"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 21 December 2012

መጪውን እሑድ - ከቅዳሴ በኋላ “ከፓትርያርክ ምርጫ ዕርቅና ሰላም ይቅደም” የምንልበት ቀን ስለማድረግ

(ደጀ ሰላም ታኅሣሥ 12/2005 ዓ.ም፤ ዲሴምበር 21/2012/ READ IN PDF)፦ ቤተ ክርስቲያናችን በመስቀልያ መንገድ ላይ እንድትቆም ያደረጉ ዋነኛዎቹ ርዕሰ ጉዳዮች ሁለት ናቸው። የመጀመሪያው ለ20 ዓመታት በውግዘት የተለያዩ አባቶች አንድ እንዲሆኑ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን፣ አንድ አስተዳደር፣ አንድ ቅ/ሲኖዶስ እንዲኖረን ለማድረግ ያልቻልነው ለምንድነው? የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ 20 ዓመት ለቆየው የአባቶች በውግዘት መለያየት ዓምድና ምልክት የነበረው የፕትርክናው ሥልጣን ጉዳይ ነው።



እንደ እግዚአብሔር ፈቃድም ይህ ልዩነቱ ሊፈታ የሚችልበት ጭላንጭል ታይቶ ነበር። ነገር ግን ይህንን የተስፋ ጭላንጭል በሚያዳፍን መልኩ በጥቂት የቅ/ሲኖዶስ አባላት ግፊት 6ኛ ፓትርያርክ ለመሾም “አስመራጭ ኮሚቴ” ተቋቁሟል። “የቤተ ክርስቲያኔ ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ምእመናን በሙሉ ውሳኔውን በጽኑዕ በመቃወም ላይ ይገኛሉ። ይህንን “ከኮምፒውተር ጀርባ”ና በስልክ የሚደረግ የኢንተርኔት ተቃውሞ መልክ ለመስጠት በመጪው እሑድ፣ ቅዳሴ ካለቀ በኋላ በየአጥቢያችን በመሰባሰብ ይህንን ሐዘናችንንና መከፋታችንን እንዲሁም በውሳኔው ማዘናችንን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ለመግለጽ መሰባሰብ ይኖርብናል።

ሰንበት ት/ቤቶች፣ ማኅበራት፣ ሰንበቴዎች እና ምእመናን በሙሉ ከሚያውቋቸው ሰዎች በመጀመር ለእሑዱ ቀጠሮ መያዝ እና የመሰባሰቡን ሁናቴ መልክ መስጠት መጀመር ይኖርባቸዋል። ዓላማችን አንድ ነው። እርሱም “ሃይማኖታችንን እና ሃይማኖታችንን ብቻ የተመለከተ ነው”። ስብስባችንን የሚጠሉ ሰዎች በፖለቲካ በማሳበብ በመንግሥት ዱላ ለማስደብደብ የሚያደርጉት ሙከራ እንደሚኖር ስለምናውቅ ከወዲሁ ለሚመለከተው ሁሉ ዓላማችንን መግለጽ እንፈልጋለን። መነጋገር የምንፈልገው ከቅ/ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አባቶች ጋር ነው። ይህንን በተመለከተ ሁላችሁም ሐሳባችሁን በመጨመርና በማስፋፋት መልክ ትሰጡት ዘንድ ደጀ ሰላም በትህትና ጥሪዋን ታቀርባለች።

ይህንን ፍፁም ሃይማኖታዊ ጥያቄ ሌላ መልክ ለመስጠት፣ ኢሕአዴግ ላይ የተነሣ ሰላማዊ ሰልፍ ለማስመሰል የሚሞክሩትን በግልጽ ከወዲሁ መልስ ልንሰጣቸው ያስፈልጋል። በሃይማኖት ስም ፖለቲካ አንነግደም። ፖለቲካውን በራሱ በፖለቲካነቱ የማራመድ ሙሉ ኢትዮጵያዊ መብት አለን። በዜግነታችን እርሱን በቦታው ማድረግ እንችላለን። አሁን የምንጠይቀው ጥያቄ ሃይማኖታዊ ነው፤ ማቅረብም የምንፈልገው ለቅ/ሲኖዶስ ነው ማለት ይገባናል።

እስካሁን ባየነው፣ ክርስቲያኑ ማንኛውንም ጥያቄ ለማንሣት ሲነሣ “በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ” ጭንቅላት ጭንቅላቱን በማለት ክርስቲያኑ እንዳይተባበር፣ እንዳይሰባሰብ፣ እንዳያውቅ፣ እንዳይጠይቅ የሚያደርጉ የተደራጁ ክፍሎች እንዳሉ ደጀ ሰላም ለማሳሰብ ትፈልጋለች። እነዚህ ሰዎች ፌስቡክን በመሳሰሉ ቦታዎች በመበተን ለሁሉም የክርስቲያኑ ጥያቄ የተጣመመ ሃይማኖት ቀመስ ማብራሪያ በመስጠት የሰዉን አፍ ያስዘጋሉ።

ለምሳሌ በተደጋጋሚ ከሚያነሷቸው አስተያየቶች አንዱ “ዋናው ጸሎት ነው፤ ሌላ ምንም ነገር አያስፈልግም” የሚል ነው። ጸሎት የሁሉ ነገር መጀመሪያና መጨረሻ ነው። ወሳኝ ነው። በጸሎት የማይለወጥ ነገር የለም። የኤርትራ ባሕር የተከፈለው፣ የኢያሪኮ ግንብ የፈረሰው፣ የአናብስት አፍ የተዘጋው ወዘተ በጸሎት ነው። ነገር ግን ጸሎት ያለ ሥራ/ምግባር ብቻውን አልነበረም። ሙሴ ከግብጽ እስከ ከነዓን ተጉዟል፣ ኢያሱ ኢያሪኮን ግንብ እየዞረ እንጂ ቁጭ ብሎ አልጮኸም፣ ዳንኤል ቀን ከሌሊት ወደ እግዚአብሔር ተማጠነ፤ ጉድጓዱ ከለከለው እንጂ። ስለዚህ “ጸሎት ብቻ” በሚል የክርስቲያኑን ልብ ከሥራ የሚያቀዘቅዙትን ልንነቃባቸው ይገባል።

ከዚህም በላይ የክርስቲያኑ ጥያቄ “አመጽ” የሆነ ይመስል ክርስቲያን አያምጽም በሚል ለማቀዝቀዝ ይፈልጋሉ። አመጽ የሰይጣን ነው። ነገር ግን ክፉ ነገርን መቃወም ግዴታችን ነው። ሰው ባንጎዳም ራሳችን ለሰማዕትነት ለማቅረብ ማን ይከለክለናል። “እክህደከ ሰይጣን” ብለን እንነሳለን። የተጣመመ ሃይማኖታዊ ትምህርት የምታስተምሩትን ነቅተንባችኋል እንላችኋለን።

እስከ እሑድ ባለው ጊዜ ለመነሻ እንዲሆን ይህንን ለማድረግ እንሞክር፦  
  • መረጃውን ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እናድርስ፣ (በስልክ የኤስ.ኤም.ኤስ መልእክቶች፣ በፌስቡክ፣ በትዊተር)፣
  • ዜናውን ለመገናኛ ብዙኃን እናድርስ፣
  • ብፁዓን አባቶችን በስልክም በአካልም በመቅረብ ስለ ጉዳዩ ማነጋገር፣ በውሳኔው እንደማንስማማ እናሳውቅ፣
  • ጉዳያችን እና ዓላማችን “ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ” ሳይሆን የቤተ ክርስቲያናችን አባት የመምረጥ ጉዳይ መሆኑን ለሚመለከታቸው አካላት አለ ፍርሃትና ያለ ሥጋት እንግለጽ፣
  • ከመንግሥት አካላት የተደበቀ የመሥራት ፍላጎት እንደሌለን ከወዲሁ በተደጋጋሚ እንግለጽ፣
  • በአገር ውስጥ ያሉ ጋዜጦችና መጽሔቶች ለጉዳዩ ሽፋን እንዲሰጡት እናበረታታ፣
  • የውጪ አገር ኢትዮጵያውያን ሚዲያዎችም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ በሚል በዚሁ ሰበብ ኢሕአዴግን ለመተቸት ሳይሆን ጉዳዩን ለክርስቲያኑ ሕዝብ በማይጎረብት መልክ እንዲያቀርቡት እናግዝ፣
  • ኦርቶዶክሳውያን ጡመራ መድረኮችም ዜናዎችን በትብብርና በኅብረት ለምእመኑ እናድርስ፣
  • እሑድን ለቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ማቅረብ የምንጀምርበት የመጀመሪያው ቀን እናድርገው።






ቸር ወሬ ያሰማን፣ አሜን።
  

Thursday 20 December 2012

ሰር ዜና:- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች አድማ መቱ! ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ!!




ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ!!ለ 29ኛዉ የአፍሪካ ዋንጫ በዝግጅት ላይ ያለዉ ብሔራዊ ቡድናችን ተጨዋቾች እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ላይ ባላቸዉ ቅራኔ በ09/04/2005 ዓ.ም ለሁለት አመት ብሔራዊ ቡድኑን ስፖንሰር ያደረገዉ ሔንከን ቢራ ባዘጋጀዉን የፎቶ የመነሳት ፕሮግራም ላይ ፎቶ አንነሳም በማለት የተጀመረዉ ተቃዉሞ በዛሬዉ አለት ደግሞ (10/04/2005 ዓ.ም) የዕለቱን ልምምድ (training) ባለመስራት ተቃዉሟቸዉን እንደቀጠሉ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ጨዋቾቹ የሚያነሱት ዋነኛዉ ጥያቄ…..የፌዴሬሽኑ አመራር አባላት ከ 31 አመታት በኃላ ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፋችን ያደረጉልን ምንም ነገር የለም (በአጭር ንግግር ቃል የተገባልን የሽልማት ገንዘብ አልተከፈለንም ማለታቸው ነው) ቢያንስ ባረፍንበት ሆቴል እንኳን መተዉ በዚህ ጉዳይ ላይ ሊያነጋግሩን አልቻሉም የሚል ሲሆን፤ በተፈጠረዉ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የፌዴሬሽኑ የስራ አስኪያጅ ኮሚቴ በፅህፈት ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጧል፡፡ ችግሩ በፍጥነት ተፈትቶ ወደ ስራ እንዲገቡ ብልሐት የተሞላበት ዉሳኔ እንጠብቃለን።፡፡በአስቸኳይም ወደ ልምምዳቸው እንዲመለሱ የሁሉም ስፖርት ቤተሰብ ምኞት ነው። የወዝግቡን ሂደት እየተከታተልን በትኩሱ ለማቅረብ ጥረት እናደርጋለን።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአፍሪካ በሞባይልና ኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢነት ከሚታወቀው የደቡብ አፍሪካው MTN ኩባንያ ጋር የስድስት ሚሊዮን ብር የስፖንሰር ስምምነት ለማድረግ እየተነጋገረ ሲሆን በቅርቡም ስምምነት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከሳምንት በፊት ከታላቁ የቢራ አምራች ድርጅት ከሆነዉ ሔንከን ቢራ ጋር የሁለት አመት የስፖንሰር ስምምነት በ24 ሚሊዮን ብር ($ 1.3 million) ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በዚሁ ዕለት የፌዴሬሽኑ የማርኬቲንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ተወልደ ገብሩ ከስምምነቱ የሚገኘው ገንዘብ ለተጨዋቾቹ አስፈላጊው ሁሉ እንዲሟላላቸው ከማድርግ ባለፈ ከክለቦች ጋር ምንም ትስስር አይኖረውም ማለታቸዉ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአፍሪካ በሞባይልና ኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢነት ከሚታወቀው የደቡብ አፍሪካው MTN ኩባንያ ጋር የስድስት ሚሊዮን ብር የስፖንሰር ስምምነት ለማድረግ እየተነጋገረ ሲሆን በቅርቡም ስምምነት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከሳምንት በፊት ከታላቁ የቢራ አምራች ድርጅት ከሆነዉ ሔንከን ቢራ ጋር የሁለት አመት የስፖንሰር ስምምነት በ24 ሚሊዮን ብር ($ 1.3 million) ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በዚሁ ዕለት የፌዴሬሽኑ የማርኬቲንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ተወልደ ገብሩ ከስምምነቱ የሚገኘው ገንዘብ ለተጨዋቾቹ አስፈላጊው ሁሉ እንዲሟላላቸው ከማድርግ ባለፈ ከክለቦች ጋር ምንም ትስስር አይኖረውም ማለታቸዉ ይታወሳል።ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአፍሪካ በሞባይልና ኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢነት ከሚታወቀው የደቡብ አፍሪካው MTN ኩባንያ ጋር የስድስት ሚሊዮን ብር የስፖንሰር ስምምነት ለማድረግ እየተነጋገረ ሲሆን በቅርቡም ስምምነት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከሳምንት በፊት ከታላቁ የቢራ አምራች ድርጅት ከሆነዉ ሔንከን ቢራ ጋር የሁለት አመት የስፖንሰር ስምምነት በ24 ሚሊዮን ብር ($ 1.3 million) ማድረጉ ይታወሳል፡፡ በዚሁ ዕለት የፌዴሬሽኑ የማርኬቲንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ተወልደ ገብሩ ከስምምነቱ የሚገኘው ገንዘብ ለተጨዋቾቹ አስፈላጊው ሁሉ እንዲሟላላቸው ከማድርግ ባለፈ ከክለቦች ጋር ምንም ትስስር አይኖረውም ማለታቸዉ ይታወሳል።

Tuesday 18 December 2012

የፀጋዬ ግጥሞች 2ኛ

የፀጋዬ ግጥሞች ልክ እንደ ማንኛውም ግጥም ይዘታቸው የተለያየ ነው። ነቢይ መኮንን ከጠቃቀሳቸው
የተወሰኑትን እናያለን። በመጀመሪያ ግን እስኪ የፀጋዬን የእንግሊዘኛ ግጥሞች
8
እንቋደስ።5
« »
A lover love-rejected
With a spirit dejected,
A monk God-forsaken
Whose total faith is shaken,
Are less lost than dreamer
Into whose peace a “question”
Plunged like a knife
And woke him to life,
To search, to find his way
To dodge, to fight his way
Not dream it away!
« ?»
I did not know, oh Sir that I stood on your way
It all happened in chance; argument is unfit,
If we fight, others will benefit,
And as this road is also where my future lay,
Destiny forces me to answer you with “Nay”
Pray lose no temper; lest you commit
A risk to result in a regrettable wit,
For, if there be crime, guilty is just the day;
I am also in yours as you are in my shoes
So do let us shift Sir, to either side
However painful it becomes, we should, though
We realize that it isn’t much to lose
That in spite of us the way is wide 6
And that after all, some day, both of us go.
« »
Showers of anguish
Rain, do not exhaust
Ocean of revenge
Of the innermost
Voice of the betrayed
Comfort of the lost,
Tears torn itself
Blood of the heart.
« »9
I am the first Earth Mother of all fertility
I am the Source I am the Nile I am the African I am the beginning
O Arabia, how could you so conveniently have forgotten
While your breath still hungs upon the threads of my springs
O Egypt, you prodigal daughter born from my first love 
I am your Queen of the endless fresh waters
Who rested my head upon the arms of Narmer Ka Menes
When we joined in one our Upper and Lower Lands to create you
O Sudan, born out of the bosom of my being
How could you so conveniently count down
In miserable billions of petty cubic yards
The eternal drops of my life giving Nile to You
Beginning long before the earth fell from the eyeball of heaven.
O Nile, that gush out from my breath of life 7
Upon the throats of the billions of the Earth’s thirsty multitudes,
O World, how could you so conveniently have forgotten
That I, your first fountain, I your ever Ethiopia
I your first life still survive for you?
I rise like the sun from the deepest core of the globe
 I am the conqueror of scorching pestilences
I am the Ethiopia that ‘stretch her hands in supplication to God’
I am the mother of the tallest traveler on the longest journey on
Earth
...
ለአባይ ቅኔ ያልዘረፈለት ተቀኚ፣ ስንኝ ያልቋጠረለት ገጣሚ፣ ቃላት ያልደረሰለት ደራሲ፣ ያላዜመለት ድምፃዊ፣
ያልተጠቀሰለት ምሳሌ፣ ወዘተ ...  የለም። ሲሻገሩት አድንቀውታል። አምላኪዎቹ ሰግደውለታል -  ጪዳ
ገብረውለታል። በምንጩ ምንነት ተከራክረውብታል -  ሁሉም አወድሰውታል።
10
ግና ማን እንደ ፀጋዬ።

ዝክረ ሎሬት ፀጋዬ ገ|መድሕን 1ኛ


ጸጋዬ ገብረ መድህን (1928-1998) ባዳ ተብላ በምትታውቅ አምቦ ካተማ አካባቢ በምትገኝ ተራራማ ቦታ ተወለዱ። በአምቦ ማአረገ ሕይወት ቀኃሥ ትምህርት ቤት ከዚያም ጀነራል ዊንጌትና በአዲስ አበባ የንግድ ትምህርት ቤት በአገር ውስጥ ትምህርታችውን ከገፉ በኋላ በቺካጎ ብላክስቶን በህግ ትምህርት ተመርቀው በ1952 እንደ ውጡ በለንደን ከተማ የቴአትር ትምህርት በሮያል ኮርት ቴአትርና በፓሪስ ኮሜዲ ፍራንሴዝ ተከታትለዋል። ከ1954 እስከ 1964 የቤሄራዊ ቴአትር በአርቲስቲክ ዳይሬክተርነት አገለግለዋል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ዲፓርትመንትን አቋቁመዋል።
ሆኖም በ1960ዎቹ ደርግ አብዛኛውን የቴአትር ስራዎቻቸውን ሲያግድ እሳቸውንም ለማሰር በቅቷል።
ብላቴን ሎሬት ጸጋዬ በርካታ ግጥሞችን፥ የቴአትር ሰራዎችን የተለያዩ መጣጥፎችንና ዘፈኖችን አበርክታዋል። ጸጋዬ በ1990 ለጉበት በሽታ ሕክምና በመሻት ወደ ማንሃታን በሄዱበት አርፈዋል። በአዲስ አበባ በስላሴ ቤተክርቲያን ተቀብረዋል። ነፍሳቸውን በአብርሃም እቅፍ ያኑርልን::
እንደ፡ አዉሮፓ፡ አቆጣጠር፡ በ 2002 ዓ.ም. የብላቴን ሎሬት ጸጋዬ፡ ገብረ መድህን፡ ግጥም፡ ("Proud to be African") በአዲስ፡ በተመሰረተዉ፡ የአፍሪካ፡ አንድነት፡ መህበር፡ በሕዝብ፥ መዝሙርነት፡ ተመርጧል።
 ... ...ብላቴን ጌታ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድሕን ቀዌሳ እነሆ በሞት ከተለየን ድፍን አስር  አመታት ተቆጠሩ። ቦዳ
(አምቦ) የተጀመረ ሕይወት ማንሀተን (ኒው ዮርክ) ተቋጨ። ግብአተ መሬቱም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
(አዲስ አበባ) ተፈጸመ። ይቺ ፅሁፍ አራተኛ ሙት አመቱን (February 25, 2006) በማሰብ የግጥም ስራዎቹን
በግርድፉም ቢሆን በማውሳት እነሆ የፀጋዬ ዝክር ትላለችፀጋዬ ከማረፉ አራት አመታት ቀደም ብሎም በዶ/ር ኄራን ሠረቀብርሃን**** አስተባባሪነት በዋሽንግተን ዲሲ የፀጋዬ
ግጥሞች በሲዲ ተቀርፀው ተመርቀዋል።
1የእረፍት ዋዜማ
የስንብት ዝግጅት ይሆን። ትንቢት አስቀድሞ ለነገር እንዲሉ።
ፀጋዬ ከማረፉ አስራ አምስት ቀን አስቀድሞ የ«አንድምታ»  ባልደረባ አናግሮት ነበር። እስኪ ሁለቱን የሎሬት
ፀጋዬን ጥኡም ወጎች ላስቀድም።
በአፄ ምኒልክ ዘመን እንግሊዞች ቱርካና ሃይቅ አካባቢ ዝሆን ያድኑ ነበርና አንዴ አደናቸውን ተከትለው ሲገስግሱ
ከኢትዮጵያ ኬላ ደርሰው ኖሮ ድንበር አላሳልፍ ካሉ የኬላ ጠባቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ይደረግና ከአዳኞቹ
አንዱ በዚሁ ምክንያት ይሞታል። እንግሊዞችም አቤቱታ ያሰሙና ነገሩ አባ መላ (ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ)
ዘንድ ይደርሳል። እንግሊዞቹ ያለአግባብ ሰው እንደተገደለባቸው አመልክተው የደም ካሳ እንዲሆናቸው
ከኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ መሬት እንዲሰጣቸው ነበር የጠየቁት። አባ መላ ነገሩን ያጠኑና ችግር እንደሌለው
ለእንግሊዞቹ ይገልጻሉ። ነገሩ ከመፈጸሙ በፊት ግን ይኸ ህግ እናንተ ሃገርም እንደሚሰራበት ማየት ስለምንሻ
በሰነድ መልክ ረቂቁ ካለ እስቲ እንየው። እውነት የእንግሊዝ ሰው የዌልስን ሰው ቢገድል እንግሊዝ ከመሬቷ
ለዌልስ የምትሰጥ ከሆነ እኛም እንሰጣለን። እሱም የሚሆነው ለተገደለብን የኬላ ጠባቂ ካሳ የሚሆን ከቱርካና
ሃይቅ አካባቢ መሬት ከተረከብን ይሆናል ብለው መለሷቸው።

ሰበር ዜና....16 የኣውሮፓ ፓርላማ ኣባላት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በአፋጣኝ እንዲፈታ የሚል ደብዳቤ ፃፉ!!!

16 Members of the European Parliament Call for the Release of Imprisoned Ethiopian Journalist Eskinder Nega

Washington, D.C.: Today, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Ethiopian Prime Minster Hailemariam Desalegn expressing their grave concern regarding the continued detention of imprisoned journalist and blogger Eskinder Nega.

Arrested in 2011 and detained without access to an attorney for nearly two months, Mr. Nega was sentenced to 18 years in prison under the country’s broad 2009 Anti-Terrorism Proclamation on July 13, 2012. Mr. Nega’s arrest and prosecution came after he wrote online articles and spoke publicly about the possibility of an Arab Spring-like movement taking place in Ethiopia. After his sentencing, the government initiated proceedings to seize his assets, including the home still used by his wife and young son. An appeal hearing in the case is scheduled for Wednesday, December 19th.

The letter, notes that the Ethiopian government has an obligation to uphold the right to free expression and reminds the newly appointed Prime Minister that he has “the unique opportunity to lead Ethiopia forward on human rights and bring the country fully within the community of nations.” The letter closes by urging the Prime Minister to take all measures within his power “to facilitate the immediate and unconditional release of Mr. Nega.”

“This is an important recognition by members of the European Parliament from across the political spectrum that the right to free expression is universal and must be respected by the Ethiopian government,” said Freedom Now Executive Director Maran Turner. “Mr. Nega has been wrongfully detained in Ethiopia in violation of his right to freedom of expression, and he must be released.”

The text of the letter is copied below and a full PDF of the letter can be found at the below link. Freedom Now, a legal advocacy organization that represents prisoners of conscience around the world, serves as international pro bono counsel to Mr. Nega.

Sunday 16 December 2012

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል


በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግሥት የገዳሙን ይዞታ የቋርፍ (የገዳማውያኑ ምግብ) የሚመረትበትን ቦታ ወስዶ ስላረሰው ገዳማውያኑ በከፍተኛ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፥ ከዚህ በተጨማሪ የገዳማውያኑ የሳር ቤት ክዳን ባለው ቤት ላይ ተባይ በማፍራቱ ገዳማውያኑን ለተጨማሪ አደጋ ተዳርገዋል። ከዋልድባ ዳልሻህ ኪዳነ ምሕረት የአንድነት ገዳም ሦስት የመነኮሳይት ቡድን ወደ አዲስ አበባ ተልኮ የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለመጠየቅ መጥተው እንደነበር እና ነገር ግን ከቤተክህነቱም ምንም ዓይነት ድጋፍ ሳይደረግላቸው መነኮሳይቱ ወደ ባዕታቸው ለመመለስ ችለዋል።