"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 19 December 2013

ምስጋና ለአያሌው ጎበዜ – አክባሪዎ አቢሲኒያዊ

አያሌው-ጎበዜእርስዎ ብዐዴን/ህወሀትን ወክለው የአማራን ህዝብ ሲመሩ መቆየትዎ ይታወቃል በዚህም የክልሉ ህዝብ ኤያሌው ጎበዜ     ለዘላለም ይኑር እያለ እንዲኖር ማድረግዎትን
                                                                                                                  የሚያስታውሱት ነው   ደመቀ መሬቱን ድንጋይ ያድርግለት እና በመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ይገባሻል ብሎ መለስም ብራቮ እንዲህ ነው እንጂ ተላላኪ ብሎ ትምህርት ሚኒሰቴር ሲያደርገው ለእርስዎ ግን ቅንጣት ታህል አለመስጠቱ ሱዳኖች እንኴን እንዲታዘቡት አድርጔል፡፡
እርስዎም ደመቀ ምክትል ጠ/ሚኒስቴር ሲሆን ቅናት ቢጤ አድርዎቦት ከሳምንታት በፊት 40 ካ.ሜ ወደ ኢትዮጵያ ገብተው የሀገሮትን መሬት ለሱዳን ማስረከብዎን ሰምቼ ድሮስ የጎበዤ ልጅ ከማን ያንሳል ብዬ ኮራሁ፡፡ በነገራችን ላይ ሰሞኑን መሬታችን ለሱዳን መሰጠቱን ተከትሎ የእርስዎ የቅርብ ዘመዶች ቤታቸው የተሸጠው መሬት ላይ በመገኘቱ ሱዳን ለዘላለም ትኑር አባይ የሱዳን ነው እያሉ መዘመራቸውን ሱዳን የሚገኝ ወዳጄ ሹክ ብሎኛል፡፡
እናማ ይሄውልዎ ተሰናባች አያሌው የእርስዎ ክልል ግዞት የሆነው የአማራ ህዝብ ብዙ እየሰማ እና እየተሰማው ሲኖር አንድም ቀን ተናግርዎት አያውቅም ለምን መሰለዎት ምን አልባት ነጋዴው ክልሉን ለሱዳን ሸጠው ከመለስ ዜናዊ አገዛዝ ነፃ ያወጡናል ብሎ ስላሰበ ይሆናል፡፡ የአማራ ክልል ህዝብ ለእርስዎ ያላቸውን ፍቅር የተረዳሁት ጉራፈርዳ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ጉራፈርዳ በቃን አያሌው ጎበዜ ናፈቀን ብለው ቢለመኑ እምቢኝ ብለው እርስዎ ክልል ሲመጡ ነው፡፡
እናም በመጨረሻም እንኩ ምስጋናዬን ተቀበሉ
1.   ሰፊውን መሬታችንን ሽጠው ጠጋ ጠጋ ብለን በመኖር ማህበራዊ ህይወታችን እንዲጠናከር በማድረግዎ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
2.   እንደ መለስ ዜናዊ ስልጣን ላይ ሳይሞቱ በመልቀቅዎ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
3.   በ1998 በኮምቦልቻ፣ በ1999 በደሴ፣ በ2000፣ በ2003 የጎንደር እና የጎጃም ህዝብን በወያኔ ወታደሮች በጥይት አስገድለው ከዘንድሮው የኑሮ ውድነት እንዲያመልጡ ስላደረጉ ምስጋና ይገባዎታል፡፡
አክባሪዎ ሁኔ አቢሲኒያዊ
ከፒተርቦሮው ዩ.