው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል!” የሚል አይነት ዜና በሰላም ቁጭ ብሎ ሻይ በሚጠጣበት ካፌ ውስጥ ሰማ፤ (እናጋን ካልን ደግሞ ዜናውን እንደውም ያነበቡት ተሜ ልክ ዜና ሲሰማ አይተው ነው…! ማለት እንችላለን…) የዚህ ዜና አላማ ግልፅ ነበር፡፡ ተሜ ደንግጦ ፖሊስ ሳይዘው በፊት መንገዱን እንዲያያዘው ማድረግ ነበር፡፡ ወዳጃችን ግን፤ ብታስሩኝ ባለ ጊዜም ባለ ብረትም ናችሁና እግሬ እምቢ ማለት አይቻለውም፡፡ ለመሰደድ ግን እሺ የሚል እግር የለኝም፡፡ ብሎ እንቅጩን ነገራቸው እና የመጣው ምጣ ብሎ ቁጭ አለ…

Sunday 23 June 2013

ጭፈራችንን መልሱልን ሰኔ 11/2005 (ለምስኪኑ ህዝባችን

ጭፈራችንን መልሱልን
ያገር ብርድ ሲቆነድደን
ኳስ ሜዳውን አልቤርጐ አርገን
ድንጋይ ጠርዙን ተንተርሰን
የታክሲ ውስጥ አልጋ አንጥፈን
... ሌት በዋዜማ አልመን፣ ነገን በዕውነት ልናበራ፤
ባንዲራ እንደደመራ
ከምረን በየኳስ ጐራ፤
ተውለብልበን አውለብልበን
ላንቃችን እስኪበጣጠስ፣ ሆ ብለን በማታ በቀን፤
በጭለማ ድል ጐስመን

Tuesday 4 June 2013

Mesfin Wolde-mariam


  • Mesfin Wolde-mariamጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመጭም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም በሚያሰፈስፉበት ጊዜ በርቱ እያሉ የሚያቅራሩ ሞልተው ነበር፤ ዛሬ አቀራሪዎቹም ሆኑ ጀብደኖቹ በኤርትራ ጦርነት ያለቀባሪ ስለቀሩት ሰዎች፣ ጠዋሪ ስላጡ እናቶችና አባቶች፣ አሳዳጊ ስለሌላቸው ልጆችና አካለ-ጎደሎ ለሆኑት የሚያስብላቸው አለ ወይ? የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መነሣትና በኢጣልያ የግራዚያኒ ሐውልት እን...ዳይሠራ የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎ ለሰልፍ የወጡትን አስሮ ያሳደረ አገዛዝ ለአገራቸው ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ያሳያል፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ሲወዱ ራሳቸው በልጽገው ለልጆቻቸው ብልጽግናን እንዲያወርሱ ሕይወታቸውን ቢጠብቁ ለአገራቸውም ክብር ይሆናሉ፡፡
    ለፍቅር መተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጠብም መተዋወቅ ያስፈልጋል፤ የተሟላ መረጃ ቢኖረን የጥንት ታሪክ እየጠቀስን ሰዎችን ለጦርነት እንቀሰቅስም ነበር ብዬ አምናለሁ፤ ስለዚህም አንዳንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ላቅርብ፤ ---

    1. የግብጽ የጦር ኃይል በዓለም አሥረኛ ነው፣ በአፍሪካና በመሀከለኛው ምሥራቅ የሚወዳደረው የለም፤ አንድ ሚልዮን ተኩል ያህል የጦር ኃይል አለው፤ በዓየር ኃይልም ከዓለም አሥራ አራተኛ ነው፤ በታንክ ብዛት አራተኛ ነው፤ በባሕር ኃይል ሰባተኛ ነው፤ በጦር በጀት አርባ ሦስተኛ ነው፤
    2. በኢትዮጵያ ዙሪያ ጂቡቲ፣ ሶማልያ፣ ሱዳን የአረብ ማኅበር አባሎች በመሆናቸው ለግብጽ ማኅበረተኞች ናቸው፤ በወያኔ ፈቃድ የተገፋችው ኤርትራም የዚሁ ማኅበር ታዛቢ አባል ነች፤ ከቀይ ባሕር ማዶ ያሉት አገሮች ሁሉ ሀብታሙንና ኃይለኛውን ሳኡዲ አረብያንም ጨምሮ የግብጽ ማኅበርተኞች ናቸው፤ በዚህ ሁሉ መሀከል የተከታተፈች ኢትዮጵያ ብቻዋን ነች፤
    3. የቤንዚን ሀብትና ከሀብቱም ጋር የሚገኘውን ወዳጅና ጡንቻ አንርሳ፤

    ይህ ማስታወሻ ለማስፈራራት አይደለም፤ ማስፈራራትን አላውቅበትም፤ እንዲያውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ‹‹አትፍሩ›› ብሏቸዋል ተብዬ ተከስሼ ታስሬአለሁ፤ ስለዚህ አላስፈራራም፤ ጦርነት ከመጣብን ልናስቀረው እንሞክር፤ ሌላው ቢቀር እንድንዘጋጅ ጊዜ እናገኛለን፤ ገፍቶ ከመጣ ግን እንቋቋመዋለን፤ ለጦርነት አንቸኩል፤ ለኤርትራም ጊዜ ተናግሬ ነበር፤ የሰማኝ የለም፤ ጥጋብ ላይ ያሉ የሚርባቸው ዝና ነው፤ የሚያገኙት ግን ውርደትን ነው፡፡

Thursday 16 May 2013

አንጋፋዋ ድምጻዊ አበበች ደራራ አረፈች


Ethiopian singer Abebech Deraraለረጂም ዓመታት በራስ ቴአትር በድምጻዊነት ስትሰራና ለአድማጮችዋ ዜማዎችን ስታቀርብ ኖራ በስተመጨረሻው ወደ እስራኤል ሀገር ከትማ ስትኖረ የነበረችው ታዋቂዋ ድምጸ መልካሟ አበበች ደራራ ዛሬ ሜይ 16 ቀን ባደረባት ህመም ሳቢያ ሕይወቷ አልፏል፡፡
አበበች ደራራ በሕመም ተይዛ ለበርካታ ወቅት በአልጋ ላይ ከመቆየቷም ባሻገር ጨርሶ ከሰዎች ጋር ግንኙነት አቋርጣ በሽታዋን ለብቻዋ ስታስታምም እንደነበረች በቅርብ የሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
የአበበች ደራራ አስከሬን በኖረችበት የቴል አቪቭ ከተማ በዛሬው እለት ከቀኑ 3.00PM ላይ ወደ ቀብር በወዳጅ ዘመዶች ታጅቦ በመሄድ ሥርአተ ቀብርዋም ይፈጸማል፡፡ 
ለወዳጅ ዘመዶቿ መጽናናትንፈጣሪን ይስጣቸው ዘንድ እለምናለሁ፡፡
አርቲስት ደበበ እሸቱ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳስቀመጠው።

Sunday 12 May 2013

የእነ መላኩ ፈንታ ጉዳይ…ተመስገን ደሳለኝ

የእነ መላኩ ፈንታ ጉዳይ…
ከአንድ ወዳጄ ጋር ሃያ ሁለት አካባቢ ምሳ በልተን ስናበቃ እንደሌላው ቀን ሹፌሬ ስላልነበር በኮንትራት ታክሲ ወደቤቴ (አሲምባ) አመራሁ፡፡ ታክሲው በውለታችን መሰረት የቀበናን አደባባይ ዞሮ ሲቆም፣ እኔም ሂሳቤን አወራርጄ ወረድኩ፡፡ ሆኖም ጥቂት እርምጃ እንደተራመድኩ ያላስተዋልኳቸው ሁለት ሰዎች አጠገቤ ደርሰዋል፡፡ በዕድሜ እኩዮቼ ይመስላሉ፡፡ አንዱ ቀጭንና ቀውላላ ነገር ነው፤ ሌላኛው ደግሞ ቁመቱ መካከለኛ ሆኖ፣ ደልደል ያለ ሰውነት አለው፤ ሁለቱም ‹‹ጠይም›› የሚባሉ ና...ቸው፡፡ ቀውላላው፡-
‹‹ሰላም ተመስገን!›› አለኝ፣
‹‹ሰላም!›› መለስኩኝ፡፡
‹‹ልናናግርህ ፈልግን ነበር?››
‹‹ይቅርታ አላወኳችሁም፡፡››
‹‹አንተ አታውቀንም! እኛ ነን የምናውቅህ››
‹‹የት ነው የምታውቁኝ? ማለቴ በምን መልኩ…››
‹‹እሱን ተወው! የእኛ ማንነትንም እንድንነግርህ አትጠብቅ፣ ይገባሃል ብለን እናስባለን!›› አለ እስከአሁን ዝም ብሎ የነበረው ደልዳላው ሰው፡፡ ሆኖም ቀውላላው ጓደኛው አቋርጦት ቀጠለ፡-
‹‹ ምን መሰለህ? ሰሞኑን እነ መላኩ ፈንታ እንደታሰሩ ታውቃለህ፤ እናም የእነርሱ ጉዳይ የእኛ ብቻ ነው፤ አንተን አይመለከትህም፡፡››
‹‹አልገባኝም! ይህ ምን ማለት ነው?››
‹‹በቃ! በዚህ ጉዳይ ላይ ትንተና፣ ማብራሪያ እፅፋለሁ ምናምን እያልክ አትድከም ለማለት ነው!›› ቆጣ ባለ መልኩ መለሰልኝ-ደልዳላው ሰው፡፡
ከትከት ብሎ መሳቅ አማረኝ፤ በጣም መሳቅ! ሆኖም ለምን እንደሆነ አልውቅም-አልሳቅኩም፡፡ በግልባጩ ድንገተኛ ንዴት በመላ ሰውነቴ ሲሰርፅ ታወቀኝ፡፡ ከሰከንዶች በኋላም እስከአሁን ሲናገር ትህትና ያልተለየው ቀውላላው ሰው እንዲህ ሲል አግባባኝ፡-
‹‹እየውልህ፣ መንግስት ሰዎቹን ያሰረው በወንጀል ላይ በመሰማራታቸው ከመሆኑ በተጨማሪ ለህዝብና ለሀገር ጥቅም ነው፤ ስለዚህም ገና ፍርድቤት ስለሚቀርቡ፣ ምርመራውም ስላላለቀ አንተ በፅሁፍህ ተሳስተህ፣ ለሌሎችም የተሳሳተ መረጃ እንዳታስተላልፍ ለመምከር ነው፡፡››
‹‹ስለምክራችሁ በጣም አመሰግናለሁ! ነገር ግን እኔ የምሰራውን አውቃለሁና ለስራዬ መካሪ አያስፈልገኝም›› ስል ባለመካከለኛ ሰውነቱ አቋረጠኝና፤ ከቅድሙ በባሰ የቁጣ ቃል መናገሩን ቀጠለ፡-
‹‹ስማ! ልንመክርህ ወይም ልናባብልህ አይደለም የመጣናው፤ በቃ በማያገባህ ጉዳይ መግባት እንደሌለብህ ልንነግርህ ነው!››
ይህን ጊዜም አነጋገሩ በስሱ አስቆጣኝና፡-
‹‹እየወልህ! እናንተ ማንም ብትሆኑ ግድ አይሰጠኝም፤ ኋላ ኪሳችሁ ያለው መታወቂያም አያሳስበኝም፡፡ እስከዛሬ ድረስ የማደርጋትን እያንዳንዷ ነገር አስቤበትና አምኜበት ነው፤ ማስፈራሪያችሁ እኔ ጋ ቦታ የለውም፡፡ ምናልባት ‹ይህንን ጻፍ፤ ይህንን አትጻፍ› ስትሏቸው ትዕዛዛችሁን በመፈፀም ያስለመዷችሁ ጋዜጠኞች ካሉ ወደእነርሱ ልትሄዱ ትችላላችሁ›› ብዬ መንገዴን ልቀጥል ስል፣ ትሁቱና ቀውላላው ሰው፡-
‹‹ተመስገን ብታስብበት መልካም ነው!›› አለ፣
‹‹ምንም የማስብበት ነገር የለም፤ ይልቅ አለቃችሁን ንገሩት፣ ሰሞኑን እንደናንተ አይነት ፀጉረ ልውጦች በቤቴ አካባቢ በዝተዋልና ሰብስብልኝ፣ ይሄ አንድም ስራ መፍታት ነው፤ ሁለትም የሀገር ሃብት ማባከን ነውና! ብሎሀል በሉት››
…ከዚህ በኋላ ቤቴ ገብቼ ስለገጠመኜ ማሰብ ስጀምር መልስ የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች በአእምሮዬ ተመላለሱ፡- በዚህች ሀገር ላይ ምን እየተደረገ ነው? እነማን፣ በእነማን ላይ እያሴሩ ነው? መላኩ ፈንታ የታሰረው እውነት በሙስና ብቻ ነውን? ኢህአዴግስ ዕውን ሙስናን ለመከላከል ቆረጦ ተነስቷል?አሁን ማ ይሙት በሙስና መጠየቅ ከተጀመረ መላኩ ነው የመጀመሪያ የሚሆነው? ወይስ…
(የሆነ ሆኖ ይህችን የሞነጫጨርኩት ‹‹አይመለከትህም!›› ያሉኝ ሰዎች እንደሚመለከተኝ ይረዱ ዘንድ ነውና፣ በቅርቡ በስፋት የምመለስባቸውን የመነሻ ሃሳቦች አስቀምጬ ልሰናበት)
1. መላኩ ፈንታ በባህርዳሩ ስብሰባ ላይ ‹‹የህወሓት ስውር እጆች›› እንደሚደግፋቸው የሚነገርላቸውን ሁለት መቶ ነጋዴዎች በስም ጠቅሶ ‹‹አላሰራ አሉኝ፤ አስቸገሩኝ!›› ብሎ ሪፖርት ማቅረቡ ያስቆጣው አካል በእስሩ ላይ መኖር አለመኖሩን፤ አዜብ መስፍን በዛው ጉባኤ ላይ ‹‹መለስ ብቻ ነው በደሞዝ የኖረው›› የሚል ጥቆማ ከማቅረቧ ጋር ተያያዥነት አለው ወይስ የለውም?
(ስለሰውየው ብቃትና ከሙስና የፀዳ ስለመሆኑ በስፋት ይነገር እንደነበር አውቃለሁ፤ በአናቱም የኢህአዴግ አመራር ሆኖ ከሙስና የራቀ ይኖራል ብሎ ማሰብ በእጅጉ ይከብዳል፡፡ በእርግጥ ‹‹የመላኩ ችግር›› ተብሎ ሲነገር እስማ የነበረው ከመልከ መልካምነቱ ጋር ተያይዛ የምትነሳ ጉዳይ ነች-ቶሎ በፍቅር መሸነፍ፡፡ በነገራችን ላይ መላኩ ከሆኑ ጊዜያት በፊት ዱባይ ውስጥ የመኪና አደጋ ደርሶበት እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ለስራ ጉዳይ ሄዶ ግን አልመሰለኝም)
2. መቼም የማይካደው ሀቅ መላኩ ፈንታ ለፓርቲው ባለውለታ መሆኑ ነው፡፡ ይኸውም በተለይ ከምርጫ 97 በኋላ ኢህአዴግ ‹‹አይደግፉኝም›› ያላቸውን ነጋዴዎች የተለያየ ምክንያት እየለጠፈ እንደአኮሰመናቸው ይታወሳል፡፡ ይህንን የስራ ሂደት ካሳኩት ‹‹ዋነኞቹ አስፈፃሚዎች›› መካከል ደግሞ እርሱ ይመራው የነበረው መስሪያ ቤት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ እናም እዚህ ጋር የሚነሳው ጥያቄ ዛሬ መላኩ ፊቱን ከጠላት ወደወዳጅ (የስርዓቱ አውራ ጣት ወደሆኑ ነጋዴዎች) ማዞሩ የመዘዘው ጦስ በድርጅቱ ውስጥ ለተፈጠረው ልዩነት ‹‹መያዣ›› (የአብርሃም በግ) አድርጎት ይሆናል ብሎ መከራከር ይቻል ይሆን? መላኩስ ይህንን ጥያቄ ያቀረበው በራሱ ተነሳሽነት ነው? ወይስ ‹‹አይዞህ›› ብሎ አደፋፍሮት ሲያበቃ የከዳው ቡድን አለ?
3. በኢህአዴግ ውስጥ የእስክንድር ነጋ ጉዳይ ልዩነት ፈጥሯል፡፡ እነ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ እንዲፈታ ይፈልጋሉ፡፡ ብአዴንም ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ይህንን ሃሳብ ይደግፋል፡፡ እናም እነዚህ ልዩነቶች መስፋታቸው ይሆናል ሁለት የብአዴን አመራር አባል የሆኑ ሚንስትሮችን በአንድ ሳምንት ውስጥ ‹‹የነቀላ››ው ሰላባ አድርጓቸው ይሆን?
4. እንዲህ አይነቱ እስር እና ድንገት ከሃላፊነት መባረር በመላኩና በብርሃን ብቻ ይቆማል? ወይስ ይቀጥላል? ከቀጠለስ ወደ እነማን ያመራል?

ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለማስከበር ማንኛውንም መስዋዕትነት መክፈል የሁላችንም ግዴታ ነው!

Thursday 2 May 2013

የአቡነ ጵጥሮስ ሃውልት መነሳት በበውቀቱ ስዩም አገላለጽ

ማለዳ መነሣት አልወድም፡፡ዛሬ ግን አቡነ ጴጥሮስ ከመታሰቢያቸው ዙፋን ሲወርዱ ለመታዘብ በማለዳው ካልጋየ ጨክኘ ወረድሁ፡፡ለአቡነ ጴጥሮስ ፍቅር ስል የማለዳ እንቅልፌን ብሰዋ አይቆጨኝም፡፡በቅርቡ በሚከፈተው ጦማሬ ላይ ስለ ጀግናው ጴጥሮስ በሰፊው የመጻፍ ሐሳብ አለኝ፡፡
በቦታው ስደርስ፣የጴጥሮስ ሀውልት በጣውላ ተገንዞ ቆሟል፡፡ድብርት ተጫጫነኝ፡፡ምናልባት አያቶቼ አቡኑ ሲረሸኑ በተመለከቱበት ሰአት የተሰማቸው ስሜት እንዲህ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የራስ ቁር የደፉ የቀን ሠራተኞች በአቡኑ ትክሻ ላይ እንደ ወፍ ሰፍረዋል፡፡ ወደ መርካቶ በሚሄዱ ተሳፋሪዎች የተሞሉ ሚኒባሶች አደባባዩን ታክከው ሽው ይላሉ፡፡ ተሳፋሪዎቹ፣ በመስታውት አሻ......ግረው የሚመለከቱት ትእይንት ብዙ የመሰጣቸው አይመሰልም፡፡በፋሲካ አስፈሪ የዶሮ ዋጋ ለተጠመደ አእምሮ ታሪክ ምኑ ነው??
ከተመልካቹ በላይ የፖሊሱ ቁጥር የሚበልጥ መሰለኝ፡፡አንድ ፒካፕ መኪና ስትበር መጣችና ቁና ሙሉ ፌደራል ፖሊስ አራገፈች፡፡ሰብሰብ ብለን በቆምንበት አንዱ ፖሊስ ጠጋ አለና‹‹ እናንተን አይመለከታችሁም ከዚህ ሂዱ›› አለ፡፡ካጠገቤ የቆመ ጎበዝ ‹‹ማየት መብታችን ነው›› ብሎ መልሶ ጮከበት፡፡አሀ! የጴጥሮስ መንፈስ አልከሰመም ማለት ነው፡፡ፖሊሱ ምንም ሳይመልስ ከሬድዮ መገናኛው ጋር እየተመካከረ ካካባቢው ራቀ፡፡
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጋዜጠኛ ጓደኞቼ ካሜራቸውን ታጥቀው ደረሱና ተቀላቀሉኝ፡፡ ሀውልቱን ማስቀረት ስላልቻሉ ምስሉን ቀርጸው ለማስቀረት ተሯሯጡ፡፡
ድንገት ቀና ብየ ሳይ ከሀውልቱ ፊትለፊት ጅማ በር የሚባል ፣ጣልያን የሠራው አሮጌ ሕንጻ ይታየኛል፡፡ባቡሩ የአቡነ ጴጥሮስን መታሰቢያ ደቅድቆ ሲያልፍ፣ጣልያን ሠራሹን ግንብ ንክች አያደርገውም፡፡ጉደኛ ባቡር!!!
በጣውላ የተገነዘውን የአቡኑን ሀውልት ለመሸከም አንድ አዳፋ ረጅም ተጎታች መኪና ብቅ አለ፡፡ዳይኖሰር የመሰለ ክሬን ሀውልቱን ነቅሎ ሲያንጠለጥለው፣ሀውልቱ የነበረበት ቦታ ጥርስ የወለቀበት አፍ መሠለ፡፡ቀሪውን የማየት ፍላጎት ስላልነበረኝ ከጓደኛየ ጋር ወደ ፒያሳ አቀናሁ፡፡ብዙ ነገር እዬተለወጠ መሆኑን አየሁ፡፡የጥንቱ መሀሙድ መዚቃ ቤት ወደ ቡቲክ መቀየሩን አስተዋልሁ፡፡የጥንቱ አያሌው ሙዚቃ ቤት ፍራፍሬ መሸጫ ሱቅ ሆኗል፡፡ከጥቂት ወራት በፊት ብርቱካኔ የሚለው ሙዚቃ ይንቆረቆርበት የነበረው ቦታ ፣አሁን ብርቱካን በኪሎ ይሸጥበታል፡፡
አዲስአበባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ያለጥርጥር፣ባቡር ይኖራታል፡፡ቀለበት መንገዶች ይኖሯታል፡፡አሪፍ ህንጻዎች ይኖሯታል፡፡ነገር ግን፣ ትናንት የሚባለው ነገር አይኖራትም፡፡ A city without past ላዲስ አበባ የተገባ ቅጽል ነው፡፡
ወደ ሰፈሬ የሚሄድ ታክሲ ስፈናጠጥ፣ የሚከተሉት የጸጋየ ገብረመድህን ግጥሞች ሽው አሉብኝ፡፡
….መጭው ደመና ጥቁረቱ፣
ጮቁ ፣ማጡ፣የክረምቱ፣አቤት ዝቅጠቱ ማስፈራቱ
የኛስ ትውልድ አከተመ፣አገራችንን አምክነን
የነገስ ዘር ምን ይበለን፣ስንተወው ሲኦል አውርሰን

የእነ አንዱዓለም አራጌ ይግባኝና የዛሬው የፍርድ ቤት ብይን

ኢትዮጵያ

 

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፤ በእነ አንዱዓለም አራጌ መዝገብና በሌሎች መዝገቦች ፤ በአሸባሪነት ተከሠው ይግባኝ የጠየቁ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአመራር አባላትና የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጉዳይ መርምሮ፣ ከአንደኛው በስተቀር የሁሉንም የእሥራት ብይን እንዲጸና አድርጓል።
የክንፈ ሚካኤል በየነ እሥራት ፤ ከ 25 ዓመት ወደ 16 ዓመት ዝቅ እንዲል ወስኗል።
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአሸባሪነት የተወነጀሉት እና ከአለፈዉ ዓመት ጀምሮ እስር ላይ ያሉትን፤ አምደኛ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንዲሁም የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዉ አንዱአለም አራጌ፤ ያቀረቡትን ይግባኝ ዉድቅ አደረገ።
«ብይኑ አሁንም ትክክል ነዉ፤ ምንም አይነት ቅነሳ አይኖርም ሲሉ» የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ ደጀኔ መላኩ ተናግረዋል። ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዲፕሎማቶች በዘመድ እና በጓደኛ በተሞላዉ ብይን ላይ ከዉሳኔዉ በኋላ « እዉነት አንድ ቀን ይወጣል» ሲል በስሜት መናገሩ ተገልጾአል።
Anwalt Abebe Guta im Prozess Journalist Eskinder Nega und Oppositionellen
Andualem Arage 020513.
Foto: Yohannes G/Egziabher DW Korrespondent 2013 ጠበቃ አበበ ጉታ
እስክንድር ነጋ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያዉቅ የምንፈልገዉ እዉነት እራሱ በግዜዉ ይወጣል፤ የግዜ ጉዳይ ብቻ ነዉ» ብሎአል። አንዱአም አራጌ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከመንግስት ተቃዋሚ ቡድን ግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላችሁ ተብለዉ እስክንድር የ 18 ዓመት ጽኑ እስራት አንዱዓለም ደግሞ የእድሜ ልክ እስራት ተበይኖባቸዋል። በአሁኑ ወቅት በእሥር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር እጎ እ 2012 ዓ,ም ዓለም አቀፉ የደራስያን ድርጅት ፔን በዓለምአቀፍ ደረጃ በሥራቸው ምክንያት ለታሠሩ ወይም አደጋ ላይ ለወደቁ ደራስያንና ጋዜጠኞች የሚበረከተዉን የመፃፍ ነፃነት ሽልማት ማግኘቱ ይታወቃል። ዝርዝሩን ዮሃንስ ገ/እግዚአብሄር ወኪላችን ተከታትሎታል።
ዮሃንስ ገ/እግዚአብሄር
ተክሌ የኋላ

Saturday 20 April 2013

Police stopped meeting in Tasta bydelshus ሰበር ዜና፣ በአባይ ስም ዶላር ለመሰብሰብ በሲውዲን የወያኔ አምባሳደር ወደ ኖርዌይ ተጉዛ ውርደት ተከናንባ ተመልሳለች]

አማርኛውን ሪፖርት እና ኖርዌ ስታቫንገር ያለ ጋዜጣ ያወጣውን  ወደ እንግሊዘኛ በመቀያር እንድታዩት አያይዠዋለው።
ከአባይ በፊት የህዝብ ስቃይ ፤እስር ፤ስደት፧ መፈናቀል ፡ይቁም

አምባሳደሯ በሁለት ወያኔዎች ታጅባ ስለ ፓስፖርትና፣ ስለ አባይ ግድብ ቦንድ መናገር ከመጀመሯ የኖርዌይ ኢትዮጵያውያን “የለም የለም ኢትዮጵያ ውስጥ በግፍ ስለታሰሩ፣ በዘራቸው ምክንያት በሀገራቸው እየተፈናቀሉ ስላሉት ወገኖቻችን በቅድሚያ ጥያቄ አለን” በማለት አምባሳደሯን ሰንገው ይይዟታል።
ኢትዮጵያውያን ከኖርዌ ስብሰባ ያባረሯት የወያኔ አምባሳደር "መብራት በየነ አባይ"።

ስብሰባው የወያኔዋ ተወካይ ባሰበችው መንገድ መሄድ አልቻለም። ተረበሸ። ግርግሩ በርትቶ በመጨረሻም አምባሳደሯ እና አጃቢዎቿ በፖሊሶች ታጅበው በመጡበት እግራቸው ተመልሰዋል።

 
.The police came out with three cars and six policemen and stopped a meeting of Tasta bydelshus where the atmosphere was becoming so very irritably among the more than 300 attendees.
OFF: toril RisholmPublished: April 20, 2013 7:51 p.m. Updated: April 20, 2013 8:13 p.m.

The 300 attendees were Ethiopian asylum seekers or people with Ethiopian background. The police feared that it would get completely out of control when people in the audience went to the hard verbal confrontation against two representatives from the Ethiopian Embassy in Stockholm who had called for and chaired the meeting.The police gave the first message that all protesters to leave the meeting while the two embassy people and their potential supporters can be seated. This denied the attendees protesters, and several feared it would come to an open confrontation between police and people in the audience. Then, specific efforts manager Øyvind Sveinsvoll of Rogaland police to stop the meeting and clear the room.It was a wise decision, said several of those present protesters. They did not want the two embassy people should be left as "victors" while they were evicted.- Our goal was to stop the meeting.

Wednesday 17 April 2013

“ማሪያም ነኝ” ባዩዋ ተፈረደባት


በአሸናፊ ደምሴ
የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች በመንቀሳቀስ ሰዎችን በማታለል “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌያለሁ፤ ከሞትም ተነስቻለሁ፤የወለድኳቸውንም ልጆች ያገኘሁት በመንፈስ ነው”
ስትልና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል በሚል የሰዎችን የግል ሀብት ለራሷ ስታደርግ ደርሼባታለሁ ሲል ክስ የመሰርተባት የ34 ዓመቷ ትዕግስት ብርሃኑ ወ/ጊዮርጊስ፤ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል ችሎት ፊት ቀርባ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ በ2 ዓመት
ከ4 ወራት ፅኑ እስራትና በአንድ ሺ ብር የገንዘብ መቀጮ እንድትቀጣ ሲል ባሳለፍነው ሳምንት ወሰነ።
እንደአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ከሆነ ግለሰቧ በአራት የተለያዩ ክሶች የተወነጀለች ሲሆን፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
“ለሰው ህይወት ማለፍ ሳቢያ ነች” ሲል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ክስ ያልተሟላ ነው ሲል ውድቅ ሲያደርገው በተቀሩት
ሶስት ክሶች ግን ጥፋተኛ ነች ብሎ እንድትከላከል ብይን ሰጥቶ ነበር።
ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባለችበት አንደኛ ክስ በየካቲትና በመጋቢት ወራት ውስጥ 1999 ዓ.ም የማይገባትን ጥቅም

ለማግኘት አስባ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 21 ልዩ ቦታው ኪዳነምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከ300 በላይ ሰዎችን በመሰብሰብ “እኔ ማርያም ነኝ፤ እንደኢየሱስም በጅራፍ ተገርፌ፤ ከሞትም ተነስቼያለሁ” የሚል የሀሰት ወሬ በመንዛትና የዓለም ፍፃሜ ደርሷል ንብረት አያስፈልግም በሚል ያላችሁን ንብረት አምጡ ስትል ከተለያዩ የግል ተበዳዮች ጥሬ ገንዘብና ወርቅ የተቀበለች ሲሆን፤ በአጠቃላይም 40ሺ ብር ለግል ጥቅሟ አውላለች ሲል በክስ መዝገቡ ያስረዳል።
እንደአቃቤ ህግ ቀጣይ ክስ ደግሞ ተከሳሿ በሰኔ 1 ቀን 1999 ዓ.ም በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 16 ልዩ ቦታው ላምበረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 50 የሚደርሱ ሰዎችን በመያዝ ወደደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በመጓዝ ወንጭ ገዳም ተብሎ ወደሚጠራው መንፈሳዊ ቦታ በመውሰድ በፆምና ፀሎት ሰበብ አብረዋት የነበሩት ሰዎች ለአምስት ቀናት ምግብ እንዳይበሉ በማድረግ እንዲዳከሙና ለከፋ ጉዳት እንዲዳረጉ አድርጋለች ሲል በክሱ ያትታል።
በሌላም በኩል ግለሰቧ በጥር 24 ቀን 2003 ዓ.ም በልደታ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 ልዩ ቦታው ተክለሃይማኖት ቤተ-ክርስቲያን ቅጥር ውስጥ ወደ 20 የሚጠጉ ህፃናት ልጆችና ሴት ተከታዮቿን በመያዝ፣ “እኔ ማርያም ነኝ፤ ልጆቼን የወለድኳቸውም በመንፈስ ነው እንጂ ከወንድ ጋር ተኝቼ አይደለም” በማለትና ተከታዮቿም እርሷ ማርያም ነች።
ሞታም ተነስታለች እንዲሁም 40 ቀን ያለምግብ ትፆማለች በማለት ሀሰተኛ ወሬዎችን እንዲነዙ በማድረግ ስታስተምር እንደነበር ከፖሊስ የምርመራ መዝገብ ደርሶኛል ያለው ዐቃቤ ሕግ፤ በዚህም ምክንያት በቤተ-ክርስቲያኗ ቅጥር ግቢ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ምዕመናን “ ሀሰት ነገር አትናገሪ” ሲሉ በመቃወማቸው ወደሁከት ውስጥ እንዲገቡ ያደረገች በመሆኑ በፈፀመችው የሀሰት ወሬዎችን በማውራትና ህዝብን በማነሳሳት ወንጀል ተከሳለች ይላል።
ጉዳዩን ሲመረምረው የቆየው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 6ኛ ወንጀል ችሎትም የዐቃቤ ሕግን ክስ ተከሳሿ ማስተባበል ባለመቻሏ ጥፋተኛ ሆና አግኝቻታለሁ ሲል፤ መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በ2 ዓመት ከ4 ወር ፅኑ እስራትና በ1000 ብር እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል።¾
ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ

Thursday 11 April 2013

ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት /ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን/

 ------------
አዬ፣ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
... እስከመቼ ድረስ እንዲህ፣ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን፣ ሰቀቀኗን፣ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺእኮ ማንም የላት….
አውሮጳ እንዲሁ ትናጋዋን፣ በፋሽስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ፣ ተምሳ፣ በስብሳ
ሂትለራዊ እባጭ ጫንቃዋን፣ እንደኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ፣ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት
ሥልጡን፣ ብኩን፣ መፃጉዕ ናት፤ ….
እና ፈርቼ እንዳልባክን፣ ሲርቀኝ የኃይልሽ ውጋገን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፣ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፣ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን፡፡
አዎን፣ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ፣ ተፈትቶ እንዳይከዳት ሠጋሁ …
አዋጅ፣ የምሥራች ብዬ፣ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማኅፀን አርፌ
ከአፈርዋ አጥንቴን ቀፍፌ
ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟ ወዜን ቀፍፌ
በሕፃ እግሬ ድሄባት፣ በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ፣ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ፣ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ፤
በጋው የእረኛ አደባባይ፣ ክረምት እንደወንዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ፣ በገደል ሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅ እና ከሚዳቋ፣ ከዥግራ ጠረን ስተሸሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ፣ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር ሩጫ ስገጥም፣ ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከናዳ ጫፍ ሣር አጨዳ፣ ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎች ራት፣ ለማታቸው ትንሽ ድርቆሽ
ለግልገሌ ካውሬ ከለል
እማሳው ሥር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል፣ ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ፣ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሣር ሲለመልም፣ ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከንበል ሲል፣ ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ፣ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ፣ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ …..
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመ ብርሃን እረሳሻት?
ያቺን የልጅነት የምሥራች? የሕፃንነት ብሥራት
የሣቅ የፍንደቃ ዘመን፣ የምኞት የተስፋ ብፅአት
ያቺን የልጅነት እናት?
አዛኚቱ እንዴት ብለሽ፣ ጥርሶችሽን ትነክሺባት?
ሥሜን በሥምሽ ሰይሜ፣ ባገልግሎትሽ ስዋትት
ከዜማ ቤት እቅኔ ቤት፣ ከድጓ ቤት እመጻሕፍት
ካንቺ ተቆራኝታ ዕድሌ፣ ካንቺ ተቆራኝታ ነፍሴ
ከቀፈፋ ደጀሰላም፣ ከቤተልሔም ቅዳሴ
እኰ፣ ቀፎ ዳባ ለብሶ
ቅኔ ዘርፎ ግስ ገሦ
መቅደስ አጥኖ ማኅሌት ቆሞ
በልብስ ተክህኖ አጊጦ፣ በብር አክሊል ተሸልሞ
እመ ብርሃን ያንች ጽላት፣ ነፍስ ላይ በእሳት ታትሞ
የመናኒው ያባ ተድላ፣ ረድ ሆኜ፣ አብሮኝ ታድሞ
ሕይወቴ እምነትሽን ጸንሶ
ሥጋ ፈቃዴ ተድሶ
ለሕንፃሽ መዲና ቆሞ፣ ለክብርሽ ድባብ ምሰሶ
ሥሜን በሥምሽ ሰይሜ፣ ሆነሺኝ የእምነቴ ፋኖስ
ለዋዜማሽ ግሸን ማርያም፣ ለክብርሽ ደብረ ሊባኖስ
ስሮጥ፣ በወንበሩ አኖርሺኝ፣ በአንበሳው በቅዱስ ማርቆስ
ታዲያ ዛሬ ኢትዮጵያ ስትወድቅ፣ ከምትሰጪኝ የፍርሃት ጦስ
ምነው በረኝነት እድሜ፣ ዓይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥንብ አንሳ ከንፎ፣ ወርዶ በጨለማ በርኖስ
ባክሽ እመ ብርሃን ይብቃሽ፣ ባክሽ ምስለ ፍቁር ወልዳ
ጽናት ስጪኝ እንድካፈል፣ የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ፣
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ፣ ከነደደችበት እቶን
የሷን ሞት እኔ እንድሞታት፣ ገላዋ ገላዬ እንዲሆን፡፡ …..
አዎን፣ ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ፡፡ …..
,,,,,,,,,,,,,,,, /ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን/
/ከጴጥሮስ ያቺን ሰዓት ፣ ታሪካዊ ተውኔት የተቀነጨበ/
ምንጭ፤ “ታሪካዊ ተውኔቶች” ጸጋዬ ገብረ መድኅን
አሳታሚ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ፤ 2003ዓ.


Tuesday 9 April 2013

ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ ታወቀ !!!

22
ዛሬ ማምሻውን ከወደ ባህርዳር አካባቢ የተሰማው ወሬ በርካቶችን እያስገረመ እና እያስደነገጠ ይገኛል፡፡በርካታ ኢትዮጲያውያን በእጅጉ የሚያደንቁት፣ ነገር ግን በደርግ መንግስት ታፍኖ የደረሰበት  ያልታወቀው ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ ከሚገኙ ደሴቶች አንዱ በሆነው የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ውስጥ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ቀደም ሲል በይስማእከ ወርቁ ደራሲነት የምናውቃቸው ዴርቶጋዳ፣ራማቶሃራ፣ዣንዥድ እና ተልሚድ የተሰኙ ስራወች የደራሲ በአሉ ግርማ መሆናቸው እና በይስማዕከ ወርቁ አማካኝነት የወጡ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ይሄ ወሬ ከተሰማ በኋላ በርካታ የባህርዳር ነዋሪወች የዳጋ ደሴትን ያጨናነቁ ሲሆን የአዲስአበባና የሌሎች የሃገራችን ክፍል ነዋሪዎችም ነገ በማለዳ ወደ
ባህርዳር ጉዞ ለማድረግ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ መኪና እና የፕሌን ትኬቶች ተሽጠው ያለቁ ሲሆን የኢትዮጲያ አየር መንገድም ነግ እና ከነገ በስቲያ ወደ ሌሎች የሃገራችን ክፍሎች የሚደረጉ በረራዎችን ሰርዞ ጉዞ ወደ ባህርዳር ብቻ እንደሚያደርግ ተነግሯል

Monday 1 April 2013

አዜብ መስፍንና የቼኮሌቱ ታሪከ


Azeb Mesfin for refusing to leave the palace.
ሰለሞን ታረቀኝ
ድሮ ነው አሉ፤ አንዲት በናዝሬት ትምህርት ቤት ትማር የነበረች ተማሪ ጥርሷን ጣፋጭ ጨርሶት ነበርና ወላጆቿ በፍጹም ቼኮላት እንዳትበላ ያስጠነቅቋታል፤ ከዚያም አንድ ቀን አንዲት ጓደኛዋ ቼኮሌት አምጥታ ኖሮ በእረፍት ሰዓታቸው ጓደኛዋ የሰጠቻትን ጥቂት ቼኮሌት ታናሽ ወንድሟ እንዳያሳብቅባት ተደብቃ ስትበላ ያ ከውካዋ ወንድሟ ድንገት ቢደርስባት እጅዋ ላይ የቀረውን በድንጋጤ ወደ አፍዋ አስግብታ ቁልቁል መስደድ፤ ወንድምየውም ቼኮሌት እንድትሰጠው ቢጠይቃት እንዳለቀባት ትነግረዋለች። እሱም ይናደድና አሳብቃለሁ ብሎ ያስፈራራታል። ከዚያም ከትምህርት ቤት ወጥተው ቤታቸው እንደደርሱ ወንድሟን ለመቅደም ብላ ማንም ሳይጠይቃት፥ እማዬ፥ እማዬ እኔ እኮ ዛሬ ቼኮሌት አልበላሁም አለች ይባላል።
የቀድሞዋ ቀዳማዊትም እንዲሁ ቀደም ቀደም ብላ ሳትጠየቅ ተክለፍልፋ ለሁለተኛ ጊዜ ባሌ የ፮ ሺህ ብር የወር ደመወዝተኛ፥ ከዚህም ተቆራርጦ ፬ ሺህ ብር ያገኝ ነበር ስትል አበሰረችን። የቼኮሌቱ አይነት መሆኑ ነው።
ሁላችንም እንደምናስታውሰው ከጥቂት ዓመታት በፊት የትንሳኤ ሬድዮ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሀብት የዘረፉ የወያኔ መንግስት ባለስልጣኖችን፥ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ የዘረፉትን ሀብት መጠንና ገንዘቡን ያስቀመጡበትን አገር ጭምር ይፋ አድርጎ ነበር። በትክክል ካስታውስኩ አቶ መለስ ዜናዊ በማሌዥያ በባንክ ፬፪ (አርባ ሁለት) ሚሊዮን ዶላር እንዳስቀመጡ ገልጾ ነበር። ይህንን ተከትሎ የመለስ ዜናዊ መንግስት የትንሳኤ ሬድዮን አሜሪካን አገር በቨርጂኒያ ስቴት በሚገኝ ፍርድ ቤት በስም ማጥፋት ወንጀል በሚል የክስ ፋይል መስርቶ እንደነበርና በሁዋላ ግን የሚያስከትለውን መዘዝ በመፍራት ይመስላል ክሱን መሳቡ (ዊዝድሮው ማድረጉ) ተነግሮ እንደነበር ይታወሳል።
ይህ ሲገርመን ከጥቂት ቀናት በፊት አንድ በኢሳት ሬድዮ ቀርቦ የነበረ ጋዜጠኛ እንዳመለከተው ሴሌብርቲ ኔትወርዝ የተባለ ድረ ገጽ አቶ መለስ ዜናዊ ያላቸው ሀብት ፫ (ሶስት) ቢሊየን ዶላር እንደሆነ ያሳያል። ይህንን በርግጥም ማንም በተባለው ድረ ገጽ አድራሻ በ http://www.celebritynetworth.com/ ሊመለከተው የሚችል ዘገባ ነው። ድረ ገጹ በዓለም ላይ ያሉ ታዋቂ ሰዎችንና እንደ እነ አቶ መለስ ዜናዊ ያሉ አምባ ገነን መሪዎች ያላቸውን ሀብት የሚዘግብ በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አላቸው ተብሎ የተዘገበው ከፍተኛ ሀብት ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠውና ሊመረመር የሚገባ ጉዳይ ይመስለኛል።
እዚህ ላይ በተለይም ኢትዬጵያውያን ጋዜጠኞች፤ የሕግ ባለሙያዎች፤ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራት እንዲሁም ይህን ጉዳይ ለማጣራት አቅምና ችሎታ ያላቸው ግለሰቦች በትንሳኤ ሬድዮም ሆነ በሴሌብሪቲ ኔትወርክ የተመለከቱትን የወያኔ ባለስልጣኖች የተካባተ ሀብት መጠንና የሚገኝበትን ስፍራ መርምረውና አጣርተው ለሕዝብ ማጋለጥ ያለባቸው ይመስለኛል።
እንደሚታወቀው ባገራችን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሙስና በከፍተኛ ደረጃ መስፋፋቱና ያገራችን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመዘረፍ ላይ እንደሚገኝ የአደባባይ ምስጢር ነው። ትናንት ምንም ያልነበራቸው የዛሬዎቹ ባለጊዜ የወያኔ ባለስልጣኖች ባገር ውስጥ የባለ ብዙ ሕንጻዎችና ሌሎችም ንብረቶች ባለሀብቶች መሆናቸው በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች መገለጹ ይታወሳል። ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተለያየ ጊዜ እንደዘገቡት ካገራችን ብዙ ቢሊዮን ዶላር እንዲሸሽ መደረጉን መግለጻቸው ያገር ሀብት ዘረፋው በከፍተኛ ደረጃ መስፋፋቱን በግልጽ የሚያመለክት ነው።
የቀድሞዎቹ አምባገነኖች የግብጹ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክና የሊቢያው ኮሎኔል ሙዓመር ጋዳፊ በውጭ አገሮች በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት አካብተው እንደነበርና፤ የስርዓታቸውን መገርሰስ ተከትሎ የያገራቸው ሕዝቦች ይህን የተዘረፈ ሀብት ለማስመለስ እንደሚንቀሳቀሱ መገለጹ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ሁኔታ እኛም ኢትዮጵያውያኖች እነዚህን ለ፪፩ ዓመታት እንደመዥገር ከሕዝባችን ተጣብቀው የዘረፉትን ቋሚም ሆነ ተንቀሳቃሽ ሀብት በሚቻለው አቅም ተከታትለን ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ማጋለጥ እንዳለብን ይሰማኛል። ይህም ወደፊት ከአይቀሬው የስርዓቱ መገርሰስ በሁዋላ ሀብታችንን ለማስመለስ ለምናደርገው ጥረት እንደ ቅድመ ዝግጅት ሊያገለግል እንደሚችል አምናለሁ።
ኢትዮጵያ አገራችንን እግዚአብሔር ይጠብቅልን።
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር።

Friday 29 March 2013

Cheers and congratulations to Endale Getaneh

Cheers and congratulations to Boschendal Getaneh, finally, after 5 years and 5 months have been granted a residence permit? In the process, I congratulate Norway; continue happily so - grant more political permits to Ethiopian refugees, and relation to the severity and consequences of it in relation to Ethiopia.

It sings Endalen Getaneh during last year's memorial ceremony in Oslo for the victims of the great massacre in Addis Ababa in 2005. A natural protest against the regime under TPLF and Meles Zenawi did not let the opposition, which was heavy with votes during elections, led to an enormous tragedy, that many of the asylum seekers from Ethiopia are highly influenced by. 193 people were killed, and around 20,000 were imprisoned and tortured. I have been told that the families of the victims were forced to pay the bullets that killed their lost close.

About massacre: http://news.bbc.co.uk/2/hi/6064638.stm

Dear Norway, please be humble, let more of those in need of protection have become. Keep in mind that many refugees have horrific stories behind them, which drives them to flee.


Nyhet!Logg deg på og klikk på stjernen for å lagre denne oversettelsen i uttrykkslisten din.
http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2013/03/26/refugee-from-ethiopia-sings-in-front-of-parliament-in-oslo/

Refugee from Ethiopia sings in front of Parliament in Oslo

Endal Getaneh, a refugee from Ethiopia sings a hymn of hope in front of Parliament in Oslo.
Norway is the first and only European countries signed an agreement on the return of refugees to the authoritarian regime in Ethiopia. Amnesty International, Human Rights Watch and several other human rights organizations in a strongly critical of the agreement.
Many of the Ethiopian refugees are actively politically in opposition to the Ethiopian regime. They fear for their lives, torture and imprisonment forcibly returned to Ethiopia

Wednesday 27 March 2013

ማልዶ የወጣ Maldo Yewta


 የዲያቆን አሸናፊ መንን ገጽ

ማንም ሰው ለእግዚአብሔር ኢትዮጵያ ወይም ኬንያ ልወለድ ብሎ አሳብ አላቀረበም፡፡ ሙሉ በሙሉ ፈቃዱ የእግዚአብሔር ሆኖ ራሳችንን በዚህ አገርና በዚህ ቤተሰብ ውስጥ አግኝተነዋል፡፡ የምንኖርበትን አገር፣ የምንወለድበትን ቤተሰብ የመረጠልን ምርጫ አዋቂው እግዚአብሔር ነው፡፡ በእግዚአብሔር የሆነልን ነገር መልካም ነው፡፡ ሰው ሆነን መፈጠራችን፣ መዳናችን፣ ክርስቲያን መሆናችን.. የሆኑልን መልካም ነገሮች ናቸው፡፡ በእግዚአብሔር ወደፊት የሚሆነውም መልካም ነው፡፡ ከእግዚአብሔር እጅ የምንቀበለው ነውር፣ ነቀፋ፣ እንከን፣ ነቁጥ የሌለበት ነው፡፡

ልጆቻችን የወደዱን በብዙ መልካምነታችን ነው፡፡ የትዳር ጓደኞቻችን የመረጡን በቁምነገራችን ነው፡፡ መሥሪያ ቤታችን የተቀበለን በሙያችን ነው፡፡ ወዳጆቻችን የወደዱን በማረካቸው ነገራችን ነው፡፡ ወላጆቻችን የወደዱን የእነርሱ ስለሆንን ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን የወደደን ስለ እኛነታችን ነው፡፡

እኛን ለቤተሰባችን፣ ቤተሰባችንን ለእኛ የሰጠ እግዚአብሔር ነው፡፡ ወላጆቻችን ያዩንና የወደዱን ከተወለድን በኋላ ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ዓለም ሳይፈጠር በአንድ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ዓይቶናል /ኤፌ. 1÷4/፡፡ በማኅፀን ደም አርግቶ፣ አጥንት ሰክቶ ፣ ጅማት አዙሮ፣ ሥጋ አልብሶ፣ እስትንፋስ ዘርቶ ሠርቶናል፡፡ በማኅፀን በስውር የመገበንም እርሱ ነው፡፡ ወላጆቻችን የሚያውቁን ስንወለድ ነው፣ እግዚአብሔር ግን የሚያውቀን ዓለም ሳይፈጠር ነው፡፡ ነቢዩ፡- “ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ” ያለው ለዚህ ነው (መዝ. 138÷ 15-16)፡፡


Saturday 23 March 2013

የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ - ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን

 



የቴዎድሮስ ስንብት ከመቅደላ

ተስፋ ባጣ ምድረ በዳ
ያንድ እውነት ይሆናል ዕዳ፡፡
እና ትንፋሼ አልሆነሽም፥ ሆኜብሽ መራር መካሪ
“ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ፣”
እውነት ላንቺ መች ተስፋ ናት፥ ጉስቁል ልሳንሽን ነክሳሽ
ክንድሽን ካዘለ ቅርስሽ፥ መጠላለፍ ሲሆን እጣሽ
ከእንግሊዝ የሞት አማልክት፥ መተናነቅ ሲሆን ድርሻሽ
መልመጥመጡ፥ መሽቆጥቆጡ፥ መስሎሽ ድንገት የሚያዋጣሽ
የኔ እውነት ሆነብሽ ዕዳሽ ፡፡ …..
ወራሪም ፈጣሪን ላያቅ
የጣለውን በስሏል እንጂ፥ ወድቋል ብሎ ግፉ ላያልቅ
መች ትተርፊያለሽ ኢትዮጵያ፥ ሕዋስሽ አብሮኝ ካልሠራ
አንገትሽ ብቻ መቅደላ፥ አፋፍ ወጥታ ብታበራ
የቀረው ሠራ-አከላትሽ፥ በየጥሻው ተዘርሮ
ከአባት በወረሽው ንፍገት፥ ነብዞ ደንዝዞ ተቀብሮ
ባጉል ወጌሻ ታጅሎ
እጅና እግርሽ ታሽቶ ዝሎ
እኔን ለጥንብ አንሳ ጥሎ፤
ከደቀቀ ከደከመ፥ ክንድሽ አልነሣ ካለ
ሞት እንጂ ለኔስ ምን አለ?.....
ሆኖም ጐስቋላ አልምሰልሽ፥ የሚያዝንልኝ አልፈልግም
ጠላትሽን በክንድሽ እንጂ፥ በእንባሽ ወዝ ባላሸንፍም
የልቤን ፍቅር በሰተቀር፥ እማወርስሽም ውል የለኝ
የኮሶ ሻጭ ልጅ ደሃ ነኝ፡፡ …..

ደሞም ያላንቺ የለኝና
ድሌም የተሰፋ ጐሕ ባይሆን፥ ከሞት ጋር ትግል ነውና
ከዚህ ሌላ ትእዝብት ውረሽ፥ ሳይነጋ እንዳስመሸሽብኝ
ጊዜና ትውልድ ይፍረደን፥ ሳልነቃ እንዳስረፈድሽብኝ፡፡
ያም ሆኖ ለራስሽ እንጂ ለኔ ከቶም አታልቅሺ
አንቺ ነሽ እንባ እምትሺ፤ …..
የእምነትሽ መተሣሰሪያ፤ ውልሽ ለተላቀቀብሽ ላንቺ ነው እንባ እሚያሰፈልግሽ፡፡
አዎን፥ ይኽን እወቁልኝ፥ ምስክር ሁኑኝ ሰማዕታት
ለሷ ነው እንባ የሚያስፈልጋት፡፡
ከጠላቶቹ ጭብጥ ውስጥ፥ ትንፋሼን በጄ ስነጥቃት
ሞቴን ከመንጋጋቸው ውስጥ፥ መንጭቄ እኔው ስሞታት
ላገሬ ብድር ልከፍላት
የነፈገቺኝን ፍቅር፥ በራሴ ሞት ልለግሳት!.....ያኔ ነው እንባዋ የሚያጥራት፡፡
ሰለዚህ ለራስሽ እንጂ፥ ልቅሶሽ ለኔ ምን ሊረባ
ብቸኛ ምሬት ነው ኃይሉ፥ ወኔ መሰለቢያው ነው እንባ፡፡
እና ለራስሽ እዘኚ
እንጂ ከቶ ለኔ እትባክኚ፡፡ …..ይልቅስ ተረት ልንገረሽ፥ የተላከ ከእንግሊዝ ዘንድ
እጅህን ስጥ አለኝ ፈረንጅ፥ እጅ ተይዞ ሊወሰድ፥
ምን እጅ አለው የእሳት ሰደድ?አያውቅም ክንዴ እንደሚያነድ፡፡ …..ዳዊት እንዲያ በበገናው፥ ማልቀስ ማላዘን መያዙ
ይኽ የጐልያድ ውላጅ፥ ቢበዛበት ነው መዘዙ
ምንጩ እንደአሽን እየፈላ፥ አገሩን ምድሩን ማንቀዙ
ቸግሮት ነው፥ መጋፈጡ፥ ከስንቱ መወናጨፉ
በባላንጣው ሳቢያ ምክንያት፥ የራሱን ወገን ማርገፉ፡፡ …..ታድያ እንግዲህ አንቺ ኢትዮጵያ፥ እኛስ ልጆችሽ ምንድነን
አመንኩሽ ማለት የማንችል፥ ፍቅራችን የሚያስነውረን
ዕዳችን የሚያስፎክረን
ግፋችን የሚያስከብረን
ቅነነት የሚያሳፍረን፥ ቂማችን የሚያስደስተን
ኧረ ምንድነን? ምንድነን?አሜከላ እሚያብብብን፥
ፍግ እሚለመልምብን፥
ከአረም ጋር ያፈራን ጊንጦች፥ ከእንክርዳድ ያልተለየን ዘር
ግርዱ ከምርቱ ተማጥቆ፥ ከቶ ያልተበራየን መከር
ምንድነን? ምንድነን እኮ?አረጋዊውን ባንቀልባ፥ ከምንሽከም እንኮኮ
ጐልማሳውን ከወኔ ጣር፥ ካልፈታን ከፍርሃት ምርኮ
እንደ ወዶ ገባ ወደል፥ መጠለሉን ከሴት ታኮ …..ካቃተን፥ ምንድነን እኮ?.....አየሽ እንቺ እማማ ኢትዮጵያ፥ አየሽ አንቺ እናት ዓለም
ቃል የእምነት ዕዳ ነው እንጂ፥ ያባት የናት እኮ አይደለም፡፡ …..

ያም ይቅርና መርዶ ላርዳሽ፥ ስሚው እኔ እንደሰማሁት
እርም በልተሽ ከምትቀሪ፥ ስሚው ገብርዬንም ጣሉት፡፡ …..እስቲ እንግዲህ በይ ፍረጂኝ፥ ከእንግዲህ እኔ ፍሬ አላይም?
ዘርቶ መቃም ወልዶ መሳምአባባል ለኔ አይባልም?እስቲ ገብርዬን መሰል ዘር፥ ፍሬው ከቶ አይለመልምም?እኔስ ዘር ዘራሁ አልልም? …..ምነው ፍንጭትክን ገብርዬ፥ ያን ፍንጭትክን አጨለሙት
እንደ ሬት ልግ አከሰሉት
እንደ ኮሶ አስመረሩት? ......ከጡቶችሽ እቅፍ ነጥቀው፥ ከማኅፀንሽ ፍቅር ቆርጠው
እውነትን ሲገሉ እንዲህ ነው፥ ፈገግታውን አጨልመው፡፡
እስቲ እባክህን ገብርዬ፥ የዛሬን እንኳ ስቀህ ሙት
በዕድል ጥቀርሻ እንደአጀሉት
እንደ ወላድ ጣውንት ጡት
አርማ ጉሳ እንደቀለሙት
ፈገግታህን አያጥቁሩት፡፡
እምቢ በላቸው ገብርዬ፥ በአባት ሤራ እንዳስገዘቱት
በመሃላ እንዳሳገዱት
የነፍሰህን ጮራ ብርሃን፥ ከገጽህ እንደቀበሩት
ዘለዓለም ላያጨልሙት
ወንድምዬ እምቢ በላቸው፥ የዛሬን እንኳ ስቀህ ሙት፡፡ …..ያለፈ ጥረታችንን፥ ሳስታምመው ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ፥ ያልሞከረነው ነው እሚቆጨኝ፡፡
እና በኔ ይሁንብህ፥ መጣሁ፥ ስቀህ ተቀበለኝ
እኔም ላዋይህ አድምጠኝ …..እጅህን ስጥ አለኝ ፈረንጅ፥ እጅ ተይዞ ሊወሰድ
ምን እጅ አለው የእሳት ሰደድ?አያውቅም ክንዴ እንደሚያነድ፡፡ …..


ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
እሳት ወይ አበባ