"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 23 August 2012

አልሸባብ እና ግብፅ ሆይ፤ የሞቱት መለስ እንጂ ኢትዮጵያ እንዳልሆነች ኮስተር ብዬ እነግራችኋለሁ።


የጠቅላይ ሚኒስትሩን መሞት ቀድመው የተረዱት የግብፅ ባለስልጣናት “ከቀጣዩ መንግስት ጋር በአባይ ጉዳይ ላይ መግባባት ይኖረናል ብለን እናስባለን!” ሲሉ በደስታ መናገራቸውን ሰምተናል።
አሁን በቅርቡ ደግሞ አልሸባብ ሆዬ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት መደሰቱን ገልፆ ከዚህ በኋላ በእርግጠኝነት ኢትዮጵያ ትበታተናለች ሲል “ቅዠቱን” ጮቤ እየረገጠ ሲነግረን፤ መቼም ጆሮ አልሰማ አይልምና አድምጠናል።
ይሄ ስለ ኢትዮጵያውያን ማንነት ጠንቅቆ ካለመረዳት የመጣ የግንዛቤ ችግር የፈጠረው ፈንጠዝያ ነው።
እርግጥ ነው ባለፉት ግዜያት በተለይም አንዳንድ የኢህአዴግ ዋና ካድሬዎች የአቶ መለስን ስዕል ከኢትዮጵያችንም በላይ አጉልተው ለማሳየት መከራቸውን ሲያዩ እኛም “ተዉ ይሄ ነገር ጥሩ አይደለም” እያልን በመምከር አበሳችንን ስናይ ከርመናል።
በተለይ ከሆነ ጊዜ በኋላ የአቶ መለስ ዜናዊ ፎቶግራፍ በየአደባባዩ እና በየቢሮው እየተሰቀለ ሀገሪቷ የእርሳቸው ሳሎን ቤት እስክትመስል ድረስ እጅግ የተጋነነ ስዕል ሲሰጣቸው ቆይተዋል። ከዛም በላይ “አባይን የደፈረ ጀግና!” በሚል ውዳሴ ግድቡ የእርሳቸው እና የኢህአዴግ ብቻ በማድረግ ታሪካዊ የሚባል ስህተት ሲሰራ ቆይቷል። ይህም በብዙዎች ዘንድ እርሳቸው ከሌሉ አባይም ሆነ ሌላው ልማት የሌለ መስሎ እንዲሰማቸው አድርጓል።
እንደ ምሳሌ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ አቶ መለስ ስልጣን ቢለቁስ? የሚል ጥያቄ በተጠየቁ ግዜ የመለሱትን መልስ ማንሳት በቂ ነው። ዶክተሩ መለስ ስልጣን ቢለቁ “ተተኪዎች ሀገር ያስተዳድራሉ የተጀመሩትን ይጨርሳሉ የተበላሹትን ያስተካክላሉ” ብለው አይደለም የመለሱት፤ ይልቁንም “ግድቡን ለማን ትተው…? የጀመሩትን ልማት ሳይጨርሱ ምን ሲደረግ ስልጣን ይለቃሉ…? ይሄማ አይሆንም!” ነበር ያሉት።
ይህ ግለሰብን ከሀገር በላይ አግዝፎ የማየት እና የማሳየት ችግር ትልቅ ጥፋት እንደሆነ የሚታወቀው እንዲህ ያለው ቁርጥ ቀን ሲመጣ ነው።
ይህ የተጋነነ ስዕል ነው ዛሬ አልሸባብም ሆነ የግብፅ ባለስልጣናት መለስ ከሌሉ ኢትዮጵያ የማትኖር አይነት የልብ ልብ እንዲሰማቸው ያደረገው።
አባይ የአቶ መለስ አይደለም። አባይ እንኳንስ ሌላው ቀርቶ የኢህአዴግም አይደለም። አባይ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው።
በነገራችን ላይ አባይ የተደፈረው ዛሬ በኢህአዴግ ዘመን አይደለም። ንጉስ ኃይለ ስላሴም ሆኑ ደርግ በአባይ ላይ የሰሯቸው ጥልቅ ጥናቶች ዛሬ ለተጀመረው ግንባታ መሰረት ናቸው። እንደውም በአባይ ጉዳይ ላይ ኢህአዴግ ከሚወቀስባቸው ነገሮች አንዱ እና ዋነኛው የራሱን የሆነ ወቅታዊ እና የተጠናከረ ጥናት ሳያደርግ በነዚህ የቆዩ ጥናቶች ላይ ተንተርሶ በመቻኮል ወደ ግንባታ መግባቱ ነው።
በአባይ ጉዳይ ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄዎች ቢኖሩም ቅሉ ግብፆች እንደሚያስቡት ግን ግንባታው መለስ ሲኖር የሚቀጥል መለስ ሲሞት ቀጥ የሚል አይደለም።
ባለፈው ግዜ አቦይ ስብሀት እንዳሉት፤ ከእርሳቸው በፊት ደግሞ እኛ እንዳልነው አባይን መለስ አልደፈሩትም። ኢህአዴግም አልደፈረውም። የደፈረው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። እናም “የኢትዮጵያ ህዝብ” የሚባለው በህይወት እስካለ ድረስ በዓባይ ላይ የተለየ ድርድር እና የተለየ አቋም ይኖራል ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው።
እርግጥ ነው አባይ የግብፅ ፍቅረኛ እንደሆነ እናውቃለን። እዚህ ላይ ተቃውሞ ያለው ያለመኖሩን ያኸል ኢትዮጵያ ደግሞ የሰማኒያ ሚስቱ እንደሆነች የሚጠራጠር ኢትዮጵያዊ አይኖርም። ኖሮም አያውቅም።
አቶ አልሸባብም “በእርግጠኝነት ኢትዮጵያ ትበታተናለች” በሚል የሰጠው አስተያየት ለአቶ መለስ ስንሰጠው ከነበረ የተጋነነ ስዕል ጋር ተያይዞ የመጣ ነው። በአልሸባብ ቤት ከአቶ መለስ በኋላ የኢትዮጵያ ጥንካሬ የለም። ይሄ ትልቅ ዜሮ የሚያሰጥ ግድንግድ ኤክስ ነው።
ኢትዮጵያ ድሮም ነበረች አሁንም ትኖራለች። መለስ ሲኖሩ የሚጠብቅ መለስ ሲሞቱ የሚረግብ ጥንካሬ የለንም።
ውድ የኢህአዴግ መንግስት ተቃዋሚዎች ሆይ በየስትራቴጂ መግለጫዎቻችሁ ላይ ስለ ኢትዮጵያ ታላቅነት መመስከር ያለባችሁ ግዜ ላይ እንዳላችሁ አመላክቶኛል።
ውድ የኢህአዴግ ደጋፊዎች በየ ሀዘን መግለጫዎቻችሁ ላይ የሞተው መለስ እንጂ ኢትዮጵያ እንዳልሆነች መመስከር ያለባችሁ ግዜ ላይ እንዳለባችሁ አመላክቶኛል።
“ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም!”

Tuesday 21 August 2012

Ethiopia: Bereket Simon cooking information?


Who was cooking information in Ethiopia rather confirming the inevitable?

Berhanu Tesfaye (chillalo@gmail)

“Procrastination is a theft of time”  was the first proverb I read next to his bed on the wall when he was a student and I do not know exactly till the 2005 election time that Meles procrastinate things to mend and bend things. It was this time he tried to negotiate till the regional governments were set up so that he assemble the rubber stamp parliament to decide what he want.

But it also served as a proverb even he was dead even-though some were telling us that he was advising the Sudan conflicts,having vacation in an specified town or he is fit as a horse except exhaustion. Some said government issued communique were right and the truth and what we learn from was that TPLF led government was accumulating lies after lies either fabrication news and figure to lie 80 million Ethiopians in order to loot and devastate the country.

Lastly may be they are short of paying the cost of the freezer and have to disclose that he is done and dusted.

The goal is not his death but we Ethiopians have struggle to bury this ethnic based poison with him. We have to come hand in hand to strengthen our struggle to bring democratic Ethiopia in the aftermath.

The tears of Ethiopians have be answered with help OG the Almighty.

ሃይለማርያም ደሳለኝ “በሪሞት የሚሰሩ” ጊዜያዊ ጠ/ሚ/ር ሆኑ


ሃይለማርያም ደሳለኝ “በሪሞት የሚሰሩ” ጊዜያዊ ጠ/ሚ/ር ሆኑ



ሃይለማርያም ደሳለኝ በብርሃኔ ገብረክርስቶስናእና በስዩም መስፍን የሚንቀሳቀሱ ባለሪሞት ኮንትሮሉ ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስተር ሆነው ተሾሙ። በሕወሓት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ ከመግባቱም በላይ የስልጣን ሽኩቻውም እያየለ ነው የሚሉ መረጃዎች እየወጡ ነው። ኢትዮጵያም በታሪኳ በሶስት ቦታ ሪሞት ኮንትሮል ሆኖ የሚያገለግል ሰው አግኝታለች።
ከአንድ ቀን በፊት የአቶ መለስ ዜናዊ አስከሬን፤ ከውጭ አገር እንዲገባ ተደርጎ በቦሌ ተርሚናል የሬሳ ማቀዝቀዣ ክፍል ውስጥ ተቀምጦ እንደቆየ የኢትዮጵያ ሚድያ መድረክ EMF አጋለጠ። ኢቲቪ አቶ መለስ የሞቱት ትናንት እንደሆነ አድርጎ መዘገቡ ዳግመኛ ውሸት መሆኑንና መለስ ከሞቱ መቆየታቸውን በርካቶች እየገለጹ ይገኛሉ።
እንደ ኢትዮጵያ ሚድያ መድረክ ዘገባ የመለስ ዜናዊ ዜና እረፍት ከተሰማ በኋላ፤ ልጆቻቸውን በመለስ አስተዳደር የተነጠቁ ወላጆች፤ ፍትህ አጥተው በእስር እና በስደት ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ደስታቸውን ሲገልጹ፤ ቀኑ የጨለመባቸው የኢህአዴግ ወገኖች ደግሞ ሆድ ብሷቸው ሲያለቅሱ ውለዋል።

Breaking News: Ethiopia declares Meles Zenawi dead




(OPride) After months of rampant online rumors and speculations about his health and whereabouts, Ethiopia’s strongman of two decades, Meles Zenawi, pronounced dead. He was 57.
Born on May 8, 1955 at Adwa in northern Ethiopia, Zenawi has been the prime minister of Ethiopia for nearly 17 years. Prior to that, he served four years as the president of Ethiopia’s transitional government. The former rebel-leader dropped out of Addis Ababa University’s Medical School, where he studied for two years, to join the Tigray Peoples Liberation Front in 1974. He has been the chairman of both the TPLF and the ruling coalition, Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Front, since 1989.
After the highly disputed 2005 election, Zenawi consolidated his grip on power acting against his critics without impunity. When his party won 99.6 percent of seats in the 2010 parliamentary election, many warned against the emergence of a strong one-man rule system. Zenawi’s regime has been widely criticized in recent years for using draconian laws to stifle free press and the civil society. Earlier in July , Ethiopia’s kangaroo court handed down heavy sentences to 24 dissidents, including prominent journalist Eskidner Nega. The country’s only functioning “media”, the Ethiopian Television and Radio, serve as megaphones for those in power.

Monday 20 August 2012

የህወሃት አመራር አባላት አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ላይ ናቸው በረከት ስምኦን ስብሃት ነጋን ከስራው አገዷቸው !

በሰሞኑ የኢትዮጵያን አመራሮች እና በህወሃት የቀድሞው አመራር አካል አቶ ስብሃት ነጋ  ከፍተኛ ውጥረት ሲኖር  ባለፈው ሳምንት በዚሁ ጉዳይ ላይ መዘገባችን ይታወሳል ።በዛሬው እለት ከኢዮጵያ በደረሰን ዜና መሰረት የመገናኛ ብዙሃን ሚንስትር መስሪያ ቤት አመራር አካላት አንዱ ከሆኑት አንዱ አቶ በረከት ስምኦን የኢንፎርሜሽን ሚንስትሩ አቶ ስብሃት  ነጋ (አቦይን) ለማገድ በቅተዋል ። ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ መጠይቅን አስመልክቶ እገዳው እንደተጣለባቸው የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ ከስፍራው  ገልጾአል ።
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው የመገናኛን አፈና  ከጊዜ ወደዜ  እየተባባሰ መምጣቱን አስመልክቶ ይህ በባለስልጣኖቻቸው የሚደረገው አፈና እና እገዳ በበለጠ በግልጽ አፈናውን የሚያሳይ መሆኑን ማእከላችን ይገልጻል ። ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ከስልጣናቸው ላይ ከተለዩ ጊዜ ጀምሮ የህወሃት አባሎች መላ ቅጡ የጠፋቸው ከመሆኑ በላይ እርስ በእርሳቸው ከመባላታቸውም አልፈው የስልጣን ሽኩቻቸውን በገሃድ አውጥተውታል ። በትላንትናው እለት የኢትዮጵያን ሪቪው ድህረ ገጽ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚንስትሩ ቦታ  መተካታቸውን የዘገበ ሲሆን የአሜሪካ ባለስልጣናቶች በጠቃላይ ሚንስትሩ ቦታ ጣልቃ ገብተው ስልጣኑን እንዳስረከቧቸው መገለጹን ይታወሳል
በአሁን ሰአት የኢትዮጵያ ጉዳይ ያሳሰባቸው ኢትዮጵያኖች ስለ ሃገራቸው ወቅታዊ ጉዳይ ወቀሳ ያቀረቡ ከመሆኑም በላይ አስቸኳይ የሆነ መግለጫ ከመንግስትም ሆነ ከመላው አለም አቀፍ ተቋማት መቀረብ እንዳለበት አሳውቀዋል ። በተለይም ባሳለፍነው ሳምንት የኢንፎርሜሽን ሚንስትሩን ጨምሮ የአማራ ክልል ባለስልጣናት ስብሰባ ያደረጉ ሲሆን በዚህ ስብሰባቸው ዋነኛ አጀንዳ የሆነው በእነ አቦይ ስበሃት ነጋ ለረጅም ጊዜ ሲመራ የነበረውን የህወሃት ድርጅትን አፍርሶ በራሳቸው ቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያደርጉት ትልቅ ትግል መሆኑን ከተገለጸ በሁዋላ የህዝቡ እና የተቀዋሚ ፓርቲዎች ጠንካሬአቸውን አሳይተው ሃገራቸውን ከአስከፊ ስቃይ መታደግ እንዳለባቸው ጠቁመዋል ።

የኢትዮጵያ ቀን በኦሰሎ


የኢትዮጵያ ቀን በኖርዌ ሲከበር በእለቱ የነበረኝን ተሳተፎ ለመግለጽ ያህል ነው ይህ ፎቶ።  ከታች የሚታዩት ደግሞ በዓሉን ለማደመቀ ከስዊድን የመጡ ተወዛዋዝ ብሩክ፡ እያዩማንያዘዋል፤ፎዚያ ያሲን፤ቴድሮስ ጌትንት ሲሆኑ  በአሉን በዓል ያደረጉት የሀገራችንን ባህላዊ ውዝዋዜ በደመቀና ባማረ ሁኔታ ሰላሳዩን እጅግ በጣም አመሰግናለው።        መልካም  አዲሰ ዓመት ይሁንላችሁ ።መጭው ጊዜ  የሰላም  የደስታና ያሰባችሁትን የምታገኙበት ዓመት  ይሁንላችሁ።