"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 4 August 2012

ወያኔ የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ባዳ ሆነውብን ይዘልቃሉ



ዋለልኝ መኮንን
የወያኔው ጠቅላይ ሚንስቴር ከሞቱ/ከታመሙ ጀምሮ የህወሃትና ወይም ኢህአዴግ( ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማጭበርበር የወጣ ስም መሆኑን እንዳትዘነጉ) ምን ያህል ከአንድ ጎጥ የተውጣጣ የበሰበሰና የተበላሸ የፓርቲና የግለሰቦች ስብስብ እንደሆነ ግልዕ አድርጎልናል:: በጣም አስገራሚው ደግሞ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች/ የወያኔ ቃል አቃባይ በረከት ስምዖን የጠቅላይ ሚንስቴሩ መታመም የኢትዮጵያን ህዝብንም እናንተንም ጋዜጠኞቹን ምንም አያገባችሁም አይመለከታችሁም የግል ጉዳይ ነው በለውን እርፍ አሉት::
የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች/ የወያኔ ቃል አቃባይ በረከት ስምዖን የጠቅላይ ሚንስቴሩ መሞት፣ የሬሳ ሳጥኑ ምን አይነት ነው ፣ መታመም፣ ምን እንዳመማቸው “ካሁን በሁዋላ የሚያሳትም የሚፅፍ የሚያወራ በአሸባሪነት ሊከሰስ እንደሚችል” የሚል ያዘለ መልዖክት አስተላልፈዋል::የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የወያኔ ቃል አቃባይ በረከት ስምዖን የጠቅላይ ሚንስቴሩ መታመም የኢትዮጵያን ህዝብንም እናንተንም ጋዜጠኞቹን ምንም አያገባችሁም አይመለከታችሁም የግል ጉዳይ ነው በለውናል እዚህ ጋር በረከት ስምዖን አንድ እውነት አለው ይህም የወያኔው ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ ህዝብ የጠቅላይ ሚንስቴሩን ስልጣን አላገኙም::
ሌላው የመለስ ዜናዊ መሞት/መታመም የት እንዳለ የሚያውቁት ወያኔዎች ብቻ ናቸው ሊያውም ጥቂት አድዋዎች:: ከፍተኛ የደህዴን ፣ የኦህዴድ፣ የብአዴን ብሎም ሌሎች አጋር ድርጅቶች ብሎ ወያኔ ስም ያወጣላችው ክልሎች ባለስልጣኖች አይደለም የመለስን መሞት/መታመም ይቅርና ትላልቅ ሀገራዊ ውሳኔዎችን የሚሰሙት ልክ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በመጀመሪያ በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጭ ባሉ የህዝብና የግል ሚዲያዎች ሲሆን ከዛም በሁዋላ በወያኔ የሚዲያ ማሰራጫዎች እንደማስተባበያ ሆኖ ሲቀርብ ነው:: በዚሁ ሳልናገር የማላልፈው ከፍተኛ የደህዴን ፣ የኦህዴድ ፣ የብአዴን ብሎም ሌሎች አጋር ድርጅቶች ብሎ ወያኔ ስም ያወጣላችው ክልሎች ባለስልጣኖች የወያኔውን ጠቅላይ ሚንስቴር መሞት ፣ መታመም እና የወያኔን እርቃኑን መቅረት እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ህዝቡ የሚያደርገውን የዲሞክራሲ የፍትህና የኩልነት ትግል እንዲቀላቀሉ እመክራቸዋለው::
ሀወሃት/ኢህአዴግ/ ወያኔ ምንም ድርጅታዊ አሰራር መዋቅር መንፈስ የሌለው የጥቂት በሰፈር የተቡዋደኑ ፣ ለአራት አስርት አመት ያህል አመለካከታቸው መቀየር ያቃታቸው ፣ ጥቂት የሰባዊነት ስሜት በውስጣቸው የሌለ ማፊያ ግለሰቦች ስብስብ እንደሆነ በቀላሉ አስረድተዉናል:: አሁን ልክ እንደጠንቁዋያቸው የሚያዩትና የሚሰግዱለት መሪያቸው መሞት/መታመም በሰፊው ከተነገረ በሁዋላ እንኩዋን የታየባቸው ባህሪ ይሉኝታ የሌላቸው ፣ የሃገር መፍረስ የህዝብ መራብ መቸገር ሳይሆን የወያኔ/የአድዋ አምባገነናዊ ሰልጣን የሚያሳስባቸው የቀን ጅቦች ናቸው:: ወያኔ በህግ መተዳደር የማይፈልግ ፣ የበታችነት መንፈስ ያናወዛቸው ፣ የስግብግብነት ስሜት ደማቸው ውስጥ የሚሮጥባቸው ፣ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ፣ በጠብመንጃ እንጂ በዕውነቶች ዙሪያ መደራደር የማይችሉ ስለመሆናቸው ያለፈው ስራቸው አስገንዝቦናል::
ዲሞክራሲያዊ ስርአት ስም ኢትዮጵያውያንንና የአለምን ህዝብ ያጭበረበሩበት የወያኔን ስልጣንና ጥቅም ብቻ የሚያስከብረው ፧ በአለም ላይ የምርጦች ምርጥ ብለው የሚፎክሩበት ፧ በወያኔ መቃብር ላይ ብቻ ማሻሻል የሚሞከረው ህገ መንግስታቸው በሁሉም መልኩ ቀዳዳ የበዛበት ነው:: ጠቅላይ ሚንስቴሩን ዘላለማዊ አድርጎ አስቀምጦዋቸዋል :: እነዚህን ቀዳዳዎች ወያኔ እስካሁን ለማሻሻል ለመድፈን አልፈለገም እንደውም ለማጭበርበርና ለማምታታት በሰፊው ሲጠቀምባቸው ተስተውሎዋል ህዝቡ ህገ መንግስታዊ መብቶቼ ተጥሰዋል ህገ መንግስቱ ይከበር ብሎ ሲጠይቅ ወያኔ ደግሞ ህገ መንግስቱን በሃይል ለመናድ ብሎ ይከሳል :: ላለፉት ሃያ አንድ አመታት ህገመንግስቱ ላይ “መያኔ ብቻ ህገ መንግስቱን መጣስ ይችላል” ተብሎ የተፃፈ ይመስል በየቀኑ መጣስ ብቻ አይደለም እየቀደደው ኖሮዋል ::
የኢትዮጵያን ህዝብ የዋህነት ፣ ታጋሽነት ፣ ጨዋነትና ታዛዝነት ልክ እንደ ፈሪነት፣ ሞኝነትና መሃይምነት ቆጥረውት በጠራራ ዐሃይ በሬ ወለደ ውሸት እየዋሹ ምንም እውነተኛ መረጃ እንዳያገኝ እያፈኑ በጠብመንጃና ኢትዮጵያውያንን እንደፈለጉ እስርቤት በሚያጉሩበት በአራዊት ህጋቸው እያስፈራሩ የወያኔ አምባገነናዊና የአንድ ብሄር የስልጣንና የምጣኔ ሀብት የበላይነት ለማረጋገጥ አቅማቸው የቻለውን ሁሉ እያደረጉ ነው:: አሁን ጠቅላይ ሚንስትራቸው ሞቶም/ታሞም ሁሉም የወያኔ አባላቶች ፧ ደጋፊዎች ፧ በዘር የተዛመዱዋቸውና በስርዐቱ አላግባብ የከበሩ እያሰቡና እየሰሩ ያሉት እንዴት ወያኔ የበላይ ሆኖ እንደሚቀጥል እንጂ እንዴት አገራዊ መግባባት እንደሚፈጠር ፣ የህግ የበላይነት እንደሚሰፍንና ፣ አገሪቱ ካለችበት የፖለቲካና የምጣኔ ሃብት ቀውስ በምን መልኩ መውጣት እንዳለባት አይደለም::
ወያኔዎች ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በማን አለብኝነት ህዝብን ማሰር ማሰቃየት መግደል ግለሰቦችንና ቡድኖችን ማንቃሸሽ መሳደብ ስልጣንን ተገን አድርጎ የሀገርና የህዝብን ሀብት መዝረፍ ለግላቸው ጥቅምና ስልጣን የሀገርንና የህዝብን ጥቅም አሳልፎ መስጠትና የመሳሰሉትን ወንጀሎች ሲፈፅሙ ቆይተዋል:: እነዚህን ሁሉ በወያኔ እምባገነንና ዘራፊ ቡድኖች የሚፈፅሙትን ኢሰብአዊና ኢፍትህአዊ ድርጊቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስወገድ በኢትዮጵያ ህዝብ የተነሱትን የፍትህ የኩልነትና የነፃነት ትግሎችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መተባበርና መሳተፍ ይጠበቅብናል::ማንኛችንም የሀገሬ ሠላምና ደህንንት ይመለከተናል የምንል ግለሠቦችም ሆንን የፖለቲካ ፓርቲ ድርጅት አባላትና ደጋፊዎች በጋራ ተሰባስበን የተቀጣጠለውንና እየተፋፋመ የመጣውን ታላቅ የህዝብ አመፅ በሁለንተናዊ የትግል እስትራቴጂ እንዲታገዝ አድርጎ የሚይዘው የሚጨብጠውን ያጣውን የወያኔን የማፊያ ስርአት እናስወግድ::

ምናባዊ ቃለ-ምልልስ ከማስታወቂያ ሚኒስትሩ ከአቶ በረከት ጋር (ደረጀ ሃ/ወልድ)

 | 

ከደረጀ ሃብተወልድ
ጥያቄ፦ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ? የት ነው ያሉትስ?
መልስ፦ እነዚህ ወገኖች የትራንስፎርሜሽኑን እቅድ ይፋ ስናደርግ ፦”ፖለቲካዊ ውጥረቱን ለማርገብ የተቀየሰና ሊሳካ የማይችል እቅድ ነው እያሉ ፕሮፓጋንዳ ሲነዙ የነበሩ ናቸው”
ጥያቄ፦ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሉ? ወይስ የሉም? መቼስ ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ?
መልስ፦”…ከዚያም የህዳሴውን ግድብ ስንጀምርም፤ በተመሣሳይ መንገድ ፦“መንግስት ይህን ታላቅ ግድብ እሠራለሁ ብሎ የተነሳው፤ በሰሜን ምስራቅ አፍሪቃ የተነሳው ዓይነት አብዮት እንዳይነሳበ
ት የህዝብን አቅጣጫ ለማስለወጥ ነው የሚል ፕሮፓጋንዳ ማራገብ ጀመሩ…”
ጥያቄ፦ “ክቡር ጠ/ ሚኒስት
ሩ ደክመዋል፤ከዚያም አልፎ አርፈዋል የሚሉ ዘገባዎች እየወጡኮ ነው።
መልስ፦ “እህ … እነዚህ ወገኖች አሁንም የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጤንነት በተመለከተ አሉባልታ እየነዙ ያሉት፤ ልማታችንን በማደናቀፍ የሚናፍቁትን የዓረብ አብዮት ለማስነሳት ካላቸው ከንቱ ምኞት በመነሳት ነው፤ይህ ግን እንደማይሳካላቸው ያውቁታል። የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት 20 ዓመታት ያጣጣማቸውን የልማት ድሎች በተጨባጭ ተገንዝቧቸዋል። ከእንግዲህ ወደ ሁዋላ አይመለስም”
ጥያቄ፦”ክቡር ሚኒስትር፤ እስካሁን ስለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጤንነት ላቀረብኩት ጥያቄ የሰጡኝ ቀጥተኛ ምላሽ የለም”
መልስ፦”እህ. እ….ክቡር ጠ/ሚ/ሩ በጥሩ የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።.. ከእንግዲህ በእርሳቸው ጤንነት ዙሪያ የሆነ ነገር በተባለ ቁጥር ፤መንግስት ለእያንዳንዷ ነገር መልስ የሚሰጥበት ሁኔታ አይኖርም”(ይህች ምላሽ ቃል በቃል ከኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር ከአቶ አሊ አብዶ የተወሰደች ትመስላለች) እናም… ሀኪም ያዘዘላቸውን እረፍት ጨርሰው ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ ብለን እናስባለን።
ጥያቄ፦ እረፍቱ እስከ መቼ ነው?አቦይ ስብሀት በአስር ቀናት ውስጥ ይመሳሉ ቢሉንም ፤ያተረፍነው ነገር፦
<ትመጣለች ብዬ- ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት ዓይኔ- ሟሟ እንደ በረዶ> የሚለውን ዘፈን ማንጎራጎር ብቻ ነው። እርስዎ በትክክል ይንገሩን? እስከ መቼ እረፍታቸውን ጨርሰው -መቼ ወደ ሥራቸው ይመለሳሉ?

የጥሩነሽ በወርቅ “ማድመቅ” እና የ “አመለወርቅ” በሀሽሽ “ማሸማቀቅ!”

 | 

የጥሩነሽ በወርቅ “ማድመቅ” እና የ “አመለወርቅ” በሀሽሽ “ማሸማቀቅ!”

Share

አቤ ቶኪቻው
ከቀናት በፊት አንድ አሳፋሪ ዜና ሰምተን ነበር። “ኢትዮጵያዊቷ ዲፕሎማት ሃሽሽ ሲያዘዋውሩ ተገኝተው በቁጥጥር ስር ዋሉ” የሚል አስደንጋጭ ዜና። ዜናው የተሰማው ከወደ እንግሊዝ ነበር። ዴፕሎማቷ ሴትዮዋ ለስሙ ስማቸው አመለወርቅ ነበር። ነገር ግን ስማቸውን መላዕክ አላወጣላቸውም እና “ድንቄም እቴ አመለወርቅ!” የሚያሰኝ ፀያፍ ስራ ሲሰሩ ተይዘው። እኛንም በአለም ፊት አሸማቀውናል!
የሰላሳ ስድስት አመቷ ወይዘሮ አመለወርቅ ይዘው የተገኙት 56 ኪሎ ግራም ካናቢስ የተሰኘ ሀሽሽ ነው። እስቲ እንደው አፈር ስሆን፤ ወንጀሉ ይቅር፣ እኛን ማሸማቀቅም የለመዱት ይሁንላቸው… ነገር ግን ይህንን ሁሉ ሲሸከሙ የጡንቻ መሸማቀቅ ይይዘኛል ብሎ ማሰብ ትንሽ አይገባም…!?
ይህንን ዜና የሰማሁ ጊዜ መንግስታችን እንደዚህ አይነት ዲፕሎማቶችን በውስጡ አቅፎ ደግፎ ይዞ ሌሎች ምስኪን ወገኖች ላይ “መልካም ገፅታዬን አጠፋችሁ፣ የሀገር ደህንነት ስጋት ሆናችሁ፣ ወዘተ ወዘታችሁ” እያለ እስር ግልምጫ እና ጡጫ ማድረሱ “የሚጠምዱትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” የማይባል ግፍ ሆኖ ነው ያገኘሁት።
ለማንኛውም ከቀናት በፊት ቢቢሲን ጨምሮ በርካታ በእንግሊዝ የሚገኙ ሚዲያዎች የመንግሰት ዲፕሎማቷ የሰሩትን አሳፋሪ ስራ በዘገባቸው ይዘው ወጥተው አንገታችንን አስደፍተውን፣ ሽምቅቅ ብለን፤ ኪሏችን ሁሉ ቀንሶ ነበር የሰነበትነው።

Amelework Wondemagegne tried to claim diplomatic immunity when she was caught with 56 kg of cannabis (© AFP)
ትላንት ደግሞ በተቃራኒው ጥሩነሽ ዲባባ ከባልንጀሮቿ ጋር በመሆን ቀና ብለን እንድንራመድ አድርጋናለች። ባንዲራችንን ከፍ አድርጋ እኛም ከፍ ብለን እንድንታይ በተዓምረኛ እግሮቿ ተአምር አሳይታናለች።
ኬኒያዊቷ ተፎካካሪዋ ከጨዋታው በፊት ለሀገሯ ዜጎች አንድ መልዕክት አስተላልፋ ነበር። “ከአሁኑ ወርቅ እንዳገኘን ርግጠኛ ሁኑ እናም ፅዋቹን አንሱ” ብላ ነበር አሉ። በንግግሯ ልበ ሙሉነት የተደሰቱት ኬኒያውያንም ቀድመው በደስታ ሞቅ ብሏቸው ነበር ሩጫውን ሲጠባበቁ የነበሩት።
በአንፃሩ ደግሞ ጥሩዬ፤ “ውጤቱን ከወዲሁ መገመት አልችልም ሜዳ ላይ ይለያል… ደሞም እግዜር ያውቃል” በሚል ትህትና ነበር የጀመረችው። ስትጨርስ ግን ለኬኒያውያኖቹ ትህትና አላሳየችም “እለፉ” አላላቻቸውም ጥላቸው እብስ አለች እንጂ… አሁን እዚህ አልነበረች እንዴ…!? ብለው አጠገባቸው ቢመለከቷት እርሷ ዙሩን ጨርሳ ባንዲራዋን ለብሳለች!
“እኛስ ኮራን በናንተ…!” ቴሌቪዥናችን ከፈተልን እኛም አብረን ዘመርን!
እኔ የምለው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቶች ላይ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ስም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለመፃፍ እጁ እምቢ ያለው ለምንድነው…!? “ክቡር ፕሬዘዳንታችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋችኋል” ብሎ ሲነግረን የጠቅላይ ሚኒስትራችንን የደስታ መግለጫ ለማየት የቋመጥን በርካታ የእርሳቸውን መልካም የምንመኝ ግለሰቦች ነበርን…! ኢቲቪ ግን ምነው እንዲህ ጠምዶ ያዛቸው…!? ችግር አለ እንዴ!?
ለማንኛውም ወዳጄ የመንግስት ባለስልጣኖቻችን “በአጠፋሪስ” ንግድ ያሸማቀቁን ከተማ ላይ አትሌቶቻችን ደግሞ በወርቅ አድምቀው ታሪካችንን ድጋሚ አድሰውልናል። እንኳን ደስ አለን! በቀጣይም ወርቁን ያብዛልን! አሜን!

Friday 3 August 2012

የርዮት አለሙ 14 ዓመት ወደ 5 ዓመት ዝቅ ተደረገ!

 



በተከሰሰችበት የ “አሸብረሽናል” ክስ 14 አመት እና ብዙ ሺህ ብር ቅጣት ተበይኖባት የነበረችው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ፤ የሚያስፈርድብኝ አንዳችም ማስረጃ አልቀረበብኝም እናም  “አቤት ክቡር ፍርድ ቤት” ብላ ይግባኝ ጠይቃ እንደነበር ይታወቃል። የማይታወቅም ከሆነ ይኸው አሁን ተናግሬያለሁ።
የርዕዮት ይግባኝ በቀጠሮ ሲንከባለል ቆይቶ በዛሬው እለት “ውሳኔ” አግኝቷል።
በውሳኔው ርዕዮት፣ ቤተሰቦቿ እና ጠበቀዋ ደስተኛ እንዳልሆኑ ምንጮቼ ነግረውኛል። እንደ ምንጮቼ ከሆነ የርዕዮት ቤተሰቦች እና ጠበቃዋ “የይግባኙ ውሳኔ አቃቤ ህግ ምንም ማስረጃ ባለቀረበበት ሁኔታ የተወሰነ በመሆኑ ፍትሃዊ ውሳኔ ነው ለማለት አያስደፍርም።” ብለዋል በመሆኑም ውሳኔውን ርዕዮት እና ጠበቃዋ በመካከር ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት ሊወስዱት እንደሚችሉ ምንጮቼ ሹክ ብለውኛል።
በዛሬው ዕለት የርዕዮትን ፍርድ ከአስራ አራት አመት ወደ አምስት አመት ዝቅ እንዲል የወሰኑት ዳኛ ርዕዮትን፤ “አንቺም ብትሆኚ በጋዜጠኝነት ስትሰሪ ደህና ደህና ነገር መፃፍ ይገባሽ ነበር!” ሲሉ “መክረዋታል” ይህንን የታዘቡ አንዳንድ አሽሙረኞችም “ደህና ደህና ነገር አለመፃፍ አምስት አመት ያሳስራል ማለት ነው!” ሲሉ ማሸሞራቸውን ሰምቻለሁ!

Thursday 2 August 2012

ትንሽ ወሬ፤ “መለስን ጥራ ሲሉት በረከት መጣ!



በመጀመሪያ ርዕሱን ቁልብጭ ለማድረግ ብዬ የተከበሩትን ሰዎች አንተ በማለቴ ይቅርታ ጠይቃለሁ። (በቅንፋችንም ካለፉት ጊዜያት ልምድ በመነሳት ባለስልጣኖቻችንን እኔ የተከበሩ ብዬ ስጠራ አንዳንድ በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦች የተቀበሩ ብለው እንደሚያነቡ ተደርሶበታል። ነገር ግን ይህ አግባብ አለመሆኑን ለማሳሰብ እወዳለሁ። ምክንያቱም ቀብር ገና ነውና…! የተቀበሩ አይባልም እላለሁ!)
ትለንት ቀን ላይ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና እወጃ “የአቶ መለስ ጤና በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ” የሚል ዜና ሰምተን፤ አለቅጥ ተደስተን፣ ልባቸን በሀሴት ሰክራ ዋለች። አንዳንዶችም “አላዛርን ከሞት ያስነሳ ታምሩ የማያልቅ ጌታ እንደምን ያለ ፅድቅ ቢሰሩ እንዲህ አስነሳቸው…!”  እያሉ ለአምላካቸው ምስጋና አቀረቡ! ዝርዝር ዜናውን ለመስማት ጋዜጠኛይቱ “ምሽት ላይ እንገናኝ” ብላ ቀጠረችን።
ምሽት ለካስ እንዲህ ቀርፋፋ ነው…!? ምሽቱን መጠበቅ የአለም ፍፃሜን ከመጠበቅ እኩል ረዘመብን።
በሀሳባችን መለስ እንደወትሮው ከዙፋናቸው ጉብ ብለው “ስለ ተጨነቃችሁልኝ አመሰግናለሁ… ትንሽ ጉንፋን ብጤ ይዞኝ ነበር። ነገር ግን የኢትዮጵያን ሰላም ማየት ያማይሹ የውጪ ሃይሎች የሻቢያ ተላላኪዎች እና የሀገር ውስጥ ነጭ ለባሾች ብዙ ነገር ሲያስወሩ እንደነበር ሰምቻለሁ እኔ ግን ይኸው አለሁ።” ሲሉን እየታየን ፈነደቅን።

Wednesday 1 August 2012

ዜና በጨዋታ፤ “አይ ሲ ጂ” የኢሳትን መረጃ “እኔ አላልኩም” አለ

አቤ ቶኪቻው
በትላንትናው እለት ኢሳት ራዲዮ “አይ ሲ ጂ” የተባለውን ተቋም ምንጮች ጠቅሶ መለስ መሞታቸውን አረጋግጫለሁ። ብሎ የዘገበ ዚሆን ዛሬ ደግሞ “አይ ሲ ጂ” በድረ ገፁ ላይ “እኔESAT Radio, Ethiopian Satellite Television አላልኩም ስለ ጠቅላይ ሚኒስትራችሁ ሞትም ሆነ ህይወት የማውቀው ነገር የለም” ብሏል።
ኢሳት ከ “ኤይ ሲ ጂ” በተጨማሪ ታማኝ የዲፕሎማት ምንጮችም ነግረውኛል “ሰውዬው ከዚህ በኋላ እቃ አይሆኑም አክትሞላቸዋል የርሳቸው ነገር ከእንግዲህ ኦሮማይ ነው!” ብሎ በልዩ የዘገባ ፕሮግራሙ ሲነግረን በአንክሮ ነበር።
ያው ትላንት እኔም ይሄንን ወሬ ሳቀብላችሁ እስቲ የአቅሜን ያኽል ወሬ ፍለጋ ዞር ዞር ብዬ አካፍላችኋለሁ ባልኩት መሰረት ስለቃቅም ካገኘሁት መሀከል፤ በትላንትናው እለት በራዲዮ ፋና ላይ “የህግ ጉዳይ” በሚወራበት ፕሮግራም ስለ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ህመም እና በእንዲህ ያለው ጊዜ ማነው የሚተካቸው? የሚለው ጉዳይ ላይ በቀጥታ ስርጭት ውይይት ሲደረግበት እንደነበር “ሶሊያና” የተባለች ወሳኝ ወዳጃችን በፌስ ቡክ ግድግዳዋ ላይ ለጥፋልን ነበር። በነገራችን ላይ ይቺው ወዳጃችን ከዚህ በፊት ሚሚ ስብሀቱ “የመነኩሴዎች ፀሎት እያለ እሳቸውማ አይሞቱብንም” ብላ በራዲዮ ፕሮግራሟ ላይ መናገሯንም ነግራን ነበር። “ሶሊን” አመስግነን “ሚሚን” ደግሞ ቆይ እንገማገማለን! እንላታለን። የሆነ ሆኖ የሁለቱ ራዲዮ ጣቢያዎች እንደዚህ መብከንከን ስንሰማ “ኢሳትማ የሆነ የደረሰበት ነገር አለ” የሚያስብል ነው።
እና ወዳጄ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንዴ ሲሞቱ አንዴ ሲነሱ አንዴ ህክምና ላይ ሲሆኑ ሌላ ጊዜ እረፍት ሲያደርጉ እርሳቸው ጠቅላይ ሆነው ሳለ፤ ነገራቸው ግን አሁንም ድረስ አልተጠቀለለም ማለት ነው።
ድሮ አባቴ ሲያጫውተኝ በምድር ላይ ክፉ ስራ የሰራ ሰው ቶሎ አይሞትም ብሎ ነግሮኛል። “አልጋው ላይ ሆኖ ሞተ ሲባል ሲድን፣ ዳነ ሲባል ሲሞት፤ ሰውም ያንገላታል እርሱም ይሰቃያል”። ይለኝ ነበር። አባቴ በተለይ አራጣ አበዳሪዎች እንዲህ አይነት ስቃይ እንደሚገጥማቸው ነግሮኛል። እንዴት ነው ነገሩ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አራጣ ያበድሩ ነበር እንዴ…!?


OFFICIAL: His Excellency Meles Zenawi is DEAD

 



Shocking news for the whole of Africa, Meles Zenawi has passed away from acute justifribilasis fatilosis at the age of 57.  No other leader in the history of the their world has done more to lift his country from the clutches of poverty and delivered Ethiopia into the forefront of modernity in less than 22 years of rule.  His Excellency Zenawi leaves behind a country that is flourishing and his legacy will forever be etched in all Africans as an intellectual giant who has done more for Africa than Nelson Mandela could have done in five lifetimes.  Today is a sad day for all Africans as a son of Ethiopia has been called home by his maker.


President Barack Obama, in a hastily arranged press conference, praised Prime Minister Meles Zenawi as a model leader who has put the needs of his people above the needs of the wealthy.

“Today Africa has lost a bright star, his Excellency Prime Minister Zenawi has been a great partner for the West”, President Obama stated in the Rose Garden.  “We shared many uplifting stories at Camp David.  Prime Minister Zenawi has been an indispensable partner to America and the West as a whole.  We have depended on him to free Somalia from Muslim extremists and have been undertaking yet another quest to stifle Muslim extremism in Ethiopia.  We will sorely miss his leadership and we look forward to the people of Ethiopia voting in a free and fair election as they did in 2005 and voting over 99% for another model Prime Sinister—a Prime Minister—that the West can depend on and value as we valued His Excellency Zenawi.”

News of the sudden passing of Prime Minister Zenawi came as a shock to the Mass Media in the West.  CNN has been forced to stop its 24/7 news coverage of Tom Cruise and Snookie and instead has sent journalists to find out more about the latest developments.  Media personalities have stopped begging for followers on Twitter and are now embarking on journalism as they were taught in college by actually following leads and asking tough questions of the Ethiopian government.

Moreover, economists in the United States are now preparing for another Great Depression unsure if companies like Starbucks will be able to reap billions of dollars in profit without paying fare wages to Ethiopian coffee growers.  Reached for comments from Starbucks CEO Howard Schultz referred to the memo that was sent out to SBX stockholders.

“We view a coming time of instability in Ethiopia, one of our most profitable cash cows in the world due to the passing of our most cherished clientele our valued dealer His Excellency Meles Zenawi”, stated the memo from Starbucks.  “We are hopeful that the next leader of Ethiopia will be a man who will be just as willing and able to let Starbucks invest in Ethiopia.  We look forward to the Ethiopian people supporting a visionary like His Excellency Meles Zenawi so that we can continue our mutually beneficial business relationship.”

News of the sudden passing of PM Zenawi sent the price per share of Starbucks crashing, as of 11:30 AM, Starbucks stock has plummeted more than 25% as coffee traders look to Ethiopia with unease unsure if Ethiopia will nationalize their coffee resources and put in place a system to brand and market their own flavor of “Yagerachif coffee”.  Starbucks locations in Alexandria and Washington DC have reported near riots as the Ethiopian diaspora has been flocking to Starbucks to buy their $5.00 cups of coffee instead of buying their coffee from an Ethiopian owned Café by the name of Sidamo Coffee and Tea in Washington.

We sent a beat reporter to Sidamo Coffee and Tea thinking that there would be an overflow of Ethiopians supporting this café owned by one of their own and instead we discovered fifty Caucasians and not one Ethiopian in this Ethiopian café.  In order to get reaction from Ethiopians, we dispatched to Starbucks three blocks away and there we found 80 Ethiopians sitting around talking politics in the middle of the day.

“Zis is a great day for all Ethiopians; finally we are liberated from this blood thirsty banda dictator who has oppressed all Ethiopians.  This Tigray bastard deserved to die and all Tigray people need to be ethnically cleansed from Ethiopia, we need a final solution for all Tigray people”, stated a man who referred to himself as Nitro Ethiopians who refused to let us use his real name or take his picture and had on ‘I am 100% Eritrean’ t-shirt on.  “We brave Ethiopians are ready to rise up, and we pray zat all Ethiopians worldwide rise up and start a revolution.  We ask all youth to pick up a gun and go shoot all Tigray people, we ask that you become brave Ethiopian revolutionaries like our group Nitro Ethiopians and start a war to free Ethiopia”.

We found it a bit ironic that Nitro Ethiopians, who had on an “I am 100% Eritrean” t-shirt on, would advocate ethnic genocide and encourage all Ethiopians to be brave like him even though he did not want his picture taken nor would he let us use his real name nor reveal his location.  A revolution started with a cup of coffee in an air conditioned Starbucks.

Those who support Meles Zenawi are refusing to come to terms with the sudden passing of Meles Zenawi.  “Woyanes”—supporters of Meles Zenawi—are posting pictures of PM Zenawi all over Facebook playing tennis and walking down airplane steps with his wife Azeb to prove that PM Zenawi is still alive.
The National Rifle Association’s Wayne LaPierre sent out a press release stating his dejection at the sudden passing of PM Zenawi.
“We at the NRA are deeply saddened at the passing of Ethiopia.  Next to Tea Party members and James Eagen Holmes, His Excellency Zenawi was a fervent supporter of the NRA,” stated LaPierre. “His commitment to AK47s and machine guns was unparalleled; Ethiopia has been the biggest importer of assault weapons are we are deeply saddened by the death of our biggest client His Excellency Meles Zenawi. However, we are certain that the next leader of Ethiopia will continue to purchase more machine guns instead of feeding his people and investing in health care”

Dr. Embi, the leader of one of Ethiopia’s 66 political parties “Yet Another Useless Acronym Liberation Front” stated his remorse for the passing of Meles Zenawi.

“To be honest, we at “YAUALF are at a loss of words to explain how we are truly depressed that Zenawi passed away,” stated Dr. Embi.  “Without Meles as a boogie man, we are not sure if the Ethiopian Diaspora will continue to give us money and support us.  We urgently need another blood thirsty dictator that will continue to harass Ethiopians and scare them to death so that we can continue to raise hundreds of thousands of dollars so we can continue to have our meetings at Renaissance hotels and I can continue to call myself Doctor and “Founder”.  To be honest, without a tyrant like Meles Zenawi, I will actually have to get a real job instead of traveling the world in first-class accommodations to various symposiums to advocate for Democracy in Ethiopia”.

Meles Zenawi, dead at the age of 57 before his time and will be sorely missed by his people.  His Excellency Zenawi will be buried at Hellgeba Cemetery on Saturday, August 18th in Addis Ababa, Ethiopia.  Gone too soon, but never forgotten by his people, Meles Zenawi will forever be mentioned in the folklore of African leaders for delivering change in Ethiopia by lifting millions of Ethiopians from poverty and as a transformational feminist standard bearer for making prostitution a booming business in Ethiopia and giving children in Ethiopia access to potable water for free from the sewer systems of Addis Sheraton.  His Excellency Zenawi will be forever remembered as the greatest African leader since Menelik.

Of course if you have not figured it out by now, this as satire—as in fake news meant to make you think.  We here at Brown Condor do not write lies, our standard for everything that we write is that we have to verify all things published from at least four independent sources and one of those sources have to be non-Ethiopians.  We need solid proof that our stories are true and we have be able to independently verify all stories before we go to print . Our stance is that our stories have to be corroborated and proven as true, we do not take the stance that “if it’s not proven as false, it must be true” as many in the Ethiopian media world and political opposition members seem to take.

The truth is that no one knows what the fate of Meles Zenawi is, it is irresponsible to print anything with respect to his health and well-being because no one knows.  It is irresponsible to send press releases announcing his death knowing its false as some try to incite riots and it is ignorant to post pictures of Meles and his wife stepping of planes from two years ago to prove his health.  We will be the first to print an obituary once we are able to verify the passing of Meles Zenawi, and even then, we will not gloat, for as much as we are against Meles Zenawi, we do not wish any man death—we just pray for PM Zenawi and the rest of Ethiopia justice and freedom above all.  You cannot fight injustice and tyranny with lies.  Those who want to replace Meles Zenawi should fight with truth and never revert to lies.  Truth is a guiding light, lies will lead to more tyranny and injustice.

The only time that we deviate from this standard is when we occasionally publish a satire piece in order to prove a point.  What point are we trying to make with this article?  We could go on and spell that to you for another three pages, but we will leave it up to you to form your own conclusions and tell us what message we are trying to prove and what thought we are trying to provoke.  You tell us below what you got out of this article and we apologize in advance for “playing a trick on you”, satire is at times cruel because it highlights our own hypocrisy and our own duplicity.  We hope that you continue reading Brown Condor because we strive to do nothing more and nothing less than provoke thought in our community and report the verifiable news and truth as we see it.

Moreover, if you care about Ethiopia, please contact CNN, MSNBC, FOX, Washington Post, New York Times, etc. Tell them to get off their collective asses and find out what is going on in Ethiopia! Ethiopia is on the brink of Civil War and the Mass Media is doing nothing to find out about the health of Melez Zenawi.  Please email them, tweet them this article URL, Facebook them, call them etc.  You can find out the contact info for each Mass Media from the West by going to their website.  Contact them and tell them to stop reporting about Snooky and acting like Yellow Journalists and instead report on the health and well-being of PM Meles Zenawi.  Ask simply, WHERE IS MELES! Please communicate that message to ALL Mass Media outlets.  Use Twitter and Facebook for something worthwhile.