"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 28 November 2015

የ“ሞጋቾቹ” ድራማ ደራሲና ፕሮዱዩሰሯ ባለመግባባት ተለያዩ


Written by  ማህሌት ኪዳነወል
የ“ሞጋቾቹ” ድራማ ደራሲና ፕሮዱዩሰሯ ባለመግባባት ተለያዩ
ድራማው በደራሲ ውድነህ ክፍሌ ሊቀጥል ነው

  በየሳምንቱ ረቡዕ ምሽት በኢቢኤስ ቴሌቭዥን የሚቀርበው የ“ሞጋቾቹ” ተከታታይ ድራማ ደራሲ በሆነው ኃይሉ ፀጋዬና በፕሮዱዩሰሯ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የተለያዩ ሲሆን ድራማው በታዋቂው ፀሐፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ ይቀጥላል ተብሏል፡፡ 

Tuesday 25 August 2015

መታሰር… መፈታት ?!? (መላኩ አላምረw



መታሰር… መፈታት ?!?
(መላኩ አላምረው)

በዚች በሀገሬ
ትላንት እና ዛሬ
ሚደጋገም ወሬ …
አዕምሯያኑ፣
ብዕራውያኑ፣
‹በነውጥ በሽብሩ›
“ታስረው” የነበሩ …
‹‹ተፈቱ! ተፈቱ! ደስ አይልም?›› ይሉኛል፣
እኔ በበኩሌ …
የመታሰርና የመፈታት ትርጉም ተቀላቅሎብኛል፡፡
በአዕምሯዊ ፍጡር - በሰብዓዊ ዓለም፣
መታሰር… መፈታት… ብሎ ነገር የለም፡፡
ወይም ለእኔ አዕምሮ ሐቁ ግልጽ አይደለም!
…..›››
‹‹እግርን በእግረ-ሙቅ - መሄድን ለማስቆም፣
ዓይንን በጨለማ - እይታን ለማድከም፤
እጅን በካቴና - ከብዕር እንዲቋረጥ፣
አናትን በኩርኩም - ላ’ሳብ ጊዜ እንዳይሰጥ፤››
እንዲያው በመመኘት…
እንዲያው በመሞኘት…
ምን ብዙ ቢደከም………
ሰብዕናን ማሰር
እይታን ማሳወር
አዕምሮን ማጣመም
ሂደትንም ማስቆም
ፈጽሞ አይቻልም፡፡
ምክንያቱም….
በአካል ላይ ሚደርሰው ስቃዩ ከፍ ቢልም፣
የነፍስን ባሕርይ - አዕምሮን ማሰር ግን - ለሰው አይቻልም!
በጥበበ አምላክ የአዕምሮ ተፈጥሮ፣
የሚቆም አይደለም እንደ-ሥጋ ታስሮ፡፡
እንዲያውም እንዲያውም…
‹አዕምሮን ራስ› እንጂ ሌላው አያስረውም
እናም እኒህ ሰዎች!
ባለ ህሌናዎች!
ታስረው ነበር አንበል! እስረኞችስ እኛ …
ህሌናችን ክደን፣
ማስመሰልን ለምደን፣
ከሐሰት ተዋልደን… እንቅልፍ የምንተኛ፡፡

Wednesday 14 January 2015

ቅድስት ዕሌኒ

ቅድስት ዕሌኒ




 የቅድስት ዕሌኒ ባለቤቷ ተርቢኖስ ይባላል፤ በቅድስና ተፋቅረው ነበር የሚኖሩት፤ ተርቢኖስ የሚል ጽሁፍ ያለበት የአንገት ሀብል አሰርቶላት ነበር። ተርቢኖስ ነጋዴ ስለነበር ከጓደኞቹ ጋር በመርከብ ተሳፍረው እሩቅ አገር ሄደው  3 ዓመት በኃላ ይመለሳሉ ፤ ታዲያ መርከብ ላይ እንዲህ እያሉ ይጫወታሉ ፤ እኛስ በሰላም ወደ አገራችን ተመለስን ሚስቶቻችን ግን በሰላም ይጠብቁን ይሆን ሌላ ወንድ ወደውና ለምደው እንዳይጠብቁን አሉ፤ ተርቢኖስ ደግሞ የኔ ሚስት ዕሌኒ ከኔ ሌላ ማንንም አትወድም አትለምድም ይላቸዋል፤ ያንተ ሚስት ከሄዋን ሴቶች ትለያለችን እኔ ሄጄ ወድጃት ወዳኝ ለምጃት ለምዳኝ ብመጣ ምን ትሰጠኛለህ ይለዋል ንብረቴ ሁሉ ላንተ ይሁን ይለዋል በወረታቸው ተወራርደው ይሄዳል::