"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 27 February 2014

‹‹ ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል ››


ስለታክሲ ጥቅሶች ማውራታችን ካልቀረ እስቲ የታዘብካቸውንና ያነበብኳቸውንና ትንሽ ፈገግ ያደርጋሉ ያልኳቸውን ላካፍላችሁ፡፡

·    የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ·  ሠውን ማመን ተፈራርሞ ነው·  ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
·
   በቴሌቶን ሂሳብ መክፈል ክልክል ነው
·
   ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
·
   ለፀባይኛ ተሳፋሪ የፀባይ ዋንጫ እንሸላማለን
·   ለስራ ነው የወጣነው
·   በመጀመሪያ የጋለ ደምህን ተቆጣጠርና ሀሳብህን ግለፅ
·
    ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
·
   ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
· 
 ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
·   ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
·   ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
·   ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር

Tuesday 25 February 2014

ከበዕውቀቱ መጣጥፎች ውስጥ ሁለቱን ጀባ ልበላችሁ\\

ኢትዮጵያ እመ-መከራ
የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ
መውደቅማ ነበር ያባት
እንደ ያሬድ እስከ ሰባት
እንደ በላ ብላቴና ፣ የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ
የትውልዴ እጣ ፋንታ ፣ መውድቅ መውድቅ መውድቅ ብቻ…

አጤ ካሌብ የተባለ የኢትዮጵያ ንጉሥ ባንድ ወቅት በቅድመ-እስልምና የመን የሚኖሩ ክርስቲያኖች ባንድ ያይሁድ ገዥ መዳፍ ስር መማቀቃቸው አስቆጥቶት ቀይ ባሕርን ተሻግሮ ተበቅሎላቸዋል። የዛሬውን አያድርገውና ፣ እንኳን ለቤት ለጎረቤት ጥቃት የሚቆረቆር ንጉሥ ማፍራት ችለን ነበር፤ አንኳን ለቤት ለጎረቤት እርዳታ የሚበቃ ጉልበት ማካበት ችለን ነበር ። ዛሬ ግን ጊዜ ከካሌብነት ወደ ከልብነት ደረጃ አውርዶናል። (“ከልብ” በግዕዝ ውሻ ማለት ሲሆን በአማርኛ ዘይቤ አንድ ሰው ያለ ካሳ ያለ ጉማ ደሙ ፈሶ ሲቀር ደመ ከልብ ሆነ ይባላል)።
አቅመ-ቢስ ሕዝቦች በጉልቤ ሕዝቦች መዳፍ ስር ገብተው መከራ ማየታቸው በታሪክ ብርቅ አይደለም። እኔን የሚገርመኝ በፋንታችን መከራ ማየታችን አይደለም ፤ እኔን የሚገርመኝ ከዚህ ሁሉ መከራ በሁዋላ ከመከራ የሚታደገን የኑሮ መላ አለማፍለቃችን ነው። ከመከራ መደራረብ በሁዋላ ያፈለቅነው የስልጣኔ ፍሬ የሙሾ ግጥም ብቻ መሆኑ ያስደንቃል።
አይሁድ በሁለተኛው ያለም ጦርነት ግፍ ከደረሰባችው በሁዋላ አንሰራርትው በርትተዋል፤ እንደ ኒቼ “ጨርሶ የማያጠፋኝ ሁሉ ያበረታኛል” ብለዋል። ዛሬ በነዳጅ መስክ ላይ የበቀሉ አረሞችን (አረቦችን) ያርበደብዳሉ ። ጀርመኖች በሁለተኛው ያለም ጦርነት ማክተሚያ ላይ በጠላቶቻቸው ከስክስ ጫማ ደቀዋል። ግን በአጭር ጊዜ አንሰራርትው ሃይላችውን እንደ ንስር አድሰዋል፤ እኛስ ይሄን ማድረግ ያቅተናል? አያቅተንም። ያገራችን አስተዳዳሪዎች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ ሀያል መንግስቶች ከመከራ ዶፍ የማይታደጉን ነዳላ ጃንጥላ መሆናችውን አይተናል። የራሳችን አዳኞች ራሳችን መሆናችንን አንርሳ ፤ ጎበዝ የዳይኖሰርን ፈለግ ከመከተላችን በፊት ትንሽ መላ እንምታ::

“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው” ዑጋንዳ የጸረ ግብረሰዶማውያን ሕግ አጸደቀች!

musevini


የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ “አከራካሪ” ሲባል የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡ ግብረሰዶማውያንን “ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ” እና “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ ግብረሰዶማዊነት በምዕራቡ ዓለም አማካኝነት ወደ አፍሪካ እየተስፋፋ የመጣ ነው ብለዋል፡፡

ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ  ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡
uganda 1ሕጉን በፊርማቸው ያጸደቁት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ሲኤንኤን ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ግብረሰዶማውያን “አጸያፊ ሰዎች ናቸው፤ ምን ዓይነት ድርጊት ይፈጽሙ እንደሆነ አላውቅም ነበር፤ በቅርቡ የሰማሁት ግን በጣም አስደንጋጭ ነው፤ ጸያፍ ነው” ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሲቀጥሉም ሰዶማውያን ሲወለዱ ጀምሮ እንደዚሁ ናቸው ስለተባለ ሁኔታውን እውነት አድርገው በመውሰድ ቸል ሊሉት እንደነበር ሆኖም ግን እስካሁን ምንም ሳይንሳዊ ማስረጃ እንዳልቀረበበት ተናግረዋል፡፡
ሙሴቪኒ ሕጉን እንዲያጸድቁ ያደረጋቸውን አንዱን ምክንያት ሲጠቅሱም፤ ግብረሰዶማዊነት ከጄኔቲክስ ጋር በተያያዘ ከውልደት ጀምሮ የሚመጣ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው በማለት ይገምቱ እንደነበር ሆኖም የአገራቸው ሳይንቲስቶች ይህንን መከራከሪያ ውድቅ ማድረጋቸውን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ሕጉ በፕሬዚዳንቱ ፊርማ ከጸደቀ በኋላ ወዲያውኑ በሥራ ላይ የዋለ ሲሆን ግብረሰዶማዊ ወሲብ ሲፈጽም የተገኘ ማንኛውም ሰው እስከ ዕድሜ ይፍታህ በሚደርስ እስራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ በወንጀሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ በ14ዓመት እስር ይቀጣል፡፡ በተደጋጋሚ ወንጀሉን ሲፈጽሙ የተገኙ፣ ዕድሜያቸው ካልደረሱ ጋር እንዲሁም ከአካለ ስንኩል ወይም ከኤችአይቪ ተጠቂ ጋር ወንጀሉን የፈጸሙ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ሕጉ ያዛል፡፡
ናይጄሪያም ከአንድ ወር በፊት ተመሳሳይ ሕግ ያወጣች ሲሆን የዑጋንዳው ሕግ በረቂቅነት ከወጣ የዛሬ አራት ዓመት ጀምሮ ምዕራባውያን ከፍተኛ ተጽዕኖ በማድረግ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን፤ ከሆነም በአብዛኛው የህጉ ክፍል እንዲሸራረፍ በርካታ ሙከራዎችን፣ ማስፈራሪያዎችንና ውስወሳዎችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡no homosexual
በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል፡፡ ሌሎች አገራት ግን እንዲህ ዓይነቱ የዕርዳታ ማቋረጥ ውሳኔ ዑጋንዳውያንን የሚጎዳ በመሆኑ እርምጃው መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡
የዑጋንዳ ሕግ አውጪዎች ያረቀቁትን ሕግ በፈረሙበት ጊዜ ሙሴቪኒ እንዳሉት ምዕራባውያን በዑጋንዳ ጉዳይ በግልጽ ጣልቃ እየገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ “አፍሪካውያን በሌሎች ላይ የራሳችንን አመለካከት አንጭንም” ያሉት ሙሴቪኒ ምዕራባውያን እስካሁን ያደረጉት ጣልቃገብነት ትክክለኛ እንዳልነበረ እና ይህም ደግሞ “ማኅበራዊ ኢምፔሪያዝም” ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡ ግትርና ግዴለሽ ምዕራባዊ ድርጅቶች የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፋፋት እየጣሩ መሆናቸውንና ለዚህም ሰዶማዊነት ተግባር የኡጋንዳን ህጻናት እየደለሉ ወደ ግብረሰዶማዊነት ወንጀል እንደሚያስገቧቸው ከሰዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሰዶማውያን ደሃ ዑጋንዳውያንን ዒላማቸው በማድረግ በገንዘብ በመደለል ለግብረሰዶማዊነት እንደሚጋብዟቸውና ቀጥሎም ለግብረሰዶማዊ አዳሪነት እንደሚዳርጓቸው ሙሴቪኒ ተናግረዋል፡፡
የዑጋንዳን ውሳኔ አስመልክቶ የማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ የሆኑ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት “ኢህአዴግም ከየምዕራቡ ለሚለቃቅመው ዕርዳታ ብሎ የአገርን ባህልና ማኅበራዊ እሴት ከሚያጠፋ ይልቅ ተመሳሳይ ተግባር ሊወስድ ይገባዋል፤ የተቃወመውን ሁሉ “አሸባሪ” በማለት በጸረ አሸባሪ ህግ ስቃዩን ከሚያሳይ የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በማውጣት ይህንን በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ወረርሽኝ መላ ሊለው ይገባል” ብለዋል፡፡