"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 20 October 2012

ቱጃሯ ሱራና ኦህዴድ ከጫት ንግድ በስተጀርባ ያለው ቁማር!!


khatlines and sura
በማናቸውም የአገሪቱ ባለስልጣናትና ተቋማት ብሔራዊ ባንክን ጨምሮ ይፋ የማያደርጉት የአገር ውስጥ የጫት ፍጆታና ገቢ በውስጡ ከፍተኛ ዝርፊያ ይከናወንበታል። ከዝርፊያው ጋር በተያያዘ አቶ መለስን ጨምሮ ከፍተኛ ሹማምንትና ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን በቅድሚያ ስማቸው ከሚጠቀሱት መካከል ናቸው። የጎልጉል የኦህዴድ ምንጮች የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትርና የንግድና ኢንዱስትሪ ምክትል ሚኒስትሩ በጫት ንግድ ዙሪያ የሚጫወቱትን ሚና አጋልጠዋል። ያገኘነውን መረጃ ለንባብ ያመች ዘንድ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።

የጫት ንግድ ዝምድና – ወ/ሮ ሱራ

በደርግ የአገዛዝ ዘመን ወደ ጅቡቲ ኤክስፖርት መደረግ የጀመረው ጫት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር የወያኔ አባላትን ቀልብ አልሳበም ነበር። ባለስልጣናቱና የቀድሞው ታጋዮች ጫት ተጠቃሚ ስላልነበሩ ስለ ጫት ንግድና ከፍተኛ ፍጆታ እንዳለው መረጃው የላቸውም። እንደውም ጫት “የሚበሉ” ሲመለከቱ ይገረሙ ነበር።
ወ/ሮ ሱራ ጅጅጋ ይኖሩ የነበሩ የሶማሌ ተወላጅ ናቸው። በቅርበት የሚያውቋቸው የሃርጌሳ ሶማሌ ጎሳ አባል የሆኑ ሙሉ የሶማሌ ዜግነት ያላቸው ሴት እንደሆኑ ይናገራሉ። ወይዘሮዋ የጫት ንግድ ስራ የጀመሩት ጅጅጋ ሲሆን ከቀን ወደ ቀን ገቢያቸውን በማሳደግ ወደ ሶማሌ ማጓጓዝ ጀመሩ።
የኦጋዴንን በረሃ በሌሊትና በቀን እያቆራረጡ ሶማሌ የሚገቡትን ላንድ ክሩዘር መኪኖች በመጠቀም ሶራ የጫት ንግዳቸውን አስፋፉ። ሲሉም ጅጅጋ የሚመጣላቸውን ጫት ከመረከብ ይልቅ ራሳቸው ከሐረር ዙሪያና ከአወዳይ አካባቢ በቀጥታ ከገበሬዎች በመግዛት ወደ ጅጅጋና ወደ ሶማሌ በበረሃ በማስረግ ሃብት ሰበሰቡ።
በኋላም ህጋዊ ፈቃድ አውጥተው ወደ ሶማሊያ ሃርጌሳ ጫት ላኪ ሆኑ። ከድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ ዘወትር ጫት በኢትዮጵያ አየር መንገድ በማመላለስ የተወለዱበትን አገር የጫት ኮታና ንግድ ለብቻቸው ተቆጣጠሩ። ሃብታቸው እየገዘፈ ሲመጣ የማጓጓዣ ወጪያቸውን ለመቀነስ የራሳቸውን አውሮፕላን ለመግዛት ፈቃድ ጠይቀው ተፈቀደላቸውና በራሳቸው አውሮፕላን ጫት ማጋዙን ተያያዙት። ሃብታቸው ገዘፈ። የጫት ማከፋፈያ መደብ ላይ ተቀምጠው አንድና ሁለት እስር ሲቸረችሩ የነበሩት ሱራ ከበሩ።

የጫት አቅርቦት ሞኖፖሊ

ሱራ የገንዘብ አቅማቸው ሲያድግ ወደ ምዕራብ ሐረርጌና ምስራቅ ሐረርጌ ክልላቸውን አሰፉ። አርሶ አደሩ ውስጥ በመግባት የጫት ማሳዎችን በኮንትራት በመግዛት በሞኖፖል ያዙት። የተሰበረ ጫት ከመግዛት ይልቅ ማሳውን በሞኖፖል በመያዝ በሚፈልጉት መጠን ማግበስበስ ያዙ። በየወረዳው ወኪሎቻቸውን አስቀምጠው ሥራውን ተቆጣጠሩት። የቀድሞውን የደርግ መንግስት የደህንነት ሰዎችና ኮማንዶዎች አደራጅተው የመንግስት ያህል ጡንቻቸውን አጎለበቱ። ሚዲያ እንኳን አጠገባቸው ሊደርስ ቀርቶ ፈራቸው። የሚታጀቡና ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርጉላቸው ባለሃብት ሆኑ። ጉልበታቸውን ተማምነው በሊዝ የያዙትን የጫት ማሳ ከገበሬ ማኅበራት አመራሮች ጋር በመሆን ወደፊት በሚከፈል እዳ ወደ ሶማሌና በቀን ሁለትና ከዛም በላይ በረራ በማድረግ ከበሩበት።  የኦህዴድ የንግድ ድርጅት የሆነውን ቢፍቱ የጫት ንግድን ሳይቀር ጉሮሮው ላይ ቆመው አንገዳገዱት። በኋላ ላይ እንዳይሆን አድርገው በብር አሽመደመዱትና ሶማሌ ውስጥ ከጀመረው የጫት ንግድ አባረሩት። ኦሮሚያና አስተዳደሮቹ የህዝባቸውን ብሎም የፓርቲያቸውን ጥቅም እንኳን ማስከበር ሳይችሉ ቀሩ። አሁን ድረስም እንደዛው ነው።
እልህ ውስጥ የገቡት የኦህዴድ ሰዎች የፖለቲካ ስልጣናቸውን በመጠቀም ሱራን እጃቸውን ለመጠምዘዝና የሶማሌን የጫት ኤክስፖርት ለመጠቅለል ዘመቻ ጀመሩ። በኦሮሚያ የጫት መቆጣጠሪያ ኬላና በአርሶ አደሮች ማኅበራት አማካይነት ከአገር የሚወጣውን የጫት መጠን በማስላት ከጫት ኤክስፖርት የሚገባውን የውጪ ምንዛሬ መረጃ በማመሳከር ከፍተኛ ማጭበርበር እንደሚካሄድ ለፌደራል መንግስት አሳበቁ። ኦህዴድ ሶማሌ ጫት ንግድ ውስጥ ለመግባት ሞክሮ እንዴት ማጅራቱን እንደተመታና እንዴት ጅቡቲ ውስጥ ተወትፎ እንደቀረ በሌላ ዜና እንመለስበታለን።
ሱራ ከየአቅጣጫው የሚነሳባቸውን ተቃውሞና ቁጥጥር እንዴት እንደሚመክቱ ኦህዴድ ውስጥ መነጋገሪያ ሆነ። በከፍተኛ ደረጃ ያሉ የኦህዴድ አመራሮችና ባለስልጣናቱ ከጫት ንግዱ በስተጀርባ ያለውን አሻጥር ቢያውቁም ሊጋፉት የማይችል ስለሆነባቸው ቀረጥ ላይ አተኩረው በመስራት ክልሉ ከጫት በኪሎ ስድስት ብር ቀረጥ እየሰበሰበ እንዲቆይ ማሳሰቢያ ሰጡ። በዚህም ከሚመዘበረው የኬላ ገቢ ወጪ ቀሪ ክልሉ በዓመት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እየሰበሰበ ቆየ። በመካከሉ ሱራ በዘረጉት ሰንሰለት አማካይነት ኬላ እንዲነሳ የጀመሩት ዘመቻ በድል መጠናቀቁ ይፋ ሆነ። ኦሮሚያ ላለፉት አምስት ዓመታት በየዓመቱ ሲያገኝ የነበረውን ገቢ ተነጠቀ። በወቅቱ ውሳኔውን ተከትሎ የክልሉ የገቢዎች ቢሮ ውሳኔውን ተቃወመ። በኦሮሚያ የቢሮው ሃላፊ በያዙት አቋምና በሼኽ መሐመድ አላሙዲ ድርጅቶች ላይ በያዙት አስገድዶ ግብር የማስከፈል ርምጃ ተዳምሮ መጨረሻቸው ወህኒ ሆነ።

ኬላ ተነሳ — ቀረጡን ሱራ መሰብሰብ ጀመሩ

የጫት ኬላ እንዲነሳ ቀደም ሲል በገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትሩና በንግድና ኢንዱስትሪ ምክትል ሚኒስትሩ አማካይነት የውጪ ምንዛሪ ገቢ እንዲጨምር በሚል ሰበብ ሃሳብ ቀረበ። ያለ ቁጥጥር ጫት ቢወጣ የውጪ ምንዛሬ ገቢውን ይጨምራል ተብሎ ዓይን ያወጣ ክህደት ክልሉ ላይ ተበየነ። ክልሉ ሃሳቡን በመቃወሙና በክልሉ ቀረጥ የመሰብሰብ መብቱን ስለሚጋፋ ተግባራዊ ሊሆን አይገባም ቢባልም ከሱራ ጀርባ ያሉት ክፍሎች በኦሮሚያ በኩል የቀረበውን ቅሬታ ወግድ አሉት። ሱራም ባሰማሯቸው ጉዳይ አስፈጻሚዎች አማካይነት ኬላው እንደሚነሳ ሲያስነግሩ የነበረው እውን እንደሚሆን ፉከራው ቀጠለ። በመጨረሻም አቶ መለስ የጫት ኬላ እንዲነሳ የቀረበውን ሃሳብ አጸደቁትና ኦሮሚያ ከጫት ቀረጥ ሲያገኝ የነበረውን ብር ትቶ እጁን ታጥቦ የበይ ተመልካች ሆነ።

“የጥቁርም የነጭም ደም ቀይ ነው” የመለስ ድራማ!! ኢህአዴግ ለመክሰስ ሲፈልግ ፊልም እንደሚደርስ ተረጋገጠ


swidish journalists in addis
የኦጋዴን ጉዳይ ሲነሳ ኢህአዴግ ይደነግጣል። ስለ ኦጋዴን አንዳችም ጉዳይ እንዲነሳበት አይፈልግም። የቢቢሲ የምርመራ ዘገባ በኦጋዴን ተፈጽሟል ያለውን ይፋ ሲያደርግ ኢህአዴግ በተለዩት መሪው፣ በህዝብ ግንኙነቱና እንግሊዝ አገር ባሉት አምባሳደሩ በኩል የማስተባበያ ዘመቻ ከፍቶ ነበር። በኬንያ ስደት ጣቢያ የሚገኙትን የክልሉ ነዋሪዎችን ያነጋገረው የቢቢሲው መርማሪ ጋዜጠኛ ሪፖርት ብቻ ሳይሆን ሂውማን ራይትስ ዎችም የከረረ መግለጫ አውጥቶ ነበር። ከአገር በቀል የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች መካከል የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄም በተመሳሳይ የኦጋዴንን አጀንዳ በማንሳት ጥሪ በማስተላለፍ ቅድሚያ እንደነበረው መረጃዎች ያመለክታሉ።
ኢህአዴግ በሃሰት ላይ የተመረኮዘ መረጃ በማዘጋጀት የሚመራውን ህዝብና የዓለም ህብረተሰብን እንደሚያወናብድ የሚያጋልጡ መረጃዎች በየጊዜው ይፋ ይሆናሉ። “ታላቅ ስህተት ሰርተናል፣ስህተቱ ህይወታችንን ሊያሳጣ ይችል ነበር …” በማለት አዲስ አበባ ከርቸሌ ውስጥ ሆነው ይቅርታ የጠየቁት ሁለቱ የስዊድን ጋዜጠኞች፣ ሰሞኑን ይፋ ያደረጉት ነገር ቢኖር ይህንኑ ኢህአዴግ ሊከድነው የሚደክምበትን ሃቅ ነው።
የተቀነባበረ ድራማ  “እንደ ሆሊ ውድ” ፊልም ማዘጋጀት የዓለምን ህብረተሰብና የሚመራውን ህዝብ ያጭበረበረው ኢህአዴግ በሞት በተለዩት መሪው አማካይነት ሲምልና ሲገዘትበት የነበረውን ማጭበርበር ማርቲን ሺብዬና ዩሃን ፐርሸን አጋልጠዋል። አቶ መለስ “የጥቁርም የነጭም ደም ቀይ ነው” በማለት ለፈጠሩት ፓርላማ ሲፈላሰፉና በህግ የበላይነት እንደሚያምኑ እያስጨበጨቡ ሲናገሩ የነበሩትን ሁሉ እርቃኑን በማስቀረት ሁለቱ ጋዜጠኞች ህያው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።በኢትዮጵያ በተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ደጋፊዎች፣ በጋዜጠኞችና ስርዓቱን በሚቃወሙ ዜጎች ላይ የሚለጠፈው “የአሸባሪነት” ወንጀል የተቀነባበረ የፈጠራ ፊልም መሆኑን አረጋግጠዋል።
ቀደም ሲል መለስ፣ አሁን ደግሞ ሃይለማርያም እየማሉበት ያለው የህግ የበላይነት ቁማር መሆኑን፣ ፍርድ ቤቶቻቸው የቁማር መጫወቻ፣ ዳኞቻቸው ታላቁን ሙያ ያረከሱና ሙሉ በሙሉ በተቀናበረ ድራማ የሚፈርዱ መሆናቸውን ሁለቱ ጋዜጠኞች ላገራቸው ሚዲያዎች፣ ለቢቢሲ አፍሪካና ለአሜሪካ ሬዲዮ አስታውቀዋል። በዚህም ተግባራቸው ቀደም ሲል የበደኖና የወተር፣ በቀርቡ ደግሞ “አኬልዳማ” የተሰኘው የመወንጀያ ዶክመንተሪ ኢህአዴግ ቆርጦ እየቀጠለ፣ እያስፈራራና በቅድመ ሁኔታ እየተደራደረ የሚያመርተው የግፍ አገዛዙ ማስቀጠያ የማታለያ ሸቀጡ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
በተለይም የአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ክፍለ ጊዜ በዝርዝር ያቀረበው የሁለቱ ጋዜጠኞች ቃለ ምልልስ አገር ቤት የተለያዩ ጉዳዮችን አስነስቷል። “በደኖ ኢንቁፍቱ /የማይጠግበው ዋሻ/፣ አርባ ጉጉ፣ ደደር፣ ወተር፣ ቆቦ … አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል። የጎሳ ፖለቲካ ጣጣ ሰለባ ያደረጋቸው የኢትዮጵያ ልጆች ከነ ህይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ ተጥለዋል። በጅምላ እንደ ባዳ ተጨፍጭፈዋል።ኢህአዴግ ህዝቡን ከመጠበቅ ይልቅ ለተራ የፖለቲካ ትርፍ በተቀነባበረው ወንጀል ስር ፊልም ያቀናብራል። የፖለቲካ ቁማር ይቆምራል። ራሱ ገደል ከቶ በሃዘን ሙዚቃ ታጅቦ ራሱ ከገደል ሲያወጣ የሚያሳይ ዘግናኝ ፊልም ለህዝብ እያሳየ እንባ ያራጫል። በሃሰት ፊልም እያመረተ ያጭበረብራል። የሁለቱ ስዊድን ጋዜጠኞች ሰሞኑን ያረጋገጡት ነገር ቢኖር ይህንኑ ነው” የሚል አስተያየት ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ተልኳል።
መለስ ቀይ መስቀልን ጨምሮ በኦጋዴን የሚገኙ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችን ሙሉ በሙሉ ሲያስወጡ ምን አስበው ነበር? ለሚለው የብዙዎች ጥያቄ ምላሽ የተገኘ ይመስላል። “መለስም አረፉ፣ እኛም አረፍን የምንለው መቼ ነው” በማለት የሚጠይቀው ቀን 2004 ዓ ም የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ነጥቦችን በመዘርዘር ስለ ኦጋዴን ችግር ያወጣው መግለጫ:-

Friday 19 October 2012

ኢትዮጵያውያኑ በኖርዌይ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ


ኢትዮጵያውያኑ በኖርዌይ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

 
በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ መንግስት እያደረሰ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ በሰልፉ ላይ ከተለያዩ የኖርዌይ ፓርቲዎች እና ድርጅቶች ተወክለው የመጡ ሰዎች በየተራ ባደረጉት ንግግር በሰብአዊ መብት ረገጣ የሚታወቀውን የኢህአዴግን መንግስት የኖርዌይ መንግስት መደገፉን እንዲያቆምና  ስደተኞችን ላይ ያለውን  አቆም እንዲያስተካክል ጠይቀዋል  እንዲሁም ዶ/ር ሙሉዓለም  ዶ/ር ግሩም ዘለቀ  እና አቶ አምሳል የኢትዮጵያ መንግስት እያደረሰ ያለውን የሰብአዊ መብት ረገጣ እንዳላቆመ ተናግረዋል:: ሰልፈኞችም የኢትዮጵያ መንግስትን የሚያወግዝ መፈክር አሰምተዋል


የኢትዮጵያ ፓርላማ አባላትን “እግዚአብሄር ኢትዮጵያን በበረከቱ ይጠብቃት” መባሉ አሳቃቸውያሳዝናል! (ደረጀ)


AMHARIC NEWS

የኢትዮጵያ ፓርላማ አባላትን “እግዚአብሄር ኢትዮጵያን በበረከቱ ይጠብቃት” መባሉ አሳቃቸውያሳዝናል! (ደረጀ)

October 18, 2012   ·   0 Comments
የትናንቱን የፓርላማ ውሎ አላየሁትም ነበር። ስብሰባውን በኢቲቪ የተከታተለ ጓደኛዬ፤ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ንግግራቸውን ሲጨርሱ<< እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንን በበረከት ይጎብኛት>> በማለታቸው አፈ-ጉባኤውን አባ ዱላን ጨምሮ የፓርላማ አባላቱ እንደሳቁ በፌስ ቡክ ገጹ አስነበበን ። “ በዚህ እንዴት ሊስቁ ይችላሉ?”ብዬ ቅሬታዬን ስገልጽ ሌለኛው ጓደኛዬ፦< ..የሳቁትኮ “..በበረከት ይጎብኛት” የሚለውን አባባል- ከአቶ በረከት ስምዖን ጋር አያይዘውት ነው>> ብሎ በማስፈገግ አረጋጋኝ። አሁን ቪዲዮውን ሳየው ግን የሳቁት የንግግሩ ቅኔነት ገብቷቸው ሳይሆን፤ የእግዚአብሔር ስም በመጠራቱ እንደሆነ ተረዳሁ።
ያደጉትና የሰለጠኑት አገሮች ዶላራቸው ላይ፦We Trust in God እያሉ ሲጽፉ፤ እነ አባ ዱላና መሰሎቻቸው፦ <እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርካት>በሚል ንግግር መንጋጋቸው እስኪታይ ይስቃሉ።ልብ በሉ! ሰውን እያመለኩ ያሉ ደካሞች ናቸው በእግዚአብሔር ስም መጠራት የሳቁት። ይሁን እንጂ ቅሬታዬ “ለምን አሜን አላሉም?” ከሚል የመነጨ አይደለም። አለማመን ወይም በፈለጉት ማመን መብታቸው መሆኑን አውቃለሁ። እያልኩ ያለሁት ፤ብብቱን እንደኮረኮሩት ሰው የእግዚአብሔር ስም ሲጠራ፤ ምን አስገለፈጣቸው ነው?
<<የሮማው ፈረስ ካሊጉላ-በንቀት ልቡ የሰባ፦
ታዛዥና ተጋላቢ-ፈረሱን ፓርላማ አስገባ፣
ከዚያን ዕለት ጀምሮ-ፈረሶች ወንበር ለመዱ፣
ለማመን ማየት ካሻችሁ-እኛ አገር ፓርላማ ሂዱ>> ያለው ማን ነበር?
እነሆ ቪዲዮው፦
http://www.amharictube.com/musicvideo.php?vid=21a52302b

የሕወሓቱ የደህንነት አናት ጌታቸው አሰፋ HIV እያራቡ ነው ተብሎ ተከሰሱ ::



የሕወሓቱ  የደህንነት አናት ጌታቸው አሰፋ HIV ፖዘቲቭ ተብለው ከታወቀበት ከዚህ አመት መጀመሪያ ጀምሮ የተለያዩ ሴቶችን ወደ ቤታቸው እየወሰዱ እና ወደ ቢሮቸው እያመጡ በሽታዉን በማስፋፋት ላይ ናቸው ሲል አንድ የደህንነት ምንጭ ከ አዲስ አበባ ገለጠ:;

ይህ ምንጭ እንዳለው ከሆነ አቶ ጌታቸው በጠባቂዎቻቸው እና በ ደላሎች አማካኝነት ከትምህርት ቤቶች ከቢሮዎች እንዲሁም ባለትዳሮችን እያስመጡ የወሲብ ብልግና ካለኮንዶም በመፈጸም ለHIV እንዲጋለጡ እያደረጉ ነው ሲል ይገልጣል::


በ ግንቦት 2012 መጀመሪያ ላይ የህ ቫይረስ በዉስጣቸው እንዳለ የተነገራቸው አቶ ጌታቸው ወደ መካከለኛው ምስራቅ በመሄድ የወሰዱት በከባድ ሳል በተያዙ ጊዜ የህክምና ክትትል ይህ በሽታ እንዳለባቸው ተነግሮዋቸዋል::


Described as a 

 http://wikileaks.org/cable/2009/03/09ADDISABABA578.html
character by the former US Ambassador to Ethiopia, the 53-year-old security officer is known to frequent brothels and is alleged to have contracted the virus from a prostitute working at the Sheraton Hotel in Addis Ababa.
Since gaining his position as the head of NISS in 2001, Assefa has accumulated a long-list of human rights abuses, including being the mastermind behind the massacres of over 400 civilians in the Gambela region and ordering the deaths of 193 civilians during the 2005 heavily disputed elections.
Dubbed as the ‘Bangkok of Africa’ by seasoned tourists, Addis Ababa continues to be a mecca for prostitution. An estimated one in every twelve women living in the capital works as a prostitute and nearly a quarter of them are said to carry the HIV virus.
 http://wikileaks.org/cable/2009/03/09ADDISABABA578.html

Tuesday 16 October 2012

Ethiopia and Egypt continue fight for Nile water Posted by quatero | October 17, 2012 |


CAIRO and ADDIS ABABA: With the first-ever Nile Basin Initiative (NBI) report on the status of the Nile River, the situation between Egypt and Ethiopia and the angst between the two foes finally has some statistics and analysis to deal with. However, it is unlikely to see any changes in the current policies that have both countries eying future water resources along the world’s longest river.

Top Ethiopia government officials have told Bikyamasr.com that they are looking at jumpstarting the massive Renaissance Dam project along the Nile River in an effort to increase water resources and energy for the East African country.

The moves could threaten the regional stability after the Egyptian government said it remained “concerned” over Ethiopia’s actions along the Nile River.

The International Monetary Fund (IMF) has also called on Addis Ababa to push the dam project to the backburner in order to focus on other economic initiatives.

While Cairo has denied any intention of attacking the dam, as reported by whistleblower website Wikileaks, the country’s Water Resources and Irrigation Minister Mohamed Bahaa el-Din said last month that his country was maintaining its concerns about the construction of the Renaissance Dam in Ethiopia.

He did say that officials at the Ethiopia foreign ministry “assured Egypt and Sudan that in case there was any impact on their water quota to the dam, other projects will be carried out to collect lost water and cover shortages.”

It is the latest in the ongoing battle for the world’s largest river’s water, with Egypt and Sudan continuing to remain obstinate in amending any of the colonial treaties that guarantee their countries with a lion’s share of water from the Nile.

Wikileaks released documents this month that revealed Egypt and Sudan had been planning to attack an Ethiopian dam project to “protect” their rights over Nile water based on colonial era treaties.

In documents revealed by Wikileaks, the Egyptian and Sudanese government appeared ready to develop a launching pad for an attack by Egypt against the dam.

Wikileaks has leaked files allegedly from the Texas-based global intelligence company, Stratfor, which quote an anonymous “high-level Egyptian source,” which reported that the Egyptian ambassador to Lebanon said in 2010 that Egypt “would do anything to prevent the secession of South Sudan because of the political implications it will have for Egypt’s access to the Nile.”

Ethiopia’s massive dam project has seen much concern from Cairo and Khartoum, who fear the establishment of Africa’s largest dam would affect previous colonial deals on Nile water-sharing.

It is to be built some 40 kilometers upstream from Sudan on the Blue Nile.

Swedish journalists tell of time in Ethiopia jail, BBC








16 October 2012 (BBC) Swedish journalists Johan Persson and Martin Schibbye have been speaking to the BBC about their time in prison in Ethiopia.

They were recently freed after serving more than 400 days of an 11-year sentence.

The pair were found guilty of entering the country illegally and supporting a rebel group, the Ogaden National Liberation Front (ONLF).

Their lengthy jail terms put the treatment of journalists in Ethiopia under the international spotlight.

Martin Schibbye and Johan Persson were captured along with ONLF rebels in June 2011.

They maintained that they were only doing their jobs, and human rights group Amnesty International said the journalists had been prosecuted for doing “legitimate work”.

But Ethiopian government spokesman Bereket Simon previously defended the decision to jail the pair, saying the journalists were caught “red handed” co-operating with “terrorist organisations”.

Former Prime Minister Meles Zenawi reportedly pardoned the journalists before his death in August, leading to their release.
‘Rats, fleas and sick people’

Johan Persson told the BBC World Service programme Newsday that conditions in the prison in which hey were held were poor.

“It was 200% overcrowded. It was very hot. There was a lack of water. It was dusty. There were rats, fleas and many people were sick with HIV or tuberculosis,” he said.

But he said the conditions were not as significant as the other inmates: “What’s interesting is who they put in there: journalists and the political opposition.”

Although the pair admit that they entered Ethiopia illegally, they argue that their trial was unfair.

“The trial was a joke,” said Mr Persson. “Meles Zenawi was saying on national television, three or four weeks before the trial started, that we were guilty.”
Continue readin

Monday 15 October 2012

የአርቲስት ዳምጠው አየለ ጥሪ !!






“ሰው ናፈቀኝ፣ ልጆቼና አገሬ ታወሱኝ፣ ባህሌና ልማዴ የት ገባ….?” የሚሉት የአንድ ስደተኛ ጥያቄዎች ለመቶ አለቃ ዳምጠው አየለ ተረት ሆነውበታል። አርቲስት ዳምጠው አየለ ከሁርሶ የመኮንኖች ማሰልጠና ማዕከል የመኮንንነት ትምህርት ተከታትሏል። ለሰላሳ ሁለት ዓመታት በምድር ጦር የሙዚቀኛ ሻለቃ አገልግሏል። በተለይም በባህላዊና አገር በሚያሞካሹ ዜማዎቹ የሚወደደው ዳምጠው አገሩን፣ ሁለት ልጆቹንና ባለቤቱን ጥሎ በስደት ኖርዌይ ከገባ ሰባት ዓመታት አሳልፏል። የስልሳ ሶስት ዓመቱ ዳምጠው ያጋጠመውን ጊዚያዊ ችግር አስመልክቶ ከጎልጉል የአውሮፓ ዘጋቢ ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። ዳምጠው ችግር እንዳጋጠመው ሲሰማ አስቸኳይ ድጋፍ ላደረጉ ወገኖች፣ ድርጅቶች፣ ማህበሮች፣ ላደረጋችሁት በአርአያነት የሚጠቀስ ተግባር የዝግጅት ክፍላችን በዚህ አጋጣሚ ለማመስገን ይወዳል።

“… አዎ፤ እኔም ራሴን እጠይቀዋለሁ። ጀግና ሲወድቅ አይቻለሁ። የጦር ሜዳ መከራና እሳት አይቻለሁ። ባልዋጋም በኦጋዴንና በሳህል ግንባር ኤርትራ ተገኝቼ የመከራን ወጋገን ተመልክቻለሁ። ጀግና ወድቆ ሲነሳ ማየቴ ትዝ ይለኛል። ምንም እንኳን በርካታ የክፉ ቀን መቋቋሚያ ልምድ ቢኖረኘም ካቅሜ በላይ ሆነብኝ። ችግር እንዳይፈታኝ አጥብቆ የያዘኝ የኑሮ ልምዴና ወታደርነቴ እያደር ላላ። እድሜዬ እየገፋ ሲሄድ ነው መሰል ባባሁ። በጀርባዬ ተኝቼ ኮርኒስ እያየሁ ልጆቼንና ባለቤቴን በማሰላሰል ደከመኝ። አስባለሁ፣ አወጣለሁ፣ አወርዳለሁ ለውጥ የለም። አናቴ ጋለ። ደም ግፊት ያዘኝ። ሌላውም ተከተለኝ። ታመምኩ። እኔ ተቆንጥጬ ያደኩ፣ ለባህሌና ላገሬ ልዩ ክብር ያለኝ ሰው ነኝ። የአገሬ ሽታ ይመጣብኛል። ከብቶች ሽታቸው ይናፍቀኛል… ታዲያ ይህንን ሁሉ አጥቼ እንዴት የምታውቀኝ የድሮው ዳምጠው ልሆን እችላለሁ?”

ጎልጉል፦ ስሜት የሚነካ ዜና ሰማን፤
ዳምጠው፦ በርግጥ ተገደድሁ። በሌላ በኩል ደግሞ ፈጣሪ ደግ ነው። በኖርዌይ ወገኖቼ ኮርቻለሁ። ደረሱልኝ። ደገፉኝ። አበረታቱኝ። በህይወት ዘመኔ አልረሳውም።

ጎልጉል፦ ምን ገጠመህ?
ዳምጠው፦ ስደት ጠባሳው ቀላል አይደለም። የውስጥ ስሜቴን አጣሁት። ታመምኩ። ልጆቼና ባለቤቴ ራቡኝ። ሰባት ዓመት ናፍቆት ለበለበኝ። ባዶ ቤት ታቅፌ ገፋሁት። ዓመታት በተቆጠሩ ቁጥር ቤተሰቦቼን የማይበት ተስፋዬ አለቀ። ቀደም ሲል ኦስሎ እያለሁ ወንድምና እህት የሆኑኝን የኦስሎ ወገኖች እየተቀላቀልኩ ብቸኛነትን መቋቋም ችዬ ነበር። ከሶስት ዓመት በፊት የመኖሪያ አድራሻዬን ቀየርኩ።

ጎልጉል፦ ለምን?
ዳምጠው፦ ኦስሎ እያለሁ እርዳታ በማገኝበት ስርዓት ውስጥ አልነበርኩም። በዛ መልኩ መቀጠል ስላልነበረብኝ እየተደገፍኩ ለመኖር ባቀረብኩት ጥያቄ መሰረት ወደ ዮቪክ ተዛወርኩ። ላለፉት ሶስት ዓመታት ብቻን ትልቅ ቤት ታቅፌ ገፋሁት። የሚያናግረኝ አልነበረም። ከትምህርት ቤት ስመለስ ብቻዬን ቤት ውስጥ ስቀመጥ ከቀን ወደ ቀን ብቸኛነቱ ጎዳኝ። በሽተኛ ሆንኩ። ሁኔታው እየከፋ ሲሄድ ሃኪሜ የአገሩ ሰዎች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ መኖር አለበት በማለት ወደ ኦስሎ ተዛወርኩ።

ሶስት ኢጲስ ቆጶሳት ለፓትርያሪክ እጩነት ቀረቡ፤ የኢት.ኦ.ተ.ቤ.ክ እርቀ ሰላም ሊወርድ ይችል ይሆናል ተብሎ ይገመታል!





መንግስት አቡነ ጳውሎስን ለመተካት 3 ጳጳሳትን አጨ (በሁለቱ ሲኖዶሶች እርቅ ዙሪያ አዳዲስ መረጃዎች ዘ-ሐበሻ እጅ ገቡ)- መንግስት አቡነ ጳውሎስን ለመተካት ያዘጋጃቸው 3ጳጳሳትን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ደረሱበት - ”መንበሩን ኢትዮጵያ ገብቶ የመረከብና ያለመረከብ
ምርጫ የፓትርያርክ አቡነ መርቆርዮስ ነው” - የአቡነ ጳውሎስን “ሌጋሲ” የሚያስፈጽሙት አቡነ ገሪማ ይገኙበታል (ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ እና በውጭ ሃገር የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ሊቀመጡ መሆኑ ተሰማ። የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች እንደጠቆሙት ከሆነ በአዲስ አበባ የሚገኘው ሲኖዶስ ከጥቅምት 21 ቀን 2005 ጀምሮ እንዲሁም በውጭ ሃገር የሚገኘው ሲኖዶስ ደግሞ ጥቅምት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ጉባኤያቸውን ይጀምራሉ።
በአዲስ አበባም ሆነ በውጭ ሃገር የሚገኙት ሁለቱ ሲኖዶሶች በዚህ ጉባዔያቸው ላይ “በአቡነ ጳውሎስ ቦታ ላይ ማን ይሾም? 4ኛው ጳጳስ አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው ይመለሱ ወይስ አይመለሱ? መንግስት የራሱን ጉዳይ እንዲያስፈጽሙ ያስቀመጣቸው 3 ጳጳሳት መካከል አንዱን እንምረጥ ወይም አንምረጥ?” በሚሉት ዋነኛ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ጠቁመው ከዚህ በተጨማሪም ይህ በሁለት ሃገራት፤ በሁለት ሲኖዶሶች የሚደረገው ጉባኤ ሌሎች የቤተክርስቲያን ጉዳዮችን ያነሳል ተብሎ ይጠበቃል።

የበአሉ ግርማ ጆሮጠቢ “የማውቀውን ሰላይ ካባረርኩማ የማላውቀውን ይተክሉብኛል” (በአሉ ግርማ)






              በኛ ዘመን የብእር ሰው ሆኖ መፈጠር መረገም ሆኖ ይሰማኛል። ከቡቃያው የሚነጋገር፣ በሁዳዱ ላይ ሽምጥ ፈረስ የሚጋልብ፣ ውሎው ከዋልካው፣ ማምሻው ከመልካው የሆነ ገበሬ እንዴት እድለኛ ነው? የኛ ዘመን ብእረኛ ህይወቱ በሰላዮች የተከበበ ነው። ተፈጥሮው ነውና አለመፃፍ አይችልም። መፃፍ ደግሞ አደጋ ነው። በአሉ ግርማ እንዲህ ባለ ችግር ውስጥ አልፎ፣ በከንቱ ያለፈ ደራሲ ነበር። ደርግ ብዙ ሰላዮች መድቦበት ነበር።
በአሉ ግርማ ምንም እንኳ ከደርግ ሰዎች ጋር በቅርብ ይሰራ የነበረ ሰው ቢሆንም ህሊናው ግን ነፃ ነበር። የደርግ የፀጥታው መስሪያ ቤት የበአሉን ነፃ መንፈስ በማወቁ፣ ነፃ ለቆት አያውቅም። በሰላዮቻቸው ከበውት ኖረዋል። በአሉ ግርማን እንዲሰልሉ ከተመደቡት አንዱ አይነስውር ለማኝ ሆኖ ነበር የሚተውነው። በአሉ ግርማ መኪናውን ውቤ በረሃ አቁሞ፣ እዚያው መኪና ውስጥ ሆኖ ሲቀመቅም፣ አይነስውር መሳዩ ለማኝ ወደ በአሉ መኪና ጠጋ ብሎ ይለምናል፣
“ስለ መድሃኒያለም፣ በቀን ጨለመብኝ። ሌትና ቀኑ ተደባለቀብኝ። በኔ የደረሰ በዘርማንዘራችሁ አይድረስባችሁ። ስለመድሃኒያለም ስትሉ እርዱኝ እባካችሁ።”
ይህ ለማኝ ሰላይ መሆኑን ግን በአሉ ግርማ ገና ድሮ አውቆ ነበር። ሆኖም ያላወቀ መስሎ በመጣ ቁጥር አስር ሳንቲም ይሰጠዋል። ሰላዩም አይኖቹን እንደ ፀደይ የቢራቢሮ ክንፍ ብልጭ ድርግም እያደረገ አስር ሳንቲሟን ተቀብሎ፣ በአሉ ግርማ ከማን ጋር እንዳመሸ ተመልክቶ ሲያበቃ፣ በነጋታው በማያዩት አይኖቹ ያየውን ለተስፋዬ ወልደስላሴ ቢሮ ሪፖርት ያደርጋል። ይህ ድብብቆሽም ለረጅም ጊዜ ቀጠለ።
ከእለታት አንድ ቀን በአሉ ግርማ እና ስብሃት ገብረእግዚአብሄር የበአሉ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው እያወጉና እየቀመቀሙ ነበር። ስብሃት እንዳጫወተኝ በመካከሉ የበአሉ ደምበኛ የሆነው አይነስውር ለማኝ መጣ፣
“ስለ ጊዮርጊስ…በቀን የጨለመብኝ…”
አስርሳንቲሙን ከተቀበለ በሁዋላ የሚያየውን አይቶ ተመልሶ ሄደ። በዚህ ጊዜ በአሉ ግርማ ለስብሃት እንዲህ አለው፣
“ለማኝ አይደለም። ሰላይ ነው…”
“እንዴት አወቅህ?”
በአሉ ግርማ እንዴት እንዳወቀ ለስብሃት አጫወተው። በዚህ ጊዜ ስብሃት በጣም ተበሳጨና እንዲህ አለው፣
“እንደነቃህበት ነግረህ ለምን ቆሌውን ገፈህ አታባርረውም? ለምንድነው በየቀኑ አስርሳንቲም የምትገብረው?”
በአሉ እየሳቀ እንዲህ መለሰ፣
“የማውቀውን ሰላይ ካባረርኩማ የማላውቀውን ይተክሉብኛል”





የረጅም ጊዜ እግርኳሳዊ ስቃይ በጥልቅ ደስታ ተተካ


  ·
October 15, 2012
By Fisseha Tegegn





ኢትዮጵያን ወደአፍሪካ ዋንጫ ከረጅም ጊዜ በኋላ የመለሷትን ሁለት ጎሎች ያስቆጠሩት አዳነ ግርማ እና ሳልሀዲን ሰኢድ እንዲሁም ደጋፊዎች ደስታቸውን በተለያየ መልኩ ሲገልጹ

ስቃይ መጨረሻው እንዲህ ሊያምር ከሆነ እንኳንስ ተሰቃየሁ የሚል አስተያየት ላይ ለመድረስ የተቃረብኩበት ቀን ቢኖር የኢትዮጵያ እና ሱዳን ጨዋታን የመሩት ሴኔጋላዊው ዳኛ የጨዋታው ማብቂያን እና ኢትዮጵያ ከ31 አመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ መሳተፏን ያረጋገጠው ፊሽካቸውን ድምጽ ሲያሰሙ ነበር። አዎ፤ የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን መስራች አባል የሆነችው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ ከተሳተፈች 31 አመታት አልፈዋል።

በረጅም ጊዜ እግርኳሳዊ የስቃይ ስሜት የተወጠረው አእምሮዬ ታዲያ ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት ያስብ የነበረው ልክ ሌሎች ጨዋታዎችን ሲያይ እንደሚያስበው “ምን አይነት አሰላለፍ ይዘው ይገባሉ? እንዴት ክፍት ቦታዎችን ይጠቀሙባቸዋል? ምን አይነት ታክቲክ ይጠቃማሉ?” የሚሉ ጥያቄዎችን ሳይሆን፤ “ታሪክ ‘ኑ እና ውሰዱኝ’ ብሎ እጁን ከዘረጋ በኋላ ይነሳን ይሆን” የሚለውን በፍራቻ የታጀበ ስሜትን ነበር።

አትፍረዱብኝ ከ31 አመታቱ የኢትዮጵያ እግርኳስ ስቃይ ውስጥ ቢያንስ ከ15 አመታ በላይ የሚሆነውን አብሬው ተሰቃይቻለሁ። እጅግ በጣም በማከብራቸውና በማደንቃቸው የእግርኳስ ተጨዋቾች በተለያየ ጊዜ የተገነቡት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድኖች ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ሳይችሉ ሲቀሩ ያየ ልብ እና አእምሮ እንዴት አሁን አይጨነቅ?