"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 14 April 2016


በዶ/ር አለማየሁ ዋሴ እሸቴ ከታተመው እመኋ ከሚለው መጽሐፍ ላይ የተወሰደ።

ለእኛ ዘመን የተሰጠ የማንቂያ ተግሳጽ!!!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

" በአፍላ ትጀምራላችሁ በወረት ትተውታላችሁ። ያወቃችሁትን ትረሳላችሁ ፣ ያላወቃችሁትን ለማወቅ ትጥራላችሁ ፣ የያዛችሁትን ትረግጣላችሁ ፣ ያረገጣችሁትን ትይዛላችሁ። ምኞታችሁ ልክ የለውም፣ አእምሮአችሁ ብዙ ነው። ያማራችሁን ስታገኙ ወዲያው ይሰለቻችኋል። ተው የተባላችሁትን ትሽራላችሁ፣ የተከለከላችሁትን ትደፍራላችሁ ፣ የተፈቀደላችሁን ችላ ትሉታላችሁ። ቤተ መቅደስ እንዳትገቡ ብትከለከሉ ወደፊት ቤተ መቅደሱን በመስታወት ሠርታችሁ መቅደስ ባትገቡም እንኳን ሁሉን ከውጪ ሆናችሁ ማየት ትፈልጋላችሁ። ሁሉን ማወቅ ትፈልጋላችሁ በአንዱም ግን አትጠቀሙበትም። ሁሉ አላችሁ ፣ ግን ባዷችሁን ናችሁ። ሃይማኖት እንጂ እምነት የላችሁም!!
......ጥበብን "ሀ ግእዝ" ብዬ ላስተምርህ ብሞክር መንደር ውስጥ በቃረምካት ዕውቀት ተመክተህ በመሰልቸት "ሆ ሳብዕ" ብለህ ቀድመህ ትዘጋዋለህ። የግል ታሪካችሁ ቢታይ ወጥነት የጎደለው ከዚህም ከዚያም የተለከፈከፈ የተማሪ ኩፋዳ ውስጥ ያለ እህል ይመስላል። ተምራችሁ እውቀት ስታገኙ፣ ሠርታችሁ ሀብት ስታፈሩ ከላይ የሆናችሁበትን ሀገር ለቃችሁ ሰፋ ወዳለው እንሂድ ብላችሁ እንደገና ከታች ትጀምራላችሁ። ትቀጥላላችሁ በመጨረሻ ከጀመራችሁበት ትገኛላችሁ። ትቸኩላላችሁ ትወስናላችሁ ወዲያው ትጸጸታላችሁ። በጽኑ ታማችኋል!"
ከታሪክ ፍቅርንና ልማትን ሳይሆን ጥላቻንና ጥፋትን ለይታችሁ ትቆፍራላችሁ። ከዚያም ቀጥላችሁ የከበረ ማዕድን እንዳወጣችሁ ሁሉ በኩራት ደረታችሁን ነፍታችሁ ሳትመርጡ ሁሉን በአደባባይ ትዘሩታላችሁ፣ እናም ወደ ኋላ ስለ ታሪካችሁና ስለ ቅርሳችሁ ባሰባችሁ ቁጥር ፍርሃትና ሃፍረት ይሰማችኋል። ስለሆነን ከኋላ ታሪካችሁና ክብራችሁ እየራቃችሁ መጣችሁ። .......
ቅቤ ላይወጣችሁ ትናጣላችሁ። በዚህ አለም ጥድፊያ ታማችኋል። ሀገራችሁን ትንቃላችሁ፣ ጥላችሁ ለመሄድ ትፈልጋላችሁ፣ ከሄዳችሁ በኋላ ደግሞ አፍታ ሳትቆዩ አገሬ ናፈቀኝ ትላላችሁ። በቁማችሁ የናቃችሁትን የሃገራችሁን አፈር በሞታችሁ ልትለብሱት ትናፍቃላችሁ። ለሀገሬ አፈር አብቃኝ ብላችሁ በድናችሁን ልካችሁ የወገኖቻችሁን ልብ ትሰብራላችሁ። ግብዝነታችሁ መጠን የለውም። ሁለት ሀገር እንዲኖራችሁ ትፈልጋላችሁ፣ አንዱን በደም ሌላኛውን በመታወቂያ ታስባላችሁ። ከአንዱም ግን በአግባቡ አትኖሩም። ዘመናችሁም በምልልስና በመዋተት ያልቃል። ምን እንደምትፈልጉ አታውቁም እናም ፍለጋችሁ አያልቅም።
.... እኛ አባቶቻችንን እናምናለን። በእነርሱም ደስ ይለናል። የነገሩንን ተቀብለን ቃል ኪዳናቸውን ጠብቀን እንኖራለን።
"ጽላተ ሙሴ አክሱም ጽዮን እንዳለች ሲነግሩን መጋረጃ ገልጠን ሳጥን ከፍተን እንይ አላልንም፣
ጌታ የተሰቀለበት የግማደ መስቀሉ ክፋይ ግሼን ማርያም አለ ሲሉን ቆፍረን አውጥተን እንመልከት አላልንም ፣
ቅዱስ ጽዋው ወንዝ ውስጥ አለ ሲሉንም አውጥተን እንመልከት አላልንም"።
" አባቶቻችንን አምነን ሀገራችን የበረከት ምድር መሆኗን ተረድተን የጌታችንን የጸጋ ስጦታ ተቀብለን በእምነት እንኖራለን። ምንም የለንም ሁሉ ግን የእኛ ነው። ድሆች ብንባልም ባለጸጎችም ነን። የተራቆትን ብንመስልም የጸጋ ልብስ አለን። ሐዘንተኞች ብንመስልም ደስተኞች ነን። ስለ ሀገራችን መባረክ ፣ ቅድስት ሀገር መሆን፣ ቅዱስ ቅርስ በእጃችን እንዳለ አለም እንዲያረጋግጥልን አንፈልግም። የሌለንን አለን፣ ያልተሰጠንን ተቀበልን ብለን የምንኮፈስ ግብዞችም አይደለንምና። የሌለን ነገር ለመጠበቅና ለመታመን ስንል ሥጋችንን እየጎሰምን በገዳም ለመኖር የምንወስን ጅሎችም አይደለንምና"።



Saturday 28 November 2015

የ“ሞጋቾቹ” ድራማ ደራሲና ፕሮዱዩሰሯ ባለመግባባት ተለያዩ


Written by  ማህሌት ኪዳነወል
የ“ሞጋቾቹ” ድራማ ደራሲና ፕሮዱዩሰሯ ባለመግባባት ተለያዩ
ድራማው በደራሲ ውድነህ ክፍሌ ሊቀጥል ነው

  በየሳምንቱ ረቡዕ ምሽት በኢቢኤስ ቴሌቭዥን የሚቀርበው የ“ሞጋቾቹ” ተከታታይ ድራማ ደራሲ በሆነው ኃይሉ ፀጋዬና በፕሮዱዩሰሯ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የተለያዩ ሲሆን ድራማው በታዋቂው ፀሐፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ ይቀጥላል ተብሏል፡፡ 

Tuesday 25 August 2015

መታሰር… መፈታት ?!? (መላኩ አላምረw



መታሰር… መፈታት ?!?
(መላኩ አላምረው)

በዚች በሀገሬ
ትላንት እና ዛሬ
ሚደጋገም ወሬ …
አዕምሯያኑ፣
ብዕራውያኑ፣
‹በነውጥ በሽብሩ›
“ታስረው” የነበሩ …
‹‹ተፈቱ! ተፈቱ! ደስ አይልም?›› ይሉኛል፣
እኔ በበኩሌ …
የመታሰርና የመፈታት ትርጉም ተቀላቅሎብኛል፡፡
በአዕምሯዊ ፍጡር - በሰብዓዊ ዓለም፣
መታሰር… መፈታት… ብሎ ነገር የለም፡፡
ወይም ለእኔ አዕምሮ ሐቁ ግልጽ አይደለም!
…..›››
‹‹እግርን በእግረ-ሙቅ - መሄድን ለማስቆም፣
ዓይንን በጨለማ - እይታን ለማድከም፤
እጅን በካቴና - ከብዕር እንዲቋረጥ፣
አናትን በኩርኩም - ላ’ሳብ ጊዜ እንዳይሰጥ፤››
እንዲያው በመመኘት…
እንዲያው በመሞኘት…
ምን ብዙ ቢደከም………
ሰብዕናን ማሰር
እይታን ማሳወር
አዕምሮን ማጣመም
ሂደትንም ማስቆም
ፈጽሞ አይቻልም፡፡
ምክንያቱም….
በአካል ላይ ሚደርሰው ስቃዩ ከፍ ቢልም፣
የነፍስን ባሕርይ - አዕምሮን ማሰር ግን - ለሰው አይቻልም!
በጥበበ አምላክ የአዕምሮ ተፈጥሮ፣
የሚቆም አይደለም እንደ-ሥጋ ታስሮ፡፡
እንዲያውም እንዲያውም…
‹አዕምሮን ራስ› እንጂ ሌላው አያስረውም
እናም እኒህ ሰዎች!
ባለ ህሌናዎች!
ታስረው ነበር አንበል! እስረኞችስ እኛ …
ህሌናችን ክደን፣
ማስመሰልን ለምደን፣
ከሐሰት ተዋልደን… እንቅልፍ የምንተኛ፡፡

Wednesday 14 January 2015

ቅድስት ዕሌኒ

ቅድስት ዕሌኒ




 የቅድስት ዕሌኒ ባለቤቷ ተርቢኖስ ይባላል፤ በቅድስና ተፋቅረው ነበር የሚኖሩት፤ ተርቢኖስ የሚል ጽሁፍ ያለበት የአንገት ሀብል አሰርቶላት ነበር። ተርቢኖስ ነጋዴ ስለነበር ከጓደኞቹ ጋር በመርከብ ተሳፍረው እሩቅ አገር ሄደው  3 ዓመት በኃላ ይመለሳሉ ፤ ታዲያ መርከብ ላይ እንዲህ እያሉ ይጫወታሉ ፤ እኛስ በሰላም ወደ አገራችን ተመለስን ሚስቶቻችን ግን በሰላም ይጠብቁን ይሆን ሌላ ወንድ ወደውና ለምደው እንዳይጠብቁን አሉ፤ ተርቢኖስ ደግሞ የኔ ሚስት ዕሌኒ ከኔ ሌላ ማንንም አትወድም አትለምድም ይላቸዋል፤ ያንተ ሚስት ከሄዋን ሴቶች ትለያለችን እኔ ሄጄ ወድጃት ወዳኝ ለምጃት ለምዳኝ ብመጣ ምን ትሰጠኛለህ ይለዋል ንብረቴ ሁሉ ላንተ ይሁን ይለዋል በወረታቸው ተወራርደው ይሄዳል::

Friday 31 October 2014

የወላዲተ አምላክ ድንቅ ተአምር (አንድ አድርገን ፤ ህዳር 21 2004 ዓ.ም)

የወላዲተ አምላክ ድንቅ ተአም

      )፡- ዛሬ ፃድቃኔ ማርያም ሄጄ በአይኔ ያየሁትን ተአምር ልፅፍላችሁ ወደድኩኝ፡፡ ቀኑ ቅዳሜ ነው ፤ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ወደ ፃድቃኔ ለመሄድ የሚነሱበት ቀን ስለሆነ መጀመሪያ የሚወጣው አውቶቡስ እንዳያመልጠን ከባለቤቴ ጋር በጠዋት ነበር አውቶቡስ ተራ የደረስነው ፤ ነገር ግን ሰው እዛ ያደረ ይመስል 12፡00 ላይ አውቶቡሱ ሞልቶ መንቀሳቀስ ጀምሮ ነበር፡፡ ባለቤቴም ‹‹አይ በዚህም ሰዓት ደርሰን አመለጠን ይገርማል ተወው ባክህ እመቤቴ እንደፈቀደች››አለችኝና ሁለተኛው አውቶቡስ ላይ ገባን፡፡ ይህኛው ደግሞ ቀጥታ ዘላቂ ሰው ስላጣ የመንገድ ሰዎችንም በመጫን ነበር የሞላው፡፡ ጉዞ ወደ ፃድቃኔ ማርያም ፤ ውዳሴዋን ደግመን ጉዞ ጀመርን፡፡ መኪናው ሲያወርድ ፤ ሲጭን 9፡00 አካባቢ  ደብረ ምጥማቅ ደረስን ፤ እዚህ እንውረድና በአቋራጭ እንሂድ ተባብለን ሰላ ድንጋይ ሳንደርስ ወረድን ፡፡ እቃችንን ለአንድ የሀገሬው ሰው አሸክመን አቋራጩን ተያያዝነው ፡፡ ልጁ እንዲህ አለን ‹‹ ዛሬ ግን ማደሪያ የምታገኙ አይመስለኝም በጣም ብዙ ሰው ነው የመጣው አለን›› :: ‹‹ችግር የለውም ውጪ አንጥፈን እናርፋለን ለመተኛት መች መጣን››አልነው፡፡




ደጇን ስንረግጥ ልጁ ያለው አልቀረ የወንዶች ማረፊያ ሁለቱም አዳራሽ ከአፍ እስከ ገደቡ ሞልቷል ፤ በረንዳውን ላይ ብናይ የበረንዳው ይብሳል ፡፡ የኔን ማረፊያ ውጭ አነንጠፍንና የእሷን ለማየት ወደ ሴቶች ማረፊያ እያቀናን ሳለ ፤ አንዲት መንፈስ ያደረባት ሴት ፤ እጇም እግሯም በሰንሰለት ታስራ እንዲ እያለች የእመቤታችንን ማዳን ትመሰክራለች ‹‹ ዛሬ ደግሞ ኪዳነምህረት ድንቅ ነገር ሰርታለች ሂዱነና እዩ›› እያለች ለሰዎች ስትናገር እንደ አጋጣሚ እኔም ሰማሁ፡፡ እሷ የጠቆመችን ቦታ ላይ ስንሄድ አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ልጅ እና እህትየዋ አንድ ላይ ቆመው ተመለከትን ፡፡ ጠጋ ብለን ምን ተደርጎላቸው ነው ስል ስጠይቅ ‹‹ የዚች ህፃን አይኗ በራላት›› ሲሉ ነገሩን፡፡ ለኔ የተደረገልኝን ያህል ደነገጥኩኝ፤ በጣምም ደስ አኘኝ፡፡ እህትየዋ የምትይዘውን የምትጨብጠውን ነገር አጥታ ነበር ፡፡ ታናሽ እህቷ የተደረገላትን ነገር እያየች ከአእምሮዋ በላይ ስለሆነ እና ደስታው ፈንቅሏት ታለቅሳለች  ፤ እኛም ገርሞን ማደሪያችንን ትተን ልጅቷ ጋር ረዥም ደቂቃዎች ስለሁኔታ ለመስማት እዛው አረፍ አልን ፡፡ እህትየዋም ሰዎች ጥያቄዎችን ሲጠይቋት እንዲህ አለች ፡-