"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 19 April 2012


ታሪክን የኋሊት ‹‹ለትግራይ ተወላጆች የቀረበ ጥሪ››


(አንድ አድርገን ሚያዚያ 11 ፤ 2004 ዓ.ም) ፡-  ቀኑ ህዳር 6 1985 ዓ.ም ነበር ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሰሜን አቅጣጫ በምትገኝው በመንበረ መንግስት ቁስቋም ቤተክርስትያን ብዙ ህዝበ ክርስትያን ተሰብስቧል ፡፡ ምክንያቱ በዓለ ቁስቋምንና የጾመ ጽጌን ፍቺ በዓል ለማክበር ነበረ ፡፡ የዕለቱም አስተማሪ አለቃ አያሌው ታምሩ ነበሩ፡፡ አለቃ ‹‹በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን›› ብለው ጀመሩ፡፡ በትምህርታቸውም ስለ እመቤታችን ስደት ፤ ስለ ቁስቋም ታሪክ ፤ ወደ እየሩሳሌም ስለ መመለሷ ፤ ከእመቤታችን 300 ዓመት በኋላ በግብጽ ስለተሰራው የመታሰቢያ ቤተክርስትያን ፤ በዚህ በዓል ምክንያት ኢትዮጵያውያን ነገስታትና ንግስታት ስላደረጓቸው መንፈሳዊ ተሳትፎዎች ፤ ስመ ጥሩዋ ኢትዮጵያዊት ንግስት እቴጌ ምትዋብ በጎንደር ስላሰሯት የደብረ ቁስቋም ቤተክርስትያን  ፤ ስለ ጾመ ጽጌ ፤ ስለ ማህሌተ ጽጌ በዝርዝር አስተማሩ፡፡ ከዚያም በመቀጠል ፤ በእመቤታችን በቅድስት ማርያምና በልጇ ስደት በረከትን ካገኙ የኢትዮጵያ አውራጃዎች አንዱ የሆነው ምድረ ትግራይ ከሌሎች ቅዱሳን የኢትዮጵያ መካናት ጋር የተጣመረ የታሪክ ተዛምዶ ያለው ከመሆኑ ባሻገር ከታቦተ ጽዮን ጀምሮ ለኢትዮጵያ ለተሰጡ ልዩ ልዩ ስጋዊ እና መንፈሳዊ በረከቶች ምንጭና ቦይ ሆኖ የኖረ ነው ፡፡ ዋልድባ ገዳምም ይህን መንፈሳዊ በረከት ከሚገኝባቸው ቦታዎች አንዱ ነው ፤  በአሁኑ ወቅት ህዝቡ የተሰጠውን  ስጋዊ ስልጣን አገሪቱንና ቤተክርስትያንን ከውድቀት ለማንሳት ሊሰራበት ይገባል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ህዝብና እግዚአብሔርን የሚያሳዝን ስራ ቢሰራ ግን ትዝብትና የታሪክ ተወቃሽነትን ያተርፋል ፤ ያለው ሰፊት ትምህርት ሰጥተዋል ፡፡(የአለቃ አያሌው ታምሩ የመንፈቅ መታሰቢያ ገጽ 26)

Tuesday 17 April 2012


የቴዲ አፍሮ “ጥቁር ሰው”

እና ጥቂት የተዛቡ የታሪክ እውነቶች                                                                                                                              (ዴቪድ ካርል)                                                                                                                                             ይህንን አጭር የታሪክ ማስታወሻ ለመጻፍ ምክንያት የሆነን፤

“ጥቁር ሰው” የተሰኘው አዲሱ የቴዲ አፍሮ ዘፈን ነው። በዚህ ዘፈን ውስጥ
በተለይም አጼ ምኒልክን የጥቁር ሰዎች ንጉሥ አድርጎ፤ በዙፋናቸው ላይ
ዙፋን ጨምሮ… አግንኖ እና አጉልቶ ስላሳየን፤ አልበሙንም ለአጼ ምኒልክ፣
ለእቴጌ ጣይቱ እና ታሪካቸው ላልተነገረላቸው ጀግኖች በማድረጉ… ለቴዲ
አፍሮ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው።
““ከኢትዮጵያ ሞት በፊት እኔን ያስቀድመኝ” በሚል የኦሮምኛ ስንኝ
የተዋበው ይህ የ”ጥቁር ሰው” ዘፈን ፤ በሙሾ እና በጀግና ሆታ የተቃኘ
ነው። በሙሾው እነዚያ ለአገራቸው የወደቁ ኢትዮጵያዊያንን እንድናስብ፣
በሆታው ደግሞ የጀግንነት ዜማ እንድናቀነቅን ያደርገናል። ይሄ እንዳለ ሆኖ
በዚህ ስራ ውስጥ የተከሰቱ ስህተቶችን በመቃኘት፤ ስራው ለወደፊት
በመድረክ ሲቀርብ ወይም በዲቪዲ ሲሰራ በሲዲው ላይ የታየው ስህተት
እንዳይደገም  እርምት እንዲደረግበት ነው… የዚህ ማስታወሻ ዋና አላማ።
በዚህ ማስታወሻችን ላይ ዋና ዋናዎቹን ስህተቶች እንግለጽ።
ዋናዎቹ በቴዲ አፍሮ ውስጥ የተከሰቱት ስህተቶች የሚያጠነጥኑት
በደጃዝማች ባልቻ እና ፊታውራሪ ሃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ ዙሪያ ነው።
ሁለቱም ጀግኖች በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ሚና በመጫወታቸው፤
በ’ያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ ልዩ ስፍራ አላቸው። ነገር ግን ምንም
ያህል ብንወዳቸው የሌላውን ታሪክ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ መስጠት
የለብንም። ቴዲ አፍሮም አውቆት ሳይሆን ባላወቀው መንገድ ይመስለናል
ስህተቱን የሰራው። እንዲህ ነው ነገሩ
የቴዲ አፍሮ የቀለበት ስነስርአት እና የዘመኑ የዘረኝነት ጣጣ                                                                                   በሳለፈነው ሳምንት  እሁድ  የቀለበት ስነርአቱ ያደረገው ወጣቱን ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁንን አስመልክቶ

በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ  እስከዛሬ ድረስ ማለዳ ተነስቶ እንደማያውቅ እና ከቀለበት ሰነ ስርአቱ ጀምሮ መነሳት እንደሚጀምር እና የማህበራው ኑሮውን በሰፊው እንደሚጀምር ገልጾአል ሆኖም ግን ከህብረተሰቡ የቀረቡ አንዳንድ ትችቶች የቀረቡ ሲሆን በአሁን ሰአት በከፍተኛ ደረጃ ተቀባይነት ያለውን እውቅናውን ለመግፈፍ የሚያደርጉት ጥረት እንደሆነ የተስተዋለ ስለመሆኑ ተገንዘበናል ::ይሀውም ባለፉት ሃያ አመታት ማንኛውም ሰው ዘሩን ሳይጠየቅ ጋብቻ ይፈጸም የነበረው የኢትዮጵያዊነት ባህርይ ዛሬ ተበርዞ እና ተከልሶ  ይህ ከየትኛው ዘር የመጣ ነው እየተባለ የሚዘባበቱበት ጊዜ ላይ እንደንደርስ የገዢው መንግስት ትልቅ ተጽእኖ እና  የአስተዳድራዊ አሉታዊ እና አወንታዊ ባህርያቶች እንደሆኑ ያመላክታሉ ።ይህም ሆኖ ማንኛውም ሰው አመጣጡን ሳይሆን ለትዳር  ተስማሚነቱን እና ፍቅር በውስጡ ሰርጾ ሃያልነቱን ሲያስመሰክረው የወደፊት የህይወት ፍሬውን ለማግኘት ሲባል ይደረግ የነበረው የጋብቻ ስነ ስርአት ዛሬ ግን ዘር ተለይቶ ማንነት ተጠንቶ እና ምን አለው ተብሎ የሚገባበት አለም መፈጠሩን አንዳንድ ግለሰቦች የጠቆሙ ሲሆን  
 ለእረጂም ዘመናት የሴት ጓደኛውን ለመግለጽ ተቸግሮ የነበረው እና ባለማወቅ ብዙ አይነት የስም ማጥፋት ዘመቻ የተካሄደበት ቴዎድሮስ ካሳሁን (አፍሮ)  ዛሬ ደግሞ ለምን ትግሬ አገባ በሚል የህብረተሰብ አስተያየት እና እሰጣ ገባ ከፍተኛውን የወሬ መናፈስ በሰሜን አሜሪካም ሆነ በኢትዮጵያ እየተዛመተ መምጣቱ የግለሰቦችን አለመብሰል እና ዘመን አመጣሽ የዘር ልዩነት በወያኔው መንግስት መፈጠሩ እንዲያባብሰው እና ህዝቡን በቁርሾ እንዲኖር ያደረገው መሆኑ ሲታወቅ በሌላም በኩል ደግሞ የገዢው መንግስት ቴዲ ካሳሁን (አፍሮ )ከህዝብ እይታ ርቆ እንዲወጣ  የሚያደርጉት ቴክኒካዊ ስልት እንደሆነ እና ትዳሩንም ከጅምሩ ለማፍረስ እንዲሁም ህዝብ በዘር ምክንያት ጥላቻውን እንዲያተርፍ የሚያደርገው የገዥው መንግስት ወስጣዊ ደባ ወይንም ሴራ ነው ሲሉ አንዳንድ ሰዎች ገልጸዋል

ለኢትዮጵያዊ ወገኑ ማነው?

            ለኢትዮጵያዊ ወገኑ ማነው?                                                                                                             በተለይ ጥቂት በማይባሉ የአፍሪካ አገሮችና በመካከለኛው ምስራቅ ባጠቃላይ ደግሞ በዓለም ደረጃ የኢትዮጵያዊ ማንነቱ በእንግዳ ተቀባይነቱ እና በጀግንነቱ ሲለካ እንደኖረ አሌ የማይባል ሀቅ ነው። በሃይማኖት መጽሐፍትና ሌሎች ቀደምት ድርሳናት በጥልቀት ሲወሳለት የኖረው እንግዳ አስተናጋጅነቱ እና ጥሩ ጉርብትናው ዛሬ እንዳልነበር ሆኖ ለመስማት በሚዘገንን ርሃብ፣ ስደትና የነጻነት እጦት ሲተካ፤ ኢትዮጵያዊ በየሄደበት ከልክ በላይ ሲናቅና ሲገፋ፤ ከሰው በታች ተደርጎ ጠቆጥሮ አንገቱን ቀና ለማድረግ እንኳ የመንፈስ ጥንካሬ አጥቶ ቁልቁል ሲሽቀነጠር አይዞህ ብሎ ከጎኑ የቆመ ማነው?