"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 8 August 2014

..የፍልሰታ ስጦታ!...እውነተኛ ታሪክ

..(...የፍልሰትዋ ተአምር...)

ከቅርብ ዓመታት በፊት ነው! በግብፅ ይኖር የነበረው ወጣት ምንም እንኳን ገና በወጣትነቱ በትምህርት፣ ሃብትና ትዳር "የተሳካለት ሰው" የሚባል ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በፊት ግን ይመካበት የነበረውን ትዳሩን ጥያቄ ውስጥ ገብቶበታል:: ባላወቀው ምክንያት የሚወዳት ባለቤቱ ከወገብ በታች ፓራላያዝ ትሆናለች:: እርስዋን ለማሳከም ያልሄደበት ሆስፒታል ባይኖርም የሚሄድበት ሆስፒታል እንደሌለ ግን ተነግሮታል:: "የያዛት በሽታ አይድንም!" የሚል መራራ ሐዘንን ሰምትዋል! ብዙ ያሰበለት የልቡ ፍቅር ሲጠወልግ፣ የወደፊት ሕልሙ ሲጨልም፣ የልጅ አምሮቱም እንዲሁ ላይመጣ ሲቀር አስቀድሞ አውቋል! ባለቤቱ አልጋዋ ላይ ትበላለች አልጋዋ ላይ ትፀዳዳለች! ለጥቂት ጊዜ እዛው አልጋዋ ላይ ሳምንታትንና ወራትን ስታሳልፍ ከራሱ ጋር እየታገለ በትዕግስት ቢያስታምማትም ከዚህ በላይ መቆየት ግን በአካል ሲኦል የመግባት ያህል ሁኖ ተሰማው:: ስለዚህ በፍቺ ከርስዋ ጋር መለያየትን መረጠ:: ነገር ግን ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት አስቀድሞ የንስሃ አባቱን ማማከር እንዳለበት አመነና ወደሳቸው ሄዶ ያሰበውን ይነግራቸዋል! እሳቸው ግን በፍፁም እንደማይሆን፣ ጌታ ያጣመረውን እርሱ መፍታት እንደማይገባ ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሱ ያስረዱታል:: ከዚያም ሁለቱም በጸሎት እንዲተጉና ወደ እመቤታችን እንዲያመለክቱ ተነጋግረው ይለያይሉ:: የንስሃ አባቱም የወጣቱንና የባለቤቱን የክርስትና ስማቸውን ፅፈው በመቅደሱ መንበር ላይ አስቀምጠው ለ 3 ቀና ያህል በፅኑ ፆምና ጸሎት እየተጉ ቆዩ::