"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 31 October 2014

የወላዲተ አምላክ ድንቅ ተአምር (አንድ አድርገን ፤ ህዳር 21 2004 ዓ.ም)

የወላዲተ አምላክ ድንቅ ተአም

      )፡- ዛሬ ፃድቃኔ ማርያም ሄጄ በአይኔ ያየሁትን ተአምር ልፅፍላችሁ ወደድኩኝ፡፡ ቀኑ ቅዳሜ ነው ፤ ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ ወደ ፃድቃኔ ለመሄድ የሚነሱበት ቀን ስለሆነ መጀመሪያ የሚወጣው አውቶቡስ እንዳያመልጠን ከባለቤቴ ጋር በጠዋት ነበር አውቶቡስ ተራ የደረስነው ፤ ነገር ግን ሰው እዛ ያደረ ይመስል 12፡00 ላይ አውቶቡሱ ሞልቶ መንቀሳቀስ ጀምሮ ነበር፡፡ ባለቤቴም ‹‹አይ በዚህም ሰዓት ደርሰን አመለጠን ይገርማል ተወው ባክህ እመቤቴ እንደፈቀደች››አለችኝና ሁለተኛው አውቶቡስ ላይ ገባን፡፡ ይህኛው ደግሞ ቀጥታ ዘላቂ ሰው ስላጣ የመንገድ ሰዎችንም በመጫን ነበር የሞላው፡፡ ጉዞ ወደ ፃድቃኔ ማርያም ፤ ውዳሴዋን ደግመን ጉዞ ጀመርን፡፡ መኪናው ሲያወርድ ፤ ሲጭን 9፡00 አካባቢ  ደብረ ምጥማቅ ደረስን ፤ እዚህ እንውረድና በአቋራጭ እንሂድ ተባብለን ሰላ ድንጋይ ሳንደርስ ወረድን ፡፡ እቃችንን ለአንድ የሀገሬው ሰው አሸክመን አቋራጩን ተያያዝነው ፡፡ ልጁ እንዲህ አለን ‹‹ ዛሬ ግን ማደሪያ የምታገኙ አይመስለኝም በጣም ብዙ ሰው ነው የመጣው አለን›› :: ‹‹ችግር የለውም ውጪ አንጥፈን እናርፋለን ለመተኛት መች መጣን››አልነው፡፡




ደጇን ስንረግጥ ልጁ ያለው አልቀረ የወንዶች ማረፊያ ሁለቱም አዳራሽ ከአፍ እስከ ገደቡ ሞልቷል ፤ በረንዳውን ላይ ብናይ የበረንዳው ይብሳል ፡፡ የኔን ማረፊያ ውጭ አነንጠፍንና የእሷን ለማየት ወደ ሴቶች ማረፊያ እያቀናን ሳለ ፤ አንዲት መንፈስ ያደረባት ሴት ፤ እጇም እግሯም በሰንሰለት ታስራ እንዲ እያለች የእመቤታችንን ማዳን ትመሰክራለች ‹‹ ዛሬ ደግሞ ኪዳነምህረት ድንቅ ነገር ሰርታለች ሂዱነና እዩ›› እያለች ለሰዎች ስትናገር እንደ አጋጣሚ እኔም ሰማሁ፡፡ እሷ የጠቆመችን ቦታ ላይ ስንሄድ አንዲት የ12 ዓመት ህፃን ልጅ እና እህትየዋ አንድ ላይ ቆመው ተመለከትን ፡፡ ጠጋ ብለን ምን ተደርጎላቸው ነው ስል ስጠይቅ ‹‹ የዚች ህፃን አይኗ በራላት›› ሲሉ ነገሩን፡፡ ለኔ የተደረገልኝን ያህል ደነገጥኩኝ፤ በጣምም ደስ አኘኝ፡፡ እህትየዋ የምትይዘውን የምትጨብጠውን ነገር አጥታ ነበር ፡፡ ታናሽ እህቷ የተደረገላትን ነገር እያየች ከአእምሮዋ በላይ ስለሆነ እና ደስታው ፈንቅሏት ታለቅሳለች  ፤ እኛም ገርሞን ማደሪያችንን ትተን ልጅቷ ጋር ረዥም ደቂቃዎች ስለሁኔታ ለመስማት እዛው አረፍ አልን ፡፡ እህትየዋም ሰዎች ጥያቄዎችን ሲጠይቋት እንዲህ አለች ፡-

Tuesday 2 September 2014

የአረብ ሃገሩ ክፉ ስደት – እንደ እቃ እንጣላለን ፣ መደጋገፉ ጠፋ! (ነቢዩ ሲራክ)

 nbyuገና ረፋዱ ላይ ጸሃዩ ናላን ያዞራል… የቢሮ የቤት ማቀዝቀዣዎች እንኳ ሙቀቱን ተቋቁመው የማብረድ ስራቸውን እንዳይከውኑ የሳውዲ ጅዳ በጋ ሃሩር ጸሃይ ፈተና ሆኖባቸዋል ! … በዚህ የቀለጠ የበርሃ ሃሩር ጤነኛ መቋቋም ያልቻለው  ሙቀት በአንዲት ሰውነቷ የደቀቀ እህት ይወርድባታል … ቦታውም ከጅዳ ቆንስል ግቢ የቅርብ ርቀት በሚገኝ የአንድ አረብ ግቢ በር ላይ ነው  …. ስለዛሬው የማለዳ አሳዛኝ አጋጣሚ ላጫውታችሁ…  ! ያሻችሁ ተከተሉኝ  !
የኩባንያ ስራየን በመከዎን ላይ እንዳለሁ እግረ መንገዴን ቀዝቃዛ ውሃና ማኪያቶዋን ለመነቃቂያ ፉት ልበል ለማለት በጅዳ ቆንስል ቅጽር ግቢ ውስጥ ወደሚገኘው የኮሚኒቲ ካፍቴርያ ብቅ ብየ ያችኑ ማኪያቶ አዘዝኩ…. ማኪያቶየን እየቀማመስኩ እንደኔው የካፍቴሪያ ታዋቂ ደንበኞች ከሆኑ ወዳጆቸ ጋር ስንጨዋወት አንድ ሌላው ወዳጃችን ግዙፍ ሰውነቱ በላብ ተጠምቆ ገባ ! … ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ በቆመበት ”  አንዲት እህት በር ላይ ወድቃለች ፣ ማን ይሆን የሚረዳኝ? ” እያለ እኛን ትቶ ሌላ ሰው በአይኑ መፈለግ ያዘ ፣ ብዙም ሳይቆይ ወጥቶ ሄደ ። የካፍቴሪያው ደንበኞች እኛ ከደቂቃዎች በፊት አድምቀን ስንረባረብበት የነበረውን ያህል ወሬ  ወንድማችን ስለሰጠን መረጃ ግድ የሰጠን አንመስልም ለማለት ደረቅ ቢልም ችግሩን ለምደነው ጉዳያችን ብለን ማንሳት ሳይገደን ቀረና ዝም ብለን ተፋጠጥን …

Monday 1 September 2014

ቴዲ አፍሮ – በሁለት ጽንፎች

ኢትዮጵያ ውስጥ ፈጽሞ ሊተቹ የማይችሉ ሶስት ግዝፍ ነገሮች አሉ። እነዚህም
1ኛ – ሃይማኖት
2ኛ – መንግስት
3ኛ – ቴዲ አፍሮ
ናቸው።
ከእንግዲህ ቴዲ አፍሮ ዘፋኝ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ መቆራቆዣ ተቋም ሆኗል። ይህን አስመልክቶ ወዳጃችን Girmabbaacabsaa Guutamaa እንዲህ ይላል….
“ቴውድሮስ ካሳሁን aka ቴዲ ኣፍሮ ዘፋኝ ብቻ ኣይደለም። በሃገሪቱ ውስጥ ካሉት ይልቁንም ባብዛኛው ሊታረቁ የማይችሉ (divergent) ማህበረ-ፖለቲካዊ እሳቤዎችን በሚያራምዱ ኤሊቶች ከሚመሩት የተለያዩ ቡድኖች መካከል የኣንዱ ግሩፕ political ideologue ነው ቴዲ።”
ይህ ብያኔ (Definition) የተለጠጠ ቢሆንም ውሸት ግን አይደለም። ቴዲ በሁለት ጽንፍ የቆሙ የፖለቲካ ወገኖች መቆራቆዣ አእማድ (Pillar) ሆኗል።
የቴዲን ዘፈኖች መተቸት ችግር ያስከትላል። የቴዲ ስራ ላይ ሂስ ማቅረብ “ሃራም” ሆኗል። ለምን ቢባል — ቴዲ ለደጋፊዎቹ የማይሳሳት እና ሁሉን አወቅ ነው። የቴዲን ስራዎች መንካት ያሰድባል፤ ያስዘልፋል፤ ባስ ሲል ደግሞ የኢትዮጵያን አንድነት እና “ኢትዮጵያዊነትን” እንደመካድ ያስቆጥራል። የቴዲን አዲሱ ነጠላ ዜማ የተቹ ሰዎች ብዙ ስድብ ሲቀምሱ ታዝቤያለሁ።
በተመሳሳይም የቴዲን ዘፈኖች ማድነቅ ችግር ያስከትላል። ቴዲ በነቃፊዎቹ ዘንድ ሁሌ ስህተት ነው። ስለዚህ የቴዲን ስራዎች ማድነቅ ብሄር ብሄረሰቦችን እንደ መጨቆን፤ የቀድሞ ስርዓትን እንደመናፈቅ እና ገፋ ሲል ደግሞ መንግስትን በ17 መርፌ እንደ መውጋት ተደርጎ ይቆጠራል። “ጥቁር ሰው” የወጣ ጊዜ የኦሮሞ ልሂቃን እና የመንግስት ደጋፊዎች ለምን የአጼ ምኒልክ ስም ተጠራ በሚል የስድብ መዓት ሲያወርዱ አስተውያለሁ።
የሆነው ሆኖ ቴዲ ከእንግዲህ ተራ ዘፋኝ ብቻ አይደለም።
በሰባ ደረጃ
“በሰባ ደረጃ የተባለው ነጠላ ዜማ ቴዲን የሚመጥን ነው ወይስ አይደለም?” የሚለው ክርክር መቋጫ አልባ ይመስላል። ይሄን ዘፈን ሌላ ዘፋኝ ቢጫወተው እንዲህ አይነት አቧራ ያስነሳ ነበር? መልሱ ግልጽ ነው። በእርግጥ ሙዚቃ የስሜት ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን በእውቀት የሚተች ጥበብም ነው።
— ለምሳሌ
አስቴር አወቀ በአንዱ ዘፍኗ ውስጥ እንዲህ የሚል ስንኝ አላት።
አዳራሽ
በብዛት ይገኛል
ሽንኩርት እና ፍራሽ
ይሄ ግጥም በሁለት መልኩ እጅግ ደካማ ነው።
1ኛ አዳራሽ ውስጥ ሽንኩርት እና ፍራሽ በጭራሽ አይሸጥም።
2ኛ ከአጠቃላይ የዘፈኑ አውድ (Context) አንጻር ይሄ ስንኝ ምንም ግንኙነት የለውም።
ይሄ አዝማሪዎች የሚታወቁበት የግጥም አይነት ሲሆን የላይኛው እና የታችኛው ሃሳብ ፍጹም አይገጥምም። በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የዘፈን ግጥም ከትችት አያመልጥም።
የቴዲ አፍሮ “በሰባ ደረጃ” ሃሳቡ በጣም ግሩም ነው። ሆኖም ግን ግጥሙ ውስጥ ልክ በድሮ ጊዜ አዝማሪዎች እንደሚያደርጉት የላይኛውና የታችኛው ስታንዛ የማይገናኝ እና ከአውዱ ውጪ የሆነ ግጥሞች መኖራቸው ዘፈኑን እንዲተች ምክኒያት ሆኗል። ይሄን ሃሳብ ለማጠናከር ብዙዎች የሚከተለውን አንጓ ከግጥሙ ውስጥ ይመዛሉ።
“አምጧት ከጎኔ ትቀመጥ
እንጀራ አይቀርብም ካለ ወጥ”
ጋዜጠኛና ገጣሚ Demeke Kebede ይሄ አይነት ግጥም ለቴዲ አፍሮ አይመጥንም በማለት ይከራከራል። ከዚህም በተጨማሪ “አርምዴ ሜሪ” ብሎ ስሟን ማዟዟሩ ተገቢ እንዳልሆነ ያሰምርበታል።
ታዋቂው ገጣሚና የወግ ጸሃፊ Bewketu Seyoum ግን በዚህ ሃሳብ አይስማማም። እንዲያውም ቴዲ አፍሮ ከዳግማዊ አጼ ቴውድሮስ ቀጥሎ የተነሳ “ሳልሳዊ ቴዎድሮስ” ነው በማለት አሞካሽቶት ሲያበቃ “አርምዴ መሪ ብሎ መጥራት የገጣሚነት ነጻነቱ ይፈቅድለታል” በማለት በተለየ መንገድ ተንትኖታል።
እርግጥ በእወቀቱ እንዳለው ቴዲ የባህል ዘፈን ለመዝፈን ግዴታ በእንኮዬ መስክ እና በኳሊ በር ወይም በጃን ተከል ዋርካ ስር እያለ መዝፈን አይጠበቅበትም። ሆኖም ግን “አርምዴ ሜሪ” ተብሎ ለትውልድ ሲተላለፍ የሚያመጣውን ጉዳት እንዴት እንደተመለከተው አልገለጸም። እስኪ አስቡት አስቴር አወቀ በአንድ ዘፈን ውስጥ “አወቀ አስቴር” ተብላ ብትጠቀስ የወደፊቱ ትውልድ አወቀ የሚባል ወንድ ዘፋኝ ነበር ብሎ ሊተረጉመው ቢችልስ? ቴዲ በጥቁር ሰው ውስጥ “ባልቻ አባቱ ነፍሶ” ያልኩት አውቄ ነው ማለቱ ብዙዎችን አሳዝኗል። የሚስራ ሰው መሳሳቱ የሚጠበቅ ስለሆነ ማመኑ አይከፋም ነበር።
የሜሪን ስም ጉዳይ ብንቀበለው እንኳን እነዚህን ግን ማለፍ አይቻልም። ሴይቼንቶ የሚለውን አጠራር ቴዲ “ሴሼንቶ” ብሎ ገድፎታል። ሴሼንቶ የሚባል መኪና አልነበረም። መውዜር የተባለውን ጠመንጃም መውዜሬ እንደማለት “መውዘሬ” ሲል አንሻፎታል።
በሰባ ደረጃ እነዚህ አይነት ህጸጾች ቢኖሩበትም በርካታ የጠፉ ቃላትን በማምጣት አዲሱን ትውልድ ታሪክ በማስተማሩ ቴዲያችን ሊመሰገን ይገባዋል።
መግቢያው ላይ ያለው የክራር ድምጽ ከሜሪ አርምዴ አገራረፍ ጋር የሚመሳል መሆኑ ጥሩ ቢሆንም በኪቦርድ ተከትፎ መሰራቱ ጥራቱን ደካማ አድርጎታል። የሙዚቃው ምት 6 በ 8 (በተለምዶ ችክችካ የሚባለው) ሲሆን ማስጨፈሪያ አይነት ስለሆነ ቴዲ ከፊታችን ላለበት የአሜሪካ ኮንሰርት ጥሩ መሳቢያ ይሆንለታል።
ቅኔ የመፈለግ በሽታ
በሰባ ደረጃ ቅኔ አለው በማለት በርካታ ሰዎች የተለያየ ትርጉም ሰጥተውታል።
– ግርማ “ቴዲ ኣፍሮና እሱ የሚወክለው ኤሊት የፒያሳውን ሰባ ደረጃ እንደመውጣት ኣድካሚ ነው ያለውን ኢትዮጵያን የማዳን ሃላፊነት በፍቃደኝነት ወስደዋል” በማለት ተንትኖታል።
– ሌላኛው አስተያየት ሰጪ “ቴዲ ለፍቅር እንጂ ለብር እንደማይንበረከክ “ብርም አይገዛሽ – ኬረዳሽ” በማለት ኮንሰርቱ ላሰረዙበት ሰዎች ነገራቸው” ብሏል።
“አቅፎ ገልዋን አልጠግብ ያለው
ማነው ካላችሁ ማነው ማነው?”
– “ያለው እኮ ለወያኔዎች ልክ ልካቸው ሲነግራቸው ነው” ብሎ የጻፈም አለ።
ጋዜጠኛ ደመቀ ግን “ሰባ ደረጃን ደግሜ ደጋግሜ ብሰማውም አንዳችም የፖለቲካ ሰበዝ ተሰብዞበት አላገኘሁትም” በማለት ዘፈኑ የፍቅር እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተከራክሯል።
እኔም ከደመቀ ጋር በብዙ መልኩ እስማማለሁ። ለምን ከተባለ አንዲት ምሳሌ ሰጥቼ ልሰናበት።
ሶስቱ አልማዞች
በደርግ መጀመሪያ ዘመን ህዝቡ ዘፈኖችን እና ስነጽሁፍን ሁሉ ቅኔ ማላበስ ፋሽን አድርጎት ነበር። አፈና ሲኖር እንዲህ አይነት የህዝብ አስተያየት (Public opinion) የተለመደ ነው። የሆነው ሆነ ጥላሁን ገሰሰ ሶስቱ አልማዞች የሚል አንድ ሸክላ አሳተመ። የዘፈኑ አዝማች እንዲህ የሚል ነው
አልማዝን አይቼ አልማዝን ባያት
ሶስተኛዋ አልማዝ ብትመጣ ድንገት
ሁለቱን አልማዞች ስላስረሳችኝ
ምርጫዬ ከምርጫ ተበላሸብኝ
ይሄ ዘፈን የተዘፈነው በወቅቱ የደርጉ ሊቀመናብርት ለሆኑት ለብ/ጄነራል ተፈሪ በንቲ፤ ለሻለቃ መንግስቱ ኃይለማሪያም እና ለሻለቃ አጥናፉ አባተ ነው ተብሎ ተወራ። ልክ ልካቸውን ነገራቸው እያለ ሕዝቡ ወሬውን አስተጋባው። ይሄ ወሬ እነ መንጌ ጆሮ ሲደርስ ወዲያው ሸክላው ታገደ። ደራሲው ተስፋዬ ለማ በቁጥጥር ስር ዋለ። ጥሌም ሁለት ጥፊ ቀምሶ ሁለት ቀን ታስረ።
ደራሲ ተስፋዬ ለማ ከረጅም ጊዜ እስር በኋላ ሲፈታ ወደ ውጪ አገር ተሰደደ። በቅርቡ ቃለ መጠይቅ ሲደረግለት እንዴት እንደጻፈው ተረከ። እንዲህ በማለት….
አንድ ቀን ከሰዓት ላይ ማኪያቶ ለመጠጣት ጆሊ ባር ገባሁ። የታዘዘችን አሻሻጭ (ባር ሌዲ) በጣም ውብ ነበረች። ታዛኝ ስትሄድ እንዴት ቆንጆ ነች … ይህቺስ አልማዝ ነች ብዬ ከጀልኳት። ማኪያቶውን ይዛ የመጣችው ግን ሌላ አስተናጋጅ ነበረች። የሚገርመው ይህቺኛዋም በጣም ውብ ሆና ታየችኝ። መጨረሻ ሂሳብ ስጠይቅ ደግሞ ሌላ ሞንዳላ አልማዝ ስትመጣ ወዲያው ከሁለቱ የበለጠ ውብ ሆና ታየችኝ። ወዲያው እስክሪብቶ አውጥቼ ማስታወሻዬ ላይ “ሶስቱ አልማዞች” ብዬ ጻፍኩ። ግጥሙን እዛው ቁጭ ብዬ ጨርሼው ጥላሁን ዘፈነው።
አይገርምም?
**ማሳሰቢያ
——————
የስድብ (አስተያየት) ፈጽሞ የተከለከለ ነው። ቴዲ እራሱ እንኳን በፍቅር እንጂ መች በስድብ ያምናል?

Friday 8 August 2014

..የፍልሰታ ስጦታ!...እውነተኛ ታሪክ

..(...የፍልሰትዋ ተአምር...)

ከቅርብ ዓመታት በፊት ነው! በግብፅ ይኖር የነበረው ወጣት ምንም እንኳን ገና በወጣትነቱ በትምህርት፣ ሃብትና ትዳር "የተሳካለት ሰው" የሚባል ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በፊት ግን ይመካበት የነበረውን ትዳሩን ጥያቄ ውስጥ ገብቶበታል:: ባላወቀው ምክንያት የሚወዳት ባለቤቱ ከወገብ በታች ፓራላያዝ ትሆናለች:: እርስዋን ለማሳከም ያልሄደበት ሆስፒታል ባይኖርም የሚሄድበት ሆስፒታል እንደሌለ ግን ተነግሮታል:: "የያዛት በሽታ አይድንም!" የሚል መራራ ሐዘንን ሰምትዋል! ብዙ ያሰበለት የልቡ ፍቅር ሲጠወልግ፣ የወደፊት ሕልሙ ሲጨልም፣ የልጅ አምሮቱም እንዲሁ ላይመጣ ሲቀር አስቀድሞ አውቋል! ባለቤቱ አልጋዋ ላይ ትበላለች አልጋዋ ላይ ትፀዳዳለች! ለጥቂት ጊዜ እዛው አልጋዋ ላይ ሳምንታትንና ወራትን ስታሳልፍ ከራሱ ጋር እየታገለ በትዕግስት ቢያስታምማትም ከዚህ በላይ መቆየት ግን በአካል ሲኦል የመግባት ያህል ሁኖ ተሰማው:: ስለዚህ በፍቺ ከርስዋ ጋር መለያየትን መረጠ:: ነገር ግን ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት አስቀድሞ የንስሃ አባቱን ማማከር እንዳለበት አመነና ወደሳቸው ሄዶ ያሰበውን ይነግራቸዋል! እሳቸው ግን በፍፁም እንደማይሆን፣ ጌታ ያጣመረውን እርሱ መፍታት እንደማይገባ ከመጽሐፍ ቅዱስ እየጠቀሱ ያስረዱታል:: ከዚያም ሁለቱም በጸሎት እንዲተጉና ወደ እመቤታችን እንዲያመለክቱ ተነጋግረው ይለያይሉ:: የንስሃ አባቱም የወጣቱንና የባለቤቱን የክርስትና ስማቸውን ፅፈው በመቅደሱ መንበር ላይ አስቀምጠው ለ 3 ቀና ያህል በፅኑ ፆምና ጸሎት እየተጉ ቆዩ::

Tuesday 3 June 2014

የእናቶች ቀን እና ቅድስት ድንግል ማርያም ፀሐፊ፡- ፍቅር ለይኩን፡፡ በእናቶች ቀን የመስቀል ላይ የፍቅር ስጦታ የሆነች እናታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ልንዘክራት ይገባናል!!!



ሰማይ ሰማያት፣ ምድርና ሞላዋ፣ አለቆች፣ ሥልጣናት፣ መናብርት፣ አጋእዝት፣ መኳንት፣ የሰማይ ሠራዊት መላእክት፡- ምሕረትንና ይቅርታን ለሰው ልጆች ሁሉ ባወጀው በእግዚአብሔር ቅዱስና ሕያው ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅ የፍቅር ትእይንት እጅግ በተደመሙበትና በተመሰጡበት፣ በዚህ ሕያው ፍቅር ምድርና ሰማይ በደመቁበትና ባሸበረቁበት፣ የፍቅር ዜማ፣ የፍቅር ልዩ ቅኔ ነፍስን በሚመስጥ ቅላጼ፣ በውብ ስርቅርቅታ፣ በታላቅ ድምጽ ከአድማስ አድማስ፣ በተራሮች፣ በባሕሮችና በውቅያኖሶች ዳርቻ ሁሉ በተሰማበት፣ ጸሐይና ከዋክብት ለዚህ ፍቅር በልባቸው ጉልበት በፍቅር እግር ስር በቀራኒዮ በተንበረከኩበት፣ ጨረቃም በፍቅር ትሕትና፣ በፍቅር ቸርነትና ትእግስት ተመስጣ ደም በለበሰችበት፣ በደም በተነከረችበት፣ ምድርና ሞላዋ፣ ሰማይ ሰማያት በፍቅር መሳጭና ልዩ ትእይንት በደመቁበት ፍቅር እንዲህ ሲል በትሑት ድምጽ፣ በፍቅር ጩኸት ቃሉን አሰማ፡-

Saturday 10 May 2014

ለፌስቡክ ባለንጀሮቼ ብቻ የተጻፈ)


ባለፈው፣በቤተ-መንግስት መውጫ፣ በሸራተን መውረጃ መንገድ ላይ የተሰቀለ ፖስተር አየሁ፡፡‹‹ባፍሪካ የመጀመርያው የሳቅ ትምርት ቤት››ይላል፡፡የዘመኑን መንፈስ ከሚያሳዩ ተቋሞች ዋናው መሆን አለበት ብየ አሰብኩ፡፡በዘመኑ ዝም ብሎ መሳቅ ከባድ ነው፡፡እንድያውም በዘመኑ ከልቡ የሚስቅ ሰው ከተገኘ እንደ ስድስት ኪሎ አንበሳ በቅጽር ከልለን ልንጎበኘውና ልናስጎበኘው ይገብባል፡፡
በረንዳ ላይ ተቀምጠህ ምሳ ስትበላ ከወገቡ በላይ ሥጋ ከወገቡ በታች የመኪና ጎማ የለበሰ ተመጽዋች ወደ ጠረጴዛህ እግር እየተንፏቀቀ ቀርቦ ልመና ይሁን ትእዛዝ ባልለየለት ድምጽ‹‹አጉርሰኝ››ሲልህ እንዴት ትስቃለህ፡፡የቤት አከራይህ ከጓሮህ ያለውን የቀለበት መ...ንገድ ከራሳቸው ኪስ አውጥተው ያስገነቡት ይመስል‹‹አካባቢውን እድገት ግምት ውስጥ በማስገባት ተዛሬ ጀምሮ በኪራዩ ላይ አንድ ሺህ ብር ጨምሬያለሁ›› ብለው ሲያረዱህ እንዴት ትስቃለህ፡፡ኮሌጅ እንዲበጥስ የሰደድከው ታናሽ ወንድምህ ለራዛ ዘመቻ የወጣ ይመስል፤ባውቶብስ ሂዶ በወሳንሳ ሲመለስ እንዴት ትስቃለህ፡፡የሳቅ ትምርትቤት መስራች አቶ በላቸው ገብቶታል፡፡ሳቅ እንደ ሂሳብ ወይም እንደ እደ ጥበብ ውጤቶች በልምምድና በጥናት ካልሆነ በቀር በዋዛ የሚገኝ አልሆነም፡፡ይህ ትምርትቤት ወደ ፊት በቢኤና በፒኤችዲ ማስመረቅ ሲጀምር ሰዎች እንደየደረጃቸው ይስቃሉ፡፡‹‹ያ ሰውየ ፍርርርስ ሲል አየከው? ከበላቸው ግርማ ትምርትቤት ማስተርሱን ስለ ሠራ እኮ ነው›› የምንልበት ቀን ሩቅ አይመስለኝም፡፡

Tuesday 18 March 2014

አበው ይናገሩ


እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ
የምንኩስና ግብር ምን ነበር ምሥጢሩ
የክርስትና ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ
መቃብሩን ክፈቱና አበው ይመስክሩ፡፡
እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና
ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና
ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ
ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ፡፡
ነብያት በመጋዝ የተሰነጠቁት
ሐዋርያት ቁልቁል የተዘቀዘቁት
ሰማዕታት በእሳት የተለበለቡት
ቅዱሳን በገዳም ደርቀው የተገኙት
ምሥጢሩ ምን ነበር? አበው ይናገሩት፡፡

Thursday 27 February 2014

‹‹ ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል ››


ስለታክሲ ጥቅሶች ማውራታችን ካልቀረ እስቲ የታዘብካቸውንና ያነበብኳቸውንና ትንሽ ፈገግ ያደርጋሉ ያልኳቸውን ላካፍላችሁ፡፡

·    የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ·  ሠውን ማመን ተፈራርሞ ነው·  ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
·
   በቴሌቶን ሂሳብ መክፈል ክልክል ነው
·
   ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
·
   ለፀባይኛ ተሳፋሪ የፀባይ ዋንጫ እንሸላማለን
·   ለስራ ነው የወጣነው
·   በመጀመሪያ የጋለ ደምህን ተቆጣጠርና ሀሳብህን ግለፅ
·
    ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
·
   ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
· 
 ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
·   ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
·   ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
·   ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር

Tuesday 25 February 2014

ከበዕውቀቱ መጣጥፎች ውስጥ ሁለቱን ጀባ ልበላችሁ\\

ኢትዮጵያ እመ-መከራ
የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ
መውደቅማ ነበር ያባት
እንደ ያሬድ እስከ ሰባት
እንደ በላ ብላቴና ፣ የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ
የትውልዴ እጣ ፋንታ ፣ መውድቅ መውድቅ መውድቅ ብቻ…

አጤ ካሌብ የተባለ የኢትዮጵያ ንጉሥ ባንድ ወቅት በቅድመ-እስልምና የመን የሚኖሩ ክርስቲያኖች ባንድ ያይሁድ ገዥ መዳፍ ስር መማቀቃቸው አስቆጥቶት ቀይ ባሕርን ተሻግሮ ተበቅሎላቸዋል። የዛሬውን አያድርገውና ፣ እንኳን ለቤት ለጎረቤት ጥቃት የሚቆረቆር ንጉሥ ማፍራት ችለን ነበር፤ አንኳን ለቤት ለጎረቤት እርዳታ የሚበቃ ጉልበት ማካበት ችለን ነበር ። ዛሬ ግን ጊዜ ከካሌብነት ወደ ከልብነት ደረጃ አውርዶናል። (“ከልብ” በግዕዝ ውሻ ማለት ሲሆን በአማርኛ ዘይቤ አንድ ሰው ያለ ካሳ ያለ ጉማ ደሙ ፈሶ ሲቀር ደመ ከልብ ሆነ ይባላል)።
አቅመ-ቢስ ሕዝቦች በጉልቤ ሕዝቦች መዳፍ ስር ገብተው መከራ ማየታቸው በታሪክ ብርቅ አይደለም። እኔን የሚገርመኝ በፋንታችን መከራ ማየታችን አይደለም ፤ እኔን የሚገርመኝ ከዚህ ሁሉ መከራ በሁዋላ ከመከራ የሚታደገን የኑሮ መላ አለማፍለቃችን ነው። ከመከራ መደራረብ በሁዋላ ያፈለቅነው የስልጣኔ ፍሬ የሙሾ ግጥም ብቻ መሆኑ ያስደንቃል።
አይሁድ በሁለተኛው ያለም ጦርነት ግፍ ከደረሰባችው በሁዋላ አንሰራርትው በርትተዋል፤ እንደ ኒቼ “ጨርሶ የማያጠፋኝ ሁሉ ያበረታኛል” ብለዋል። ዛሬ በነዳጅ መስክ ላይ የበቀሉ አረሞችን (አረቦችን) ያርበደብዳሉ ። ጀርመኖች በሁለተኛው ያለም ጦርነት ማክተሚያ ላይ በጠላቶቻቸው ከስክስ ጫማ ደቀዋል። ግን በአጭር ጊዜ አንሰራርትው ሃይላችውን እንደ ንስር አድሰዋል፤ እኛስ ይሄን ማድረግ ያቅተናል? አያቅተንም። ያገራችን አስተዳዳሪዎች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ ሀያል መንግስቶች ከመከራ ዶፍ የማይታደጉን ነዳላ ጃንጥላ መሆናችውን አይተናል። የራሳችን አዳኞች ራሳችን መሆናችንን አንርሳ ፤ ጎበዝ የዳይኖሰርን ፈለግ ከመከተላችን በፊት ትንሽ መላ እንምታ::

“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው” ዑጋንዳ የጸረ ግብረሰዶማውያን ሕግ አጸደቀች!

musevini


የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ “አከራካሪ” ሲባል የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡ ግብረሰዶማውያንን “ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ” እና “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ ግብረሰዶማዊነት በምዕራቡ ዓለም አማካኝነት ወደ አፍሪካ እየተስፋፋ የመጣ ነው ብለዋል፡፡

ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ  ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡
uganda 1ሕጉን በፊርማቸው ያጸደቁት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ሲኤንኤን ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ግብረሰዶማውያን “አጸያፊ ሰዎች ናቸው፤ ምን ዓይነት ድርጊት ይፈጽሙ እንደሆነ አላውቅም ነበር፤ በቅርቡ የሰማሁት ግን በጣም አስደንጋጭ ነው፤ ጸያፍ ነው” ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሲቀጥሉም ሰዶማውያን ሲወለዱ ጀምሮ እንደዚሁ ናቸው ስለተባለ ሁኔታውን እውነት አድርገው በመውሰድ ቸል ሊሉት እንደነበር ሆኖም ግን እስካሁን ምንም ሳይንሳዊ ማስረጃ እንዳልቀረበበት ተናግረዋል፡፡
ሙሴቪኒ ሕጉን እንዲያጸድቁ ያደረጋቸውን አንዱን ምክንያት ሲጠቅሱም፤ ግብረሰዶማዊነት ከጄኔቲክስ ጋር በተያያዘ ከውልደት ጀምሮ የሚመጣ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው በማለት ይገምቱ እንደነበር ሆኖም የአገራቸው ሳይንቲስቶች ይህንን መከራከሪያ ውድቅ ማድረጋቸውን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ሕጉ በፕሬዚዳንቱ ፊርማ ከጸደቀ በኋላ ወዲያውኑ በሥራ ላይ የዋለ ሲሆን ግብረሰዶማዊ ወሲብ ሲፈጽም የተገኘ ማንኛውም ሰው እስከ ዕድሜ ይፍታህ በሚደርስ እስራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ በወንጀሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ በ14ዓመት እስር ይቀጣል፡፡ በተደጋጋሚ ወንጀሉን ሲፈጽሙ የተገኙ፣ ዕድሜያቸው ካልደረሱ ጋር እንዲሁም ከአካለ ስንኩል ወይም ከኤችአይቪ ተጠቂ ጋር ወንጀሉን የፈጸሙ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ሕጉ ያዛል፡፡
ናይጄሪያም ከአንድ ወር በፊት ተመሳሳይ ሕግ ያወጣች ሲሆን የዑጋንዳው ሕግ በረቂቅነት ከወጣ የዛሬ አራት ዓመት ጀምሮ ምዕራባውያን ከፍተኛ ተጽዕኖ በማድረግ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን፤ ከሆነም በአብዛኛው የህጉ ክፍል እንዲሸራረፍ በርካታ ሙከራዎችን፣ ማስፈራሪያዎችንና ውስወሳዎችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡no homosexual
በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል፡፡ ሌሎች አገራት ግን እንዲህ ዓይነቱ የዕርዳታ ማቋረጥ ውሳኔ ዑጋንዳውያንን የሚጎዳ በመሆኑ እርምጃው መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡
የዑጋንዳ ሕግ አውጪዎች ያረቀቁትን ሕግ በፈረሙበት ጊዜ ሙሴቪኒ እንዳሉት ምዕራባውያን በዑጋንዳ ጉዳይ በግልጽ ጣልቃ እየገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ “አፍሪካውያን በሌሎች ላይ የራሳችንን አመለካከት አንጭንም” ያሉት ሙሴቪኒ ምዕራባውያን እስካሁን ያደረጉት ጣልቃገብነት ትክክለኛ እንዳልነበረ እና ይህም ደግሞ “ማኅበራዊ ኢምፔሪያዝም” ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡ ግትርና ግዴለሽ ምዕራባዊ ድርጅቶች የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፋፋት እየጣሩ መሆናቸውንና ለዚህም ሰዶማዊነት ተግባር የኡጋንዳን ህጻናት እየደለሉ ወደ ግብረሰዶማዊነት ወንጀል እንደሚያስገቧቸው ከሰዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሰዶማውያን ደሃ ዑጋንዳውያንን ዒላማቸው በማድረግ በገንዘብ በመደለል ለግብረሰዶማዊነት እንደሚጋብዟቸውና ቀጥሎም ለግብረሰዶማዊ አዳሪነት እንደሚዳርጓቸው ሙሴቪኒ ተናግረዋል፡፡
የዑጋንዳን ውሳኔ አስመልክቶ የማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ የሆኑ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት “ኢህአዴግም ከየምዕራቡ ለሚለቃቅመው ዕርዳታ ብሎ የአገርን ባህልና ማኅበራዊ እሴት ከሚያጠፋ ይልቅ ተመሳሳይ ተግባር ሊወስድ ይገባዋል፤ የተቃወመውን ሁሉ “አሸባሪ” በማለት በጸረ አሸባሪ ህግ ስቃዩን ከሚያሳይ የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በማውጣት ይህንን በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ወረርሽኝ መላ ሊለው ይገባል” ብለዋል፡፡

Thursday 6 February 2014

በአዲስ አበባ የ“ዳይመንድ ድራማ” ተጧጡፏል!


ኔትዎርክ ያቆማል የተባለው የ“ማሾ ዳይመንድ” 4ሚ. ብር ተሸጧል
የዳይመንዱን ትክክለኛነት የሚያረጋግጡት “የውጭ ኤክስፐርቶች” ናቸው
ባለሃብቶች የሚጭበረበሩት በሚያውቋቸውና  በቅርብ ባልንጀሮቻቸው ነው
በአዲስ አበባ የሚኖሩት አቶ አየለ ጣፋ እና አቶ ጎሽሜ ሁንያንተ የልብ ጓደኛሞች ሲሆኑ ሁለቱም በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ አቶ ጎሽሜ ለበርካታ አመታት በጣሊያን ኖረው ነው ወደ አገራቸው የተመለሱት፡፡ አቶ አየለ የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ከውጭ እያስመጡ የሚሸጡ ሲሆን ልጆቻቸውም በስራቸው ያግዟቸዋል፡፡
ከጥቂት አመታት በፊት አቶ አየለ ሰሚት አካባቢ መኖሪያ ቤት ሲገዙ፣ የልብ ጓደኛቸው አቶ ጐሽሜ አለኝታነታቸውን የገለፁት የ300ሺ ብር ስጦታ በማበርከት ነበር፡፡ ትንሽ ቆይተው ታዲያ ውለታ ጠየቁ - አቶ ጐሽሜ፡፡ በእርግጥ ውለታው ከባድ አልነበረም፡፡ ዘቢደር የተባለች ዘመዳቸው አቶ አየለ ቤት፣ በቤት ሠራተኛነት እንድትቀጠር ነው የፈለጉት፡፡
አቶ አየለም፤ “አንተ ብለህ ነው?” በማለት ዘቢደርን ለሌሎች ሠራተኞቻቸው ከሚከፍሉት ደሞዝ በእጥፍ ቀጠሩላቸው፡፡ 300ሺ ብር በስጦታ ላበረከተ ለጋስ ጓደኛ ይህቺ ምን አላት! አቶ አየለ አንድ ሴራ እየተጐነጐነላቸው መሆኑን ግን አላውቁም፡፡
የአቶ ጐሽሜ ዘመድ ናት የተባለችው ዘቢደር፣በእንክብካቤ አንድም ነገር ሳይጐድልባት አቶ አየለ ቤት ለአንድ ዓመት ቆየች፡፡ ዋና ተልዕኮዋ የሚጀምረውም ከዚህ በኋላ ነው፡፡ አጐቴ የምትላቸው አቶ አጐናፍር (ዋና ስማቸው መኮንን ሃብታሙ) ከገጠር “ሊጠይቋት” ይመጣሉ፡፡ አመጣጣቸው ግን ለሌላ ነበር፡፡