"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 22 June 2012

የተለያዩ የተለያዩ ጥሩ እና መጥፎ አባባሎች


ትንሽ ፉገራ፤ የአፋልጉኝ ማስታወቂያ አቶ መለስ የት ናቸው!?


ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፤ እንግዲህ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ጣጣው ይሄው ነው። እያንዳንዷ ጥቃቅን ጉዳይዎ ሁላ ለአደባባይ ትበቃለች። ባለፈው ጊዜ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ደሞዝ ልክ የሰማን ሰሞን፤  ፕሮፌሰር መስፍን በፃፉት አንድ መጣጥፍ ላይ “ስድስት ሺህ አራት መቶ ብር ላጥ እያደረጉ ማሰር ሰለቸን አይባልም! በአግባቡ ከሆነ ማሰርም መፍታትም ስራዎ ነው!” ብለው ወረፍ አድርገዎት ነበር። እናም መተቸትም መወረፍም የስራዎ አካል ነው ማለት ነው። እናም ቻል ያድርጉት!

ትንሽ ፉገራ፤ የአፋልጉኝ ማስታወቂያ አቶ መለስ የት ናቸው!?
ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰውነት ጎዳና መውጣታቸውን አስመልክቶ በርካታ የኢንተርኔት አሳቢ ወዳጆች አስተያየቶችን ሲሰጡ ተመልክተናል።
ከአስተያቶቹ ውስጥ የተወሰኑትን ለማየት ያክል…
“የማይመቱት ልጅ ሲቆጡት ያለቅሳል”  በሚል ርዕስ አንድ ስዕል ተለጥፎ ተመልክተናል። ስዕሉ አቶ መለስ ክስት ብለው በመከራ ለመሳቅ ሲሞክሩ እና አበበ ገላው ከላይ ሆኖ “መለስ ዜናዊ አምባ ገነን ነው… እስክንድር ነጋ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት” ሲል የሚያሳይ ነው።
በነገራችን ላይ እነ እስክንድር ነጋ ላይ ዛሬ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ ውሳኔውን ይሰጣል ተብሎ ይገመታል። በርካቶችም በየ ፌስ ቡካቸው ላይ ንፁሀንን ፍቱልን እነ በርባንን እሰሩልን! እያሉ እወተወቱ ነው… ወደ በርባን ስንመለስ… ብዬ ወደ ስለ ጠቅላይ ሚኒስትሬ የጀመርኩትን ብቀጥል ሌላ ይመስልብኝ ይሆን…!? ስለዚህ እንዳይቀየሙኝ ዝም ብዬ ፌቴን ወደ እርሳቸው አዞራለሁ፤
(ፈጥኖ በደረሰኝ ዜና እነ አስክንድር ነጋ ዳግም ለመጨረሻ ውሳኔ ሰኔ ሃያ እንደተቀጠሩ ሰምቻለሁ! እንኳንም ሰኔ ሰላሳ አልሆነ ሰኔ ሰላሳ የፀብ ቀጠሮ ነው! ብሎኛል መረጃውን አደረሰኝ አሽሟጣጭ!)

አውራምባ ታይምስ (ዋሺንግተን ዲ.ሲ) – የህግ ባለሙያ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች እንዲሁም የኢትዮጵያዊያን ውርስና ቅርስ ማህበር በሰሜን አሜሪካ ሊቀመንበር የሆነው ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ ኢትዮጵያዊን በዲሲው የአላሙዲን ሰፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዳይገኙና ለነጻነትና ዴሞክራሲ የሚደረገውን ትግል አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቀረበ፡፡
ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ

የጀግኖች አባቶች አገር የሆነችው ኢትዮጵያ በትውልድ ሽግግር የተገነባ ማንነቷ በጥቅማጥቅም ሸጠው ዛሬን ብቻ እንኑር የሚሉ ጥቂቶች አገር ብቻ ሆናለች ያለው ዶ/ር ሼክስፒር፣ ጋዜጠኞች ገለልተኛ አመለካከት በማንጸባረቃቸው፣ ተቃዋሚዎች በህገ መንግስቱ የተረጋገጠላቸውን መብት ተግባራዊ በማድረጋቸው ብቻ ለእስር እየተዳረጉ እንዲሁም ሚሊዮኖች በረሀብ አለንጋ እየተገረፉ ባለበት በአሁኑ ወቅት ከወንጀለኞች ጋር አሸሼ ገዳሚ የምንልበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም በማለት ኢትዮጵያዊን ሆዳሞች የሚያቀርቡትን መደለያ ውድቅ አድርገው በዳላስ እንዲሰባሰቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

በሲዳማ ዞን ከፍተኛ የሆነ የዘር ግጭት ሊነሳ ይችላል በማለት የአካባቢው ሰው በስጋት ወድቋል


ሰኔ አስራ አራት ቀን ፳፻፬ ዓ/ም 
ኢሳት ዜና:- የአዋሳ ዘጋቢዎች እንደገለጡ

በሲዳማ ዞን ከፍተኛ የሆነ የዘር ግጭት ሊነሳ ይችላል በማለት የአካባቢው ሰው በስጋት ወድቋል
ት ትናንት በአለታ ጩኮ የተነሳውን ተቃውሞ ተክትሎ በዛሬው እለትም ከአዋሳ በ 10 ኪሜ ርቅት ላይ በምትገኘው ቱላ ከተማ ውስጥ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውንና መኪኖችን አግተው ለመስክ ስራ የሄዱ ሰራተኞች ስራ ሳይሰሩ እንዲመለሱ ማድረጋቸው ታወቋል።
ተማሪዎች በየመኪኖች ውስጥ እየገቡ የወላይታ ተወላጆችን እንዲወርዱ ሲጠይቁ እንደነበር የገለጠው ዘጋቢያችን ትናንት ማታ 2 የወላይታ ተወላጆች በአዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ ተገድለው መገኘታቸው ውጥረቱን አባብሶታል ብሎአል። በአዋሳ ከተማ ዳርቻዎች የሚገኙ ሱቆች ግጭት ይነሳል በሚል መዘጋታቸውን ዘጋቢአችን ገልጧል። የፌደራል ፖሊስ አባላት በብዛት በአዋሳና አካባቢዋ መስፈራቸውም ታውቋል። “አዋሳ ለወላይታ ተሽጣለች፣” አዋሳን እናድን፣ ለተቃውሞ ሰልፍ ውጡ” የሚሉ በራሪ ወረቀቶች እየተበተኑ ነው።
አዋሳ ለወላይታ ተሽጣለች የተባለው ምናልባትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውለድ ቦታ ጋር ሳይያዝ እንደማይቀር ነው ዘጋቢያችን የጠቆመው። ትናንት በአለታ ጩኮ በተነሳው ተቃውሞ 4 ሰዎች መገደላቸውን ፣ በዛሬው እለትም ሱቆች ፣ ትምህርት ቤትና መስሪያ ቤቶች ተዘግተው መዋላቸውን ዘጋቢአችን አክሎ ገልጧል።
በቅርቡ በፌደራል መንግስትና በሲዳማ ዞን ባለስልጣናት መካከል የተካሄደው ውይይት ያለውጤት መበተኑን መግለጣችን ይታወሳል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

Thursday 21 June 2012

ስልሳ ኢትዮጵያዊንን ይዞ በማላዊ ኅይቅ ላይ ይጓዝ የነበረ ጀልባ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ እስካሁን 47 ሰውሞተ


ዋሽንግቶን ፖስት የማላዊ ፖሊስን በምንጭነት ጠቅሶ ባወጣው በዚህ የአሰቃቂ አደጋ ዘገባ 60 ኢትዮጵያዊያንን ይዞ በማላዊ ኃይቅ ላይ ይጓዝ የነበረ ጀልባ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ እስካሁን የ47 ኢትዮጵያውያን ሬሳ መገኘቱንና ቀሪዎቹም ሳይሞቱ እንዳልቀረ ጠቅሷል።

የፖሊስ ሪፖር ህገ ወጥ ስደተኞች ያላቸውን 60 ኢትዮጵያዊያንን የጫነው ጀልባ አደጋ የደረሰበት ካሮንጋ በተሰኘ ከተማ አቅራቢያ ማለትም ከማላዊ ዋና ከተማ 600 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ከምትገኝ ካሮንጋ በተሰኘች ከተማ አቅራቢያ ባለፈው ሰኞ ሌሊት እንደሆነ ተዘግቧል። የአካባቢው ነዋሪዎች  በውሃው ላይ የሚንሳፈፍ የሰው አካል ያዩት ማክሰኞ ጠዋት እንደነበርም ዘገባው አክሎ ገልጿል።

 ችግር ከበዛባቸው የአፍሪካ ሃገራት የሚነሱ ዜጎች በማላዊና ታንዛኒያ እንዲሁም በማላዊና ሞዛምቢክ መካከል የሚገኘውን ፖሮስ የተሰኘውን ድንበር በማቋረጥ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ጥረት ማድረጋቸው የተለመደ ነው ሲል ይሀው ዘገባ ያስረዳል።

Filed in: Amharic Posts

Eskinder Nega Verdict Trial Delayed



(ADDIS ABABA) — An Ethiopian judge has again delayed the verdict in the case of 24 people charged withterrorism, including a prominent journalist and an opposition member, a defence lawyer said Thursday.
The verdict is now expected to be delivered on June 27, in order to give the judges time to “evaluate and pass a decision”, lawyer Abebe Guta said.
Among those charged are prominent journalist Eskinder Nega and opposition member Andualem Arage. Both appeared in court in suits and smiled and waved to friends and family as they filed into the courtroom.
The courtroom was packed with family members, journalists and diplomats, including US Ambassador Donald Booth.
This is the second time the verdict has been delayed. Judges were expected to deliver a ruling on May 11, but said the defendants’ case had not been transcribed in full.
Eskinder was honoured in New York last month with a “freedom to write” award from the US-based media watchdog PEN.

Wednesday 20 June 2012

መለስ ዜናዊ ፕሬዝዳንት ቡሽና ቶኒ ብሌር


መለስ ዜናዊ ፕሬዝዳንት ቡሽና ቶኒ ብሌር
የወያኔው መሪ መለስ ዜናዊ የአሜሪካ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ቡሽና የእንግሊዝ የቀድሞው ጠ/ሚ ቶኒ ብሌር በለንዶን
የጠ/ሚር ቢሮ ሻይ ቢጤ ይዘው ስለ የሃገራቸው የህክምና ሳይንስ እድገት እየተጨዋወቱ ነው።
ቡሽ፡ ይገርማችኋል የአሜሪካ ሳይንቲስቶች ነፍስ ለመስራት ተቃርበዋል ማለት ይችላል፡፤ በቅርቡ በችካጎ ዩኒቨርሲቲ
የህክምና ማዕከል ውስጥ ሁለት እጅ የሌላት ሕጻን ተወለደች። ሳይንቲስቶቹ ባጋጣሚ ህጻኗ በተወለደችበት ቀን ከሞተች
ሌላ ሕጻን ላይ እጆችዋን ወስደው ገጥመውላት አሁን ሁለቱም እጆችዋ የተፈጥሮ እጅ ያህል ጤነኛ ናቸው። ብሎ
በመኩራራት ይናገራል።
ብሌር ፈገግ ብሎና በንቀት አስተያየት ቡሽን መልከት አድርጎ። እናንተ አሜሪካኖች ለካ ገና 18 ኛው ክፍለ ዘመን ላይ
ናችሁ?  እንግሊዝ ውስጥ አሁን አንተ የተደቅክበት እጅ መቀጠል የተሰራው በ18ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ሲል
በመኩራራት ከተናገረ በኋላ እኛ አሁን በጣም ረቀናል። ከአንድ ሰው ሴል ዲ ኤን ኤ በመውሰድ ያንኑ ሴል በላብራቶሪ
ካባዛን በኋላ የሰውየውን ኮፒ ወይም ክሎን መፍጠር ችለናል በማለት ቡሽና መለስ በእንግሊዝ የህክምና ጥበብ
እንደሚደነቁ ሳይጠራጠር እጅግ ተኩራርቶ በፈገግታ ይመለከታቸዋል። እውነትም ቡሽ ማመን አቅቶት እራሱን
እየነቀነቀ አድናቆቱን ገለጸ። መለስ ግን ምንም ሳይገረም እንዲህ ሲል ተራውን መናገር ጀመረ።
መለስ እናንተ ኃያላን መንግስታት ለካ በሳይንስ ረገድ ገና ብዙ ይቀራችኋል። እኛ በርሃ እያለን የሰራነውን ገና የዛሬ 100
ዓመትም የምትሰሩት አይመስለኝም። ሲል
ብሌር  ደሞ ወያኔ በርሃ እያለች... ምን ሰራች ልትል ነው ? ሲል ጠየቀ።
መለስ እኛ በርሃ ሳለን ሁለት ያለ ጭንቅላት የተፈጠሩ ሰዎች አግኝተን ለአንደኛው ዱባ ገጥመንለት ስሙን አባ ዱላ
ስንለው ሌላኛውን ደግሞ ድንች ገጥመንለት አዲሱ ለገሰ ብለነዋል። ሁለቱም ዛሬ ድረስ በሙሉ ጤንነት ከኛው ጋ
ይገኛሉ በማለት ወያኔ በበርሃ የፈጸመውን የህክምና ሳይንስ ጥበብ ነግሮ አስደንቋቸዋል።

Tuesday 19 June 2012

ትንሽ ወሬ፤ ጠቅላይ ሚኒስትርዬ ከሱብኝ!





ትንሽ ወሬ፤ ጠቅላይ ሚኒስትርዬ ከሱብኝ!

ትላንትና ከስንት ጊዜ በኋላ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትርዬን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየኋቸው። ያኔ አበበ ገላው በዋሽንግተን ዲሲ ቆሌያቸውን ከገፈፋቸው በኋላ በቴሌቪዥን መስኮት ስናያቸው ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው። (በቅንፍ፤ እንደ ድሮ ጎረቤት ብንሆን ኖሮ በቴሌቪዥን መስኮት ሲጠፉብን በሳሎናቸው መስኮት ለማየት ሙከራ እናደርግ ነበር። ዛሬ ግን ሩቅ ሆንና ናፍቆታቸው ሲያስቸግረን ሰነበተ! ብዬ ሀሳቢነቴን ለመግለፅ እወዳለሁ።)

አረ እዝች ጋ ሳይረሳ ባለፈው ጊዜ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ሰዎች “አበበ ገላው ዋሽንግተን ዲሲ ያልሄደው በርካታ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ስላሉ እነርሱን ፈርቶ ነው!” ብላችሁን ነበረ። ረስቼላችሁ፤ ሰውየው እኮ አንገታቸውን የደፉት በዋሽንግተን ዲሲ ነው።

ታድያ የዛን ጊዜ ያ ሁሉ የአንገት እና የቅስም ስብራት ያጋጠማቸው የጋዜጠኛ አበበ ገላው ንግግር ብቻ መስሏችሁ ከሆነ ተሸወዳችሁ።

ከውጪ የነበሩት የአካባቢው ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ጩኸትም “ምነው እግሬን በሰበረው!” አስብሏቸው ነበር። ውስጥ ደግሞ አበበ ትንታግ ሲጨመርበት…!  እና ታድያ አዲስ አድማሶች ይሄ ሁሉ ነገር በዋሽንግተን ዲሲ ሲከናወን ደጋፊዎቻቸው የት ሄደው ይመስላችኋል? “በልማታዊ ስራ ተወጥረው ነበር!” ብላችሁ ሳቄን እስቲ አብዙልኝ! “ምን አይነት አዲስ አድማስ መጣ ደሞ ባካችሁ!?”

በነገራችን ላይ አሁንም እርሳቸው እርም የላቸውም የቡድን ሃያ አገራት ስብሰባ ላይ ደግሞ ሊገኙ ሲሄዱ ነው ያየኋቸው። እንደኔ እንደኔ ይሄ ቡድን ምናምን የሚባል ነገር ቢቀርባቸው ይሻላል። በርግጥ ስብሰባ ሊናፍቃቸው አንደሚችል ጠረጥራለሁ።  ምን ችግር አለው ታድየ በፈለጉ ጊዜ የሚሰበስቡት በፈለጉ ጊዜ የሚበትኑት ፓርላማ አላቸው አይደል እንዴ…!?  እዛው እንደሚሆኑ ቢሆኑ ይሻላቸዋል እንጂ፤ ገና ለገና የፈረንጆቹ “ቡድን” አያልቅም እና እርሳቸው “በድን” እየሆኑ የሚመጡበት ምክንያት ምንድነው!?

የሆነ ሆኖ “ታንክ ተደግፈው መፅሀፍ የሚያነቡት ጀግናው ጠቅላይ ሚኒስትራችን” በአበበ ገላው ንግግር የተነሳ ለአንድ ወር ያህል ተሸማቀው እና ተሸምቀው ሲያበቁ ትላንት በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለዋል።

ታድያልዎ፤ ትላንት ሳያቸው ክስት ብለዋል። ምን ሆኑ!? እንዴ ጠንከር ይበሉ እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትርዬ! ቀጣዩ ጩኸት እኮ እየባሰ ነው የሚመጣው! ታድያ ጠንከር ጠንከር ማለት አይሻልም ይላሉ? ቁጣ እና ጩኸት ይህንን ያህል የሚረብሽዎት ከሆነ ግን ዘዴውን ልንገርዎት…!? እሺ አይሉኝም እንጂ ዛሬውኑ ስልጣንዎን ልቅቅ አድርገው አዲስ አገራዊ መግባባት፣ አዲስ አገራዊ ምርጫ ማከናወን! አቤት ያኔ ጤናዎ ላይ ራሱ ምን አይነት መሻሻል አንደሚመጣ ያዩት ነበር።

የባልካኑ የእግር ኳስ ንጉስ!(ቴዎዶር ገስላሴ)


የባልካኑ የእግር ኳስ ንጉስ!(ቴዎዶር ገስላሴ)

ከጥቂት ዓመታት በፊት ይህን ስም ማንም አያውቀውም
ከወላጆቹና አብሮ አደግ ጓደኞቹ በስተቀር ዛሬ ግን በዓለም
ላይ ያሉ የኳስ አፍቃርያን በሙሉ ማለት ይቻላል ይህን
ምትሃተኛ የቀኝ መስመር ተከላካይ ተጫዋች ዐይናቸውን
ሳያሹ የአውሮፓው ክስተት መሆኑን ያምናሉ።ይህ ልጅ ማን
ነው?የት ተወለደ?የትስ አደገ?ግለ ታሪኩን ቆንጥሬ
ላካፍላችሁ ወደድኩኝ።
ቴዎዶር ገስላሴ
24/12/86 እ.ኤ.አ. በቀድሞዋ ቼኮዝላቫኪያ በአሁኗ ቼክ
ሪፐብሊክ ለትምህርት ሄዶ ፍቅር ካጣመራቸው የአገራችን
ዜጋ ከኢትዮጵያዊ አባትና ከቼካዊት እናት በትንሿ
የቼኮዝላቫኪያ ከተማ ትሬቢክ(Třebíč, Czechoslovakia)ተወለደ።
1.82cm ቁመት ያለውና የ25 ዓመቱ ወጣት ቴዎዶር
እግር ኳስን ገና የ7ዓመት ልጅ እያለ ነበር የጀመረው።
በአሁኑ ወቅት ለአገሩ ቡድን ስሎቫክ ሊበራክ ሲጫወት፣
ለወጣት ብሔራዊ ቡድኑም አገልግሏል፣በቼክ ታሪክ
ውስጥ የመጀመሪያው ጥቁር ተጫዋች ሲሆን በቀለሙ
ከባላንጣዎቹ የስፓርታ ፕራግ ደጋፊዎችና አሁን
እየተካሄደ ባለው 2012የአውሮፓ ዋንጫ ላይም ከሩሲያ
ደጋፊዎች የዘረኝነት ፀያፍ ስድቦች ደርሰውበታል።
ስለዚህ ጉዳይ ሲጠየቅ ግን¨እኔ ምንም አስተያየት
አልሰጥም¨በማለት ጉዳዩን ለጋዜጠኞች ዘግቶታል።
ቴዎዶር ቼክ የምትመካበት ድንቅ ተከላካይ ብቻም
ሳይሆን ፈጣንና ንቁ፣ለጎል ኳሶችን አመቻችቶ የሚሰጥ፣
በሌሎች ትልልቅ የአውሮፓ ቡድኖች የሚፈለግ የወቅቱ
ክስተት ነው።የት መጫወት እንደሚፈልግ ሲጠየቅ
¨የስፔን እግር ኳስ ይስበኛል እወደዋለሁም¨ በማለት
አጭርና ግልፅ መልስ ሰጥቷል።የዚህ ኢትዮ-ቼካዊ ወጣት
ማረፊያ የት ይሆን?
*መልካም የጫወታ ዘመን ይሆንለት ዘንድ የሁላችንም
ኢትዮጵያዊያን ምኞት ነው!¨ደም ከውሃ ይቀጥናል
ይባል የለም?¨

Like ·

የስደቱ ወላፈን በኖርዌ


የስደቱ ወላፈን በኖርዌ
(ክፍል ሁለት)
ከብ.ወ

                          ናታን "መጠቀምያ" ወይንስ "የስደቱ ፖለቲካ የጥቃቱ ሰለባ"?

ዘወትር በሚታተሙት የኖርዌ ጋዜጦች ላይ ሕፃኑ ስደተኛውን ናትንን ያዘለ ዜና እስከነፎቶግራፉ ብቅ ይላል።
ምናልባት ማጋነን አይሁን እንጂ ከሃገሪቱ ንጉሳዊ ቤተሰቦች ይልቅ በሰሞነኞቹ ጋዜጣ ላይ በመውጣት ረገድ ናታን
የመሪነቱን ደረጃ ሳይዝ ይቀራል ብላችሁ ነው። በእርግጥ በሽብርተኝነት ከተከሰሰው ከአንደርስ ብራይቪክ
ባይበልጥም።
ናታን በዚህች ዓለም በተፈጥሯዊዋ ውድ የዘር ግንድ ሃገሩ ኢትዮጵያ ሳይሆን በኖርዌ መወለዱ የሕይወት ዕጣው
ሆኖ እንጂ ፈቅዶ ያደረገው አይደለም። ናታን በፈረንጅ ሃገር መወለዱ ከእናትና አባቱ የስደት ታሪክ ጋር የተያያዘ
እንድምታ ቢኖረውም እንኳን እርሱ ራሱ - በራሱ ላይ የደነገገው ውሳኔ አይደለም። ናታን የዚህችን ዓለም ውዝግብና
ቅራኔን ያልተረዳ የሰባት ዓመት ጨቅላ ነው።
ታድያ የናታን ወላጆች - "ኖርዌን ለቃችሁ ውጡ" - ወይንም ደጎም - "ጉዳያችሁ እንደገና እስከሚታው ቆዩ"  -
እየተባለ ወዲህና ወድያ ሲያወዛውዟቸው ናታንንም አብረው ያንገላቱታል። ይህ ሁኔታ የየሰዉ ዓይን የሚበላቸውን
የወላጆቹን ቅስም ያደቃል። እንደ ኢትዮጵያዊ ሆነን ስንመለከተው ደግሞ ጨርሶ አንገትን አስደፊ ሆኖ እናገኘዋለን።

አበበ ባልቻ እንደ ሕወሐት?




ከተስፋዬ ገ/አብ
“ሰው ለሰው” የተባለው ድራማ በድንገት ከመጠናቀቁ ጋር በተያያዘ በርካታ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው። ትኩረቴን የሳበው ግን ስለ ተዋንያኑ ውክልና ፌስ ቡክ ላይ የተሰራጨው ወግ ነው። ይችን ቁራጭ መታጥፍ ለመክተብ መነሻ ሆኖኛል።
አበበ ባልቻ ሲተውነው የቆየው ገፀባህርይ (አስናቀ አሸብር) እንደ ህወሃት ወኪል ተሰይሞአል። አስናቀ በጠባዩ ለሃገሪቱ ደንታ የለውም። ገንዘብ በጣም ይወዳል። አብሮአደጉን መስፍን ሊበቀለው ይፈልጋል። ተሳዳቢ ሲሆን፣ በጉልበቱ ይመካል። በቅጥረኞቹ በኩል ሰዎችን ያስደበድባል፣ ያስገድላል። ሃብታም ካገኘ ሊዘርፈው በማሰብ ያንዣብባል። ያም ሆኖ ግን አስናቀ መጨረሻው አላማረም። ንብረት ያከማቸበትን አዳራሽ ሲከፍተው፣ በህገወጥ መንገድ ያከማቸው ንብረት ብን ብሎ ጠፍቶአል። የነበረውን ጥሬ ገንዘብ በሙሉ ወዳልታወቀ ሃብታም፣ (አላሙዲ?) በማዛወሩ በድንገት ባዶውን ቀረ። እና የደም ግፊት? አንቀጥቅጦ ገደለው። የቅርብ ረዳቱ እያሳቀበት ህይወቱ አለፈች።

Monday 18 June 2012

“የወያኔ ፌዴራል ፖሊስና ምስኪኑ ገበሬ......”


“የወያኔ ፌዴራል ፖሊስና ምስኪኑ ገበሬ......”
አንድ ገበሬ ካመረተው እህል ጥቂቱን ያህል ወደ ከተማ ወስዶ ለመሸጥ አህያው ላይ ጭኖ በአዲስ አበባ ዙሪያ
ከሚገኘው የገጠር መንደሩ በማለዳ ተነስቶ በቀለበት መንገድ ላይ ጉዞ ይጀምራል። ብዙ ከተጓዘም በኋላ በድንገት
ከኋላው በፍጥነት ይመጣ የነበረ ፌዴራል ፖሊሶችን የጫነ ትራክ እሱንም አህያውንም ክፉኛ ይገጫቸውና ገበሬው
በአንድ ጥግ አህያውም በሌላው ጥግ ተፈናጥረው ይዘረራሉ።
ይህ ከሆነ ከ15 ቀን በኋላ ገበሬው የትራኩን ሹፌር ከሶ ፍርድቤት ያቆመዋል። የትራክ ሹፌሩ ጠበቃም ገበሬውን ራሱን
በምስክርነት ይጠራዋል።
ገበሬው መዳፉን በመጽሃፍ ቅዱስ ላይ አስቀምጦ በእውነት  ለመመስከር መሃላ ከፈጸመ በኋላ በደረሰበት ጉዳት
አከርካሬው ተሰብሮ ነበርና ቆሞ ለመመስከር ስለማይችል ዊልቸሩ ላይ እንደተቀመጠ ጠበቃው ጥያቄውን ቀጠለ።
ጠበቃ፡ የፌዴራል ፖሊስ አባል የሆነው 10  አለቃ  ሃጎስ  በርሄ ያሽከረክረው በነበረው ትራክ ላደረሰብኝ ጉዳት ካሳ
ይክፈለኝ ብለሃል?
ገበሬው! እንዴታ አዎ! ብያለሁ ይ! ጉዳቱንም ሃኪም አርጋግጦታል፤ ይሀው ማስረጃው! አከርካሬዬ ተሰብሮ..! አድቅቆ
ጥሎኝ...እያለ በምሬት ሊቀጥል ሲል ጠበቃው ጣልቃ ገብቶ፤ እሺ ይበቃል መልሱ ተመልሷል ወደ ሌላው ጥያቄ
እንለፍ።.....ይላል

በቺካጎ የኢሳት ገንዘብ ማሰባሰብ ፕሮግራም በድል ተጠናቀቀ “በሳውዝ አፍሪካ የአገኘሁት ክብር በሚሊዮን ዶላር አይከፈልም” ታማኝ በየነ


www.maledatimes.com

በቺካጎ የኢሳት ገንዘብ ማሰባሰብ ፕሮግራም በድል ተጠናቀቀ
በሳውዝ አፍሪካ የአገኘሁት ክብር እሚሊዮን ዶላር አይከፈልም ታማኝ በየነ
በቺካጎ ከተማ የተካሄደው የኢሳት የገንዘብ ማሰባሰብ ፕሮግራም በመልካም ጅመር የተከናወነ ሲሆን በእለቱ ከአምስት መቶ በላይ የሚጠጉ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያኖች እና የለውጥ ፈላጊ ኢስቶአክቲቪስቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲ አባላቶች  በስፍራው መገኘታቸው በአካባቢው  የተገኘው ሪፖርተራችን ዘግቦአል። ይህም ሆኖ ሳለ  በአዘጋጅ ኮሚቴው የመክፈቻ ንግግር የተደረገ ሲሆን መልካም አስተዳደር በሃገሪቱ ላይ እንዲሰፍን እና የመገናኛ ብዙሃን ነጻነታቸውን አግኝተው መስራት የሚችሉበትን መንገድ መፍጠር አለብን ብለዋል ።ቀጣዩን ንግግር አክቲቪስት ታማኝ በየነ ከስር መሰረቱ አመጣጡን እና  እና የኪነጥበብ ሰውነቱን ከመግለጽ አንስቶ በአለው የድምጽ መናገር መብትን አስመልክቶ በሃገሪቱ ላይ የሚከናወነወን አሰቃቂ ተግባር ገልጾአል ። ይህም ሲሆ በመንግሥት አስተዳደር ግፋዊ አገዛዝ የሚደረገውን ጭቆና ሲኮንን ተሰምቶአል ። በመቀጠልም በኢትዮጵያ የሚደረጉትን አፈናዎች አስመልክቶ ሲጠቁም በቅርቡ የተካሄደውን የስካይፒ አፈና እና የፍርዱን ሁኔታ ጠቆም ሲያደርግ በሃገሪቱ ላይ መስዋት ከሆኑት አንስቶ የየኔሰው ገብሬ የነጻነት መንፈስ የሁላችንም የትግል ህይወት መሆንን አመክሮ ገልጾአል   በኩል የመለስ ዜናዊ አስተዳደር ፍራቻቸው የመገናኛ ብዙሃን ሲሆን ለዚህም ዋነኛ ምሳሌ የሚሆነው በሃገሪቱ ላይ የተሰማራውን የኢሳት ቴሌቪዥን አፈና እንደምክንያት ገልጾአል ። ለሃያ አንድ አመታት በአስተዳደርላይ የቆየው የወያኔ መንግስት አንድም ቀን እውነትን ሳይናገሩ መውደቂያቸው ደረሰ በአገሪቱ ላይ መንግስግት በሚያስተዳድረው ቴሌቪዥን ከእውነት የራቀ ነው ሲል አብራርቶአል መረጃዎችን በማጣቀስ ባቀረበው ሪፖርት ላይ ዘገባዎቹን ለህዝብ በምስል አቅርቦ አሳይቶአል ።በሌላም በኩል ባሳለፍነው ወር በሳውዝ አፍሪካ የተደረገለትን አቀባበል እና በኢሳት የገንዘብ ማሰባሰብ ፕሮግራም ላይ ለተደረገው ትልቅ ተሳትፎ የሚደነቅ ነው በሳውዝ አፍሪካ ያገኘሁት ወይንም የሰጡኝ  ክብር የሚሊዮን ዶላርስ የሚከፈል አይደለም ።እንደ ሌሎቹ በጥቅም አልንበረከክም እኔ የምኖረው ለህዝብ ነጻነት እና የህሊና ዳኝነት እንጂ ውሸትን ዋሽቼ ለመኖር አይደለም እንደዚያ ቢሆን ኖሮ ቀድሞ ከሼክ መሃመድ አላህሙዲ ጋር የነበረኝን ግንኙነት አላቋርጥም ነበር ።የህሊና ዳኝነት የመንፈስ እርካታን ይሰጣል እንጂ አይጎዳም በማለት አክሎ ገልጦአል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በጂ8 ሰሚት ፕሮግራም ላይ ለመለስ መንግስት ላይ የተጣለባቸውን የግፋዊ አገዛዝ አመልካችነትን  ሃሳብ በገለጸው በጋዜጠኛ  አበበ ገላው አስመልክቶ የምስል ቅንብር በቀረበበት ሰአት የተስብሳቢው ህዝብ በሞቀ አቀባበል  እና ጭብጨባ አድናቆታቸውን ቸረውታል።
መለስ ዜናዊ በጋዜጠኞች ላይ የተናገሩትን የፓርላማ  ንግግር አስመልክቶ “ጋዜጠኞች በመንግስት ሳይከሰሱ በሚሳኤል ይገደላል “ብለው መናገራቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነበር ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች በመላው አለም ተቀባይነት አግኝተው የሽልማት የክብር ተሸላሚ በመሆን ስማቸው በአለም ገናና ሆነዋል በማለት በአለም አቀፍ ተሸላሚ የሆኑትን ሰርካለም ፋሲል፣ዳዊት ከበደ፣ሲሳይ አጌና ፣እስክንድር ነጋ ፣ ርዮት አለሙ በአብነት ሊጠቀሱ በቅተዋል ።
በየጊዜው ለሚከናወነው የኢሳት እርዳታ ማንኛውም ሰው ግዴታውን መወጣት የሚችለው በየወሩ ከኪስ ገንዘቡ 20$ በማውጣት ቢረዳው የወደፊት የሃገሪቱን ነጻነት እና የመገናኛ ፍላጎት ጥማት ማሳደግ እንደሚቻል በተደረገው ፓናል ውይይት ለይ ለመግለጽ ተችሏል። በሌላም በኩል የፕረስ ነጻነትን አስመልክቶ በተለያዩ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ላይ እየተሰራጨ ያለውን የአበበ ገላው የአለም አቀፍ የጋዜጠኝነት ፍቃድ ተነጥቆአል የሚለው የተናፈሰ ወሬ ከእውነት የራቀ ትልቅ ውሸት ነው በማለት አበበ ገላው የገለጸ ሲሆን የመንግስት ሚዲያዎች እንደ አንድ ተራ ሰው እንጂ እንደጋዜጠኛ አለመቁጠራቸውንና ምንም እንዳልተፈጠረ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በውጭ ጉዳይ ሚስኒስቴር ቃል አቀባይ የውሸት ሪፖርት መተላለፉም ይታወሳል ።ሆኖም ግን ይህንን ሪፖርት እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያኖች የመለስ ዜናዊን አስደንጋጭ የሆነ የራስ ምታቸውን በዩቲዩብ እና በሌሎች የቪዲዮ ቻናሎች ላይ መጎብኘታቸውን ለማወቅ ችለናል ።
አበበ በለውም በበኩሉ የህዝብ መረጃ ፍላጎት ተስተካክሎ እስካልቀረበ ድረስ እና ለውጥ እስካለመጣ እኔ እራሴን መስዋእት እስከማድረግ ድረስ ለመድረስ የምችል ሰው መሆኔን እና ለእውነት ብቻ በመቆም ለፕረስ ነጻነት እና  ለህዝብ ህሊና ዳኝነት ለመታገል ወደ ኋላ አልልም በማለት ገልጦአል ።
በመጨረሻም በቺካጎ በተደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ፕሮግራም $ 12.000 ከበጎ ፍቃደኞች የተሰበሰበ ሲሆን ከአንድ ግለሰብ ደግሞ የቴዎድሮስ ካሳሁን ጥቁር ሰው አልበም እና የታደለ ገመቹን አልበም በበጎ ፍቃደኝነት በነጠላ 50 ኮፒዎችን በመስጠት የሽያጩ ገቢ ለኢሳት እንዲሆን ያደረገ ሲሆን በሌላም በኩል ደግሞ በአጼ ሃይለስላሴ ዘመነ መንግስት መገባባያ የነበረውን የብር ኖት የያዘ ስእላዊ ቅርጻ ቅርጽ (እውነተኛ ብር ኖት)በተከፈተው ጨረታ $11369 የደረሰ ሲሆን የጨረታው ሁኔታ ከፍተኛ ፉክክር ስላመጣ  የብር ኖቱን የያዘው የፎቶ ግራፍ ፍሬም ለኢሳት የወደፊት ማሰባሰቢያ ሊያደርግበት እንዲችል ለአሰባሳቢው ኮሚቴ ገቢ እንዲሆን ተደርጓል።

Task force calls upon all Ethiopians to boycott Al amoudi’s Festival, AESAONE


Awramba Times (Washington DC) – Joint task force of Ethiopians in North America, calls upon all freedom loving Ethiopians to boycott All Ethiopian Sports Association One (AESAONE).
According to the press statement sent to Awramba Times, the fraudulent sports event in Washington D.C. from July 1 to July 7, 2012 is backed by the Ethio- Saudi billionaire, Mohamed Al Amoudi, while millions are starving back home.
Read the press statement below.
Press Statement
WE CALL UPON ALL FREEDOM LOVING ETHIOPIANS TO SAY NO TO THE WOYANE FESTIVAL THAT IS BEING ORGANIZED BY ALAMUDI SERVANTS IN WASHINGTON D.C. UNDER THE NAME OF AESAONE
Alamudi’s servants haven’t stopped from trying to accomplish their evil tasks. This group whose members are individuals who have sold their souls for money have come up with a fiasco organization by the name All Ethiopian Sports Association One (AESAONE). They are now organizing a fraudulent sports event in Washington D.C. from July 1 to July 7, 2012. We want all Diaspora Ethiopians to know that behind this greedy bunch whose daily bread is provided by Alamudi lurks a Woyane ploy to divide Ethiopians in the name of sports.
Dear Compatriots!
This is a call to boycott AESAONE in Washington D.C. by all freedom loving Ethiopians in diaspora. We plead with all Ethiopians in diaspora or in Ethiopia who knowingly or unknowingly cooperate in this fiasco festival as sports competitors, singers, dancers, musicians and vendors to stop and reflect on the true meaning of your cooperation. If you participate in the AESAONE fiasco it means you don’t care about the plight of millions of your countrymen who are suffering under the aprthaid rule of Woyane as long as you get money out of the event. Before it is too late to reverse your mistakes we like to caution you not to cooperate in the fiasco sports event organized under AESAONE by Alamudi and Woyane servants. We also call upon all freedom loving Ethiopians to boycott businesses and artists that ignore this call and participate in AESAONE fiasco in Washington D.C.
Joint Task Force
sebawinet@gmail.com

Going to Ethiopia? If you use Skype, you could be there 15 years



By Salvador Rodriguez
(Los Angeles Times) – If you’re heading to Ethiopia sometime soon, I’d like to offer you one small but crucial bit of advice: Don’t get on Skype.
The Ethiopian government last month passed a law making it a crime for people to utilize audio or video communication using Voice-over-Internet-Protocol (VoIP) services, which include Google Voice, Skype and essentially any other video chat service available.
So what’s the punishment? Well, the maximum penalty for breaking the law is 15 years in prison. That’s right — a decade and a half.
But the law isn’t that surprising when you put it in context.
Ethiopia has a track record for censoring the communication activities of its journalists and citizens. And Skype is a more difficult form of communication to intercept than regular phone calls, according to the BBC.

Sunday, June 17th, 2012 | Posted by zehabesha Is Meles Zenawi Smart?


 

by Aklog Demissie (aklogdem@gmail.com)
 
After coming to the forefront of TPLF/EPRDF at the later stage of their rebellious movement, Meles Zenawi has transformed into a cult hero for some and a brutal authoritarian for others. I have met a few people who are not a supporter of the EPRDF regime but only a supporter of Mr. Zenawi. Most of his fervent supporters and even some of his opponents laud Mr. Zenawi as an eloquent speaker, an intellectual whose all rounded knowledge on issues such as politics, economics and history is credit worthy and a leader who stands out among his African peers. In this piece, I will cover different facts that presented Meles Zenawi as a smart leader.
After a huge ideological shift of him and his party from a communist to a capitalist movement during their jungle years, Meles used to get frequent supports from the Western governments. Even during his rebellious time he used to have direct contact with United States President Jimmy Carter and show the progress of his army on the marxist Derg regime [1]. It is evident that such a stretched connection even at his infant days doesn’t come without a strong western support to his leadership of the party. He was also labeled a new generation of African leaders by President Bill Clinton together with his partner-in-rebel Issayas Afewerki. But I dont think just because someone is a leader that he is automatically smart and intelligent.