"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 16 June 2012

ሉሲዎች ለአፍሪካ ዋንጫ አለፉ፤ ቡድናችንን የጫነው አውሮፕላን ከአደጋ ተረፈ




(፟ዘ-ሐበሻ) በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን መጠሪያው “እቱ መላ ምቺ” ይሰኝ ነበር። ዛሬ ስማቸው ተቀይሮ “ሴቶቹ ዋሊያዎች” ወይም “ሉሲ” በመባል ይጠራሉ።በተለያዩ ጊዜያት አኩሪ ድሎችን እያስመዘገቡ የሚገኙት ሉሲዎች ዛሬ ወደ ታንዛኒያ ተጉዘው አኩሪ ድል ይዘው ተመልሰዋል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ብርቱካን ገ/ክርስቶስ በ65ደቂቃ ባስቆጠረችው ግብ የታንዛኒያ አቻውን 1-0 በማሸነፍ ኢኳቶሪያል ጊኒ ለምታዘጋጀው ስምንተኛ የአፍሪካ ማለፉን አረጋግጧል። የሴቶች የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾቻችን 60ሺ ተመልካች በሚይዘው በታንዛኒያ ስታዲየም ፍፁም የጨዋታ የበላይነት ነው ጨዋታውን በድል የማጠናቀቅ የቻሉት፡፡ ቡድኑ በታንዛኒያ ባስመዘገበው ድል ኢትዮጵያ ቡድን ለሁለተኛ ጊዜ ለአፍሪካ ጨጫቻ እንዲያልፍ አድርገዋል፡፡
በ እንዲህ እንዳለ ነገ ቤኒን ላይ ላለበት ወሳኝ ጨዋታ የወንዶቹ ብሔራዊ ቡድናችን በቴክኒክ ችግር ምክንያት ከመንገድ ተመልሶ እንደነበር ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ አመለከተ፡፡ አውሮፕላኑ ወደ ቤኒን መብረር ከጀመረ በኋላ የቴክኒክ ችግር ገጥሞት ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ለመቆም ተገዶ ነበር። የአይን እማኞች እንደሚሉት በአሁኑ ሰዓት አውሮፕላኑ በሰላም ካረፈ በኋላ የእሳት አደጋ መኪና ሲከተለው ነበር ብለዋል። ሆኖም ግን አውሮፕላኑ ከቆመ በኋላ መንገደኞቹ በሰላም መውረዳቸውንና ምንም የተጎዳ ሰው እንደሌለ ከአዲስ አበባ ለዘ-ሐበሻ ድረ ገድ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

ኪነትና ነፃነት


 (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም)

በደርግ ዘመን በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ የኪነት ስብሰባ ተካሂዶ ነበር፤ እንጉርጉሮ በምትል ትንሽ የግጥም ጥራዝ ሳይሆን አይቀርም ለስብሰባው ተጋብዤ ነበር፤ በዚህ ስብሰባ ላይ አቶ አያልነህ ሙላትና ዶር. ኃይሉ አርአያም አስተናጋጆች እንደነበሩ አስታውሳለሁ፤ የመክፈቻው ንግግር ሥርዓት እንዳበቃ መድረኩ ለአስተያየት ሲከፈት የመጀመሪያው ጠያቂ እኔ ነበርሁ፤
‹‹በመድረኩ ላይ የተባለው ሁሉ በትክክል ገብቶኝ እንደሆነ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ፤ ስለዚህም አንድ ጥያቄ ላቅርብ፤›› ብዬ- ‹‹ኪነት ማለት አዝማሪነት ማለት ነው ወይ?››-- ብዬ ተቀመጥሁ፤ በሦስቱም የስብሰባ ቀኖች ‹‹ኪነት አዝማሪነት ነው ወይ?›› የሚለው ጥያቄ እየተነሣ ቆየ፤ አዝማሪነት ስትል ምን ማለትህ ነው ብለው የጠየቁ ነበሩ፤ በቀለለ አማርኛ ልገልጽ አልችልም በማለት እስከ ሦስተኛው ቀን ቆየሁ።
አንድ ሎሌ እየተውዘገዘገ ርእዮተ ዓለምንና አብዮትን የሕይወት ካባ አስመስሎ ‹‹ከርእዮተ ዓለሙ ውጭ ምን አለ!›› እያለ አለማወቁን አሳወቀ፤ ኪነት አዝማሪነት ነው፤ አዝማሪነት ኪነት ነው ማለቱ ነበር፤ ሌሎችም ኪነትንና አዝማሪነትን ለማጋባት የቃጣቸው ሎሌዎች ነበሩ፤ አንዳንዶች ግራ ገብቶአቸው ለቡና ስንወጣ የጠየቁኝ እንደታምራት ሞላ ያሉ የኪነት ሰዎች ነበሩ፤ በእውነቱ እዚያ ውስጥ ከነበሩት ውስጥ ማንኛውም ቢሆን በልቡናው ኪነትንና አዝማሪነትን መለየት ያቃተው የነበረ አልመሰለኝም።
በሦስተኛው ቀን ተነሣሁና በአንዲት ልጅ ፍቅር ተወጥሬ አንድ ግጥም ብጽፍ ርእዮተ ዓለሙ ወይም አብዮቱ በእኔና በልጅቱ መሀከል በምን ቀዳዳ ይገባል? ሕይወት አይቆምም፤ ይቀጥላል፤ ርእዮተ ዓለም ግን በርእዮተ ዓለም ይለወጣል፤ ለአብዮትም አብዮት አለው በማለት ሎሌዎቹን አስደንግጬ ድርሻዬን ተወጣሁ!

ኪነት ነፃነት ነው፤ ኪነት የፈጣሪነት ጥበብ ነው፤ ኪነት ውበት ነው፤ ኪነት ደስታና ሳቅ ነው፤ ኪነት ሐዘንና ለቅሶ ነው፤ ነፃነት፣ የፈጣሪነት ጥበብና ውበት የኪነት መለያ ባሕርዮች ይመስሉኛል፤ ኪነት በሰው ልጅ ውስጥ የፈጣሪው እስትንፋስ መኖሩን የሚገልጽና ፈጣሪነትን ከፈጣሪው የሚጋራበት ስጦታም ችሎታም ነው፤ እንደዚህ ያሉ ሰዎች የአንድ አገር ዓይንና ጆሮ፣ አእምሮና ኅሊና ናቸው፤ የአንድ አገር ሕዝብ የሥልጣኔ ደረጃ በእንደዚህ ያሉ ሰዎች ብዛትና በድንበር-ዘለል ተጽእኖአቸው ይለካል፤ ለምሳሌ ፈረንሳይ የኪነት ሰዎችን ከየትም የመሳብ ችሎታዋ ወደር የሌለው ነው፤ እንዲሁም አሜሪካ በሙሉ ባይባልም ኒው ዮርክ የኪነት ሰዎችን የሚስብ ከተማ ነው።

በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ አቶ ሐዲስ ዓለማየሁ ፍቅር እስከመቃብር ውስጥ በጥሩ መልኩ በጉዱ ካሣ ያመለከቱት ይመስለኛል፤ ክፉ መልኩ ግን አስቀያሚ ነው፤ ዘፈኖች የሚታሰሩበት አገር ነው፤ የኪነት ሰዎች የሚታሰሩበት አገር ነው፤ መጻሕፍትን ማቃጠልም እናውቅበታለን፤ አሁን ደግሞ ከየመሥሪያ ቤቶች ቤተ መጻሕፍት እያወጡ መጻሕፍትን መሸጥ ፈሊጥ ሆኖአል፤ በአጠቃላይ የፈጠራ ሰዎችን ከነፈጠራቸው ማፈን የሚወራረሱት ልማድ ሆኖአል፤ ከተለመደውና ከተፈቀደው ወጣ ያለ ነገር ወይ ለእስር ወይ ለስደት ይዳርጋል፤ በእውነቱ ከሆነ ኪነት የሚሰደድ አይመስለኝም፤ የኪነት ሕይወቱም ሆነ ሞቱ በነፃነት ነው፤ የተሰደደ ኪነት የሬሳ ጭፈራ ነው።

በብዙ አገሮች ኪነትን የሚደግፉ ሀብታሞች አሉ፤ በኢትዮጵያም አቶ መሀመድ አላሙዲ የዘፋኞች አለኝታ መሆኑ ይነገራል፤ አንድ ሰው መኖሩ የጠቅላላውን ጨለማ አይገፈውም። ግራም ነፈሰ ቀኝ ራሱን ነፃ ያላወጣ ኪነት ከአዝማሪነት ይቆጠራል፤ አዝማሪነት ከመዝፈን ጋር ብቻ የተያያዘ አይደለም፤ ውዳሴንም ሆነ ገድልን ለወፍራም እንጀራ የሚጽፍ አዝማሪ ነው፤ በሌሎችም ሙያዎች ያው ነው። አዝማሪነት የፈጣሪነት ጥበብንና ውበትን ሊይዝ ይችል ይሆናል፤ ነፃነት ግን ለአዝማሪነት የባሕርዩ አይደለም፤ ጥቅምን አይቶ የሚነሣ አዝማሪነትና ያለምንም ምኞት አፍአዊ ሁኔታዎች በሚቀሰቅሱት ሀሳብና ስሜት በጥልቀት ነፍሱ ሲነካ ነፍሱን ቧጥጦ የሚወጣው ኪነት አንድ ሊሆኑ አይችሉም። በአንድ ዓይነት ኪነት ላይ ያለውን የባህል አጥር እየጣሱ ስሜታቸውን በመጠኑም ቢሆን የሚገልጹ ሰዎች ነበሩ፤ አዝማሪዎች፣ አልቃሾችና እረኞች፤ በተረፈ ግን ኢትዮጵያ የኪነት አገር ለመሆን አልታደለችም፤ ነፃነት ሲመጣ ኪነት ይነግሣል፤ ችጋርም ይጠፋል።

የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሠራተኛ በፖሊሶች ተደብድቦ መሞቱ ተገለጸ

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለዋል

ላለፉት አምስት ዓመታት ያህል በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ይሠራ የነበረው አቶ ሀሚድ ወዳጆ የተባለ ግለሰብ፣ ሰኔ 2 ቀን 2004 ዓ.ም ምሽት ላይ ቄራ አካባቢ በፖሊሶች በደረሰበት ከባድ ደብደባ ሕይወቱ ማለፉን ቤተሰቦቹ ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ አቶ ሀሚድ በፖሊሶች ተደብድቦ ሕይወቱ ሊያልፍ የቻለው ከጓዳኞቹ ጋር ሲዝናኑ አምሽተው የ2012 የአውሮፓ ዋንጫ ተፋላሚ የነበሩትን የጀርመንና የፖርቹጋል ጨዋታን በሚመለከት የተወሰኑት ‹‹ወደ ቤት እንግባ›› ሲሉ የተወሰኑት ደግሞ ‹‹ጨዋታውን እንመልከት›› በማለት ሲነጋገሩ ‹‹ለምን ትረብሻላችሁ?›› በማለት ፖሊሶቹ ባነሱት ጥያቄ አለመግባባት ላይ በመድረሳቸው፣ በደረሰበት ድብደባ መሆኑን ከጓደኞቹ የተረዱት ቤተሰቦቹ ተናግረዋል፡፡

በወቅቱ አብሮት የነበረው ጓደኛው እንደገለጸው፣ ቄራ አካባቢ ሲዝናኑ ቆይተው  መስቀልኛ ጫፍ ላይ ሲደርሱ ‹‹ኳስ እንይ ወይስ ወደቤት እንግባ?›› እየተባባሉ ሲነጋገሩ፣ አራት ዱላ የያዙና ሁለት ክላንሽኮቭ መሣሪያ የያዙ ስድስት ፖሊሶች ተጠግተዋቸው ‹‹ምን ያስጮሀችኋል? ለምን ትረብሻላችሁ?›› ብለው ጥያቄ እንዳቀረቡላቸው ተናግሯል፡፡

Friday 15 June 2012

ማመልከቻ፤ “ኢህአዴግ” ከሚለው ውስጥ ዴ እንድትወጣ ስለመጠየቅ




እኔ የምለው ኢህአዴግ ድሮ “ብሶት የወለደው” ነበር የሚባለው። አሁን ደግሞ የሚሰራውን ልብ ብለው ያዩ አንዳንድ ግለሰቦች “ጭንቀት የወለደው እያሉ”  ሲጠሩት እየሰማሁ ነው። ስጠረጥር የሆኑ እጣ ፈንታ ነጋሪ፤ “መጨረሻህ እየደረሰ ነውና ከባድ ጥንቃቄ አድርግ” ብለው አስጨንቀውታል መሰለኝ!  በየቦታው የሚወሰዱ ከእርግጫ የሚስተካከሉ እርምጃዎችን ልብ ብትሉ  የምርም ጭንቀት የወለዳቸው ናቸው!   (እኔን ጭንቅ ይበለኝ!  ወይስ አይበለኝ…?)

እናም ሀገሬው “ጭንቀት የወለደው የኢህአዴግ ሰራዊት በሃያ አንድ አመቱም በርካታ ነገሮችን እየተቆጣጠረ እና እየቆጣጠረ ይገኛል” እያለ እየቦጨቀው ይገኛል።

በየጊዜው የሚወጡት አዎጆች እና ህጎች በሙሉ “አይቻልም” የሚሉ ናቸው። ማንኛውም ታጋይ እና የታጋይን ገድል በየ ግንቦት ሃያው የሰማ ሰው እንደሚያስታውሰው ህውሐት ያኔ ጫካ እያለችም የማትከለክለው ነገር አልነበራትም። እንኳንስ ሌላው ቀርቶ ተፈጥሯዊ የሆነውን የወንድና ሴት ግንኙነት ራሱ በጥብቅ ከልክላ ነበር።

በአሁኑ ጊዜ ደግሞ “ታጋዮቹ የፈለጉት ነገር ሁሉ ሲፈቀድላቸው እኛ ህዝቦቹ በተራችን ሁሉንም ነገር እየተከለከልን ነው።”  የሚል ሰው ተበራክቷል። እስከ አሁን በይፋ ያልተከለከለው የፍቅር ግንኙነት ብቻ ነው። እርሱም ቢሆን፤ “ተገናኝተን ሻይ ቡና እንኳ ለማለት የሚያስችል አቅም በማጣታችን እንደተከለከለ ቁጠረው!” ያሉኝ ወዳጆች አሉ።

የምር ግን ወዳጄ ዘንድሮ ያልታገደ ነገር ምንድነው? በየነጋው የምንሰማው ሁሉ እንትን ተከለከለ፣ እንትን ታገደ፣ እንትን ተዘጋ፣ የሚል ብቻ ሆኗል። ከዚህ በፊት ኢቲቪ እንደነገረን፤ “የአሁኑ መንግስት ልማታዊ መንግስት ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትሩም ልማት እንጂ ለዚህ  ህዝብ ዴሞክራሲ ምንም አያደርግለትም በሚለው ዜማቸው ሲናገሩ እንደሰማነው “ዴሞክራሲ እና ልማት ምንም ግንኙነት የላቸውም።” ብለውናል። አንዳንድ ካድሪዎች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ሲተረጉሙ ዴሞክራሲ “እንደውም የእድገት ፀር ነው።” ብለው እየተናገሩ ነው።

ታድያ እንደዚህ ከሆነ በአውራው ፓርቲ ስያሜ ኢህአዴግ ውስጥ “ዴ” ምን ልታደርግ ተሰነቀረች? ሰዉ እኮ ፊልም ሲታገድ፣ ስካይፕ ሲታገድ፣ ዌብ ሳይቶች ሲዘጉ፣ ራዲዮ ጣቢያዎች ሲጠረቀሙ፣ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ሲታወኩ “እንዴ!” እያለ የሚደነቀው እኮ በስማችን ውስጥ “ዴ” በመኖሯ ሳቢያ ነው።

“ዴ” ማለት ዴሞክራሲ ማለት ነው። እንግዲያስ ከልካዩ መንግስታችን ሁሉን ነገር እየከለከለ አረ የ ”ዴ” ስራ ምንድነው? በሚል ለተቺዎች አጋልጦ ከሚሰጠን አንድ ጊዜ ስያሜውን ቢያስተካክለው ግልግል ይሆናል የሚል አስተያየት አለኝ። ስለዚህም እንደሚከተለው አመለክታለሁ።

እኔ አመልካቹ ግለሰብ በሀገሪቱ ውስጥ እየተከናወነ ያለውን ገደብ የለሽ ክልከላ በሙሉ ልቤ የምደግፍ ስሆን፤ በዴሞክራሲ እና “በልማት መካከል ምንም ግንኙነት የለም” የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትሬን ንግግር ወደ መዝሙር ቀይሬ ጠዋት ማታ የማንጎራጉር መሆኔንም ለማሳወቅ እወዳለሁ።

መንግስታችን ሁሉንም ነገር መከልከሉ ለእኛው አስቦ እንዳንበላሽ ሰግቶ እንደሆነም አምናለሁ።   ዴሞክራሲ የሚባለው ነገርም አጉል ቅብጠት መሆኑ ገብቶኛል። በመሆኑም በገዢው ፓርቲ ስያሜ “ኢህአዴግ” ውስጥ ያለችውን “ዴ” እንድትወጣልን በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።

Thursday 14 June 2012

The Ethiopian government has clamped down on Internet-based voice-calling service, making their use a criminal offence. By Craig Wilson.


The Ethiopian government has clamped down on Internet-based voice-calling service, making their use a criminal offence. By Craig Wilson.

Ethiopia’s state-owned Internet service provider, the Ethiopian Telecommunication Corporation (Ethio-Telcom), has begun performing deep-packet inspection of all Internet traffic in the country. The country’s government recently ushered in new legislation that criminalises the use of services such as Skype, Google Talk and other forms of Internet phone calling.


The new law, which came into effect on 24 May, makes use of Internet voice services punishable by hefty fines and up to 15 years in prison.


The official line from the government is that the move is intended to protect national security and protect the national, state-owned telecoms carrier from losing revenue to Skype and similar services; this, despite the fact that Ethiopia’s fixed-line penetration rate is the second worst in Africa (after Sierra Leone) at an estimated 1% of its 85m strong population.

Ethiopia has instituted numerous restrictions on its digital community in recent years. The government has previously closed down Internet cafes offering voice-over-Internet protocol services and, in December 2006, made it obligatory for Internet cafes to keep records of the names and addresses of their customers in an effort to clamp down on bloggers and other users critical of the regime.

The new law prohibits all VoIP traffic along with audio and video data traffic via social media. The Africa Review reports that the law also gives the government the right to inspect any imports of voice communication equipment and accessories.

The OpenNet Initiative, which tracks Internet filtering and surveillance, says in a report on Ethiopia that the country already blocks all blogs hosted at blogspot.com and at nazret.com, a site that aggregates Ethiopian news and has space for blogs and forums.

The new legislation is no doubt also motivated by the events of the Arab Spring that saw mass protests organised via social media. With many bloggers critical of Ethiopia’s current government, censorship by the state looks likely to increase

Skype users in Ethiopia could face 15 years of jail time



Skype users in Ethiopia could face 15 years of jail time
Posted by admin on June 14, 20120 Comment
By Aljazeera – a new law in Ethiopia has criminalized the use of VOIP (Voice Over Internet Protocol) services such as Skype. Users could face up to 15 years of jail time. The law was passed May 24th, but the story wasn’t picked up by international media until recently. 
http://stream.aljazeera.com/story/ethiopia-skype-me-maybe-0022243

ተወዛዋዥ ኩሪባቸው ወ/ማርያም ተወገዘች




Wednesday, June 13th, 2012 | Posted by

(ከሮቤል ሔኖክ)
“የበላችበትን ወጪት ሰባሪ” ነበር ያለው በዋሽንግተን ዲሲ የሚኖረው ኢትዮጵያዊው ስንታየሁ ገብሩ። “ኩሪን ለረዥም ጊዜ በውዝዋዜዋ አደንቃት ነበር። በተለይ በዋሽንግተን ዲሲ ከማሪቱ ለገሠ ጋር ከ15 ዓመት በፊት እዚህ ስትመጣ በችግር ላይ በነበረችበት ወቅት የደረሰላት የኢትዮጵያ ሕዝብ ነበር። ይህች አርቲስት ዲሲ በወረቀት እጦት ስትሰቃይ ቆይታ ለአሜሪካ መንግስት ጥገኝነት ጥያቄ አቅርባ ወረቀት ያገኘችው በባል ነው። በችግሯ ጊዜ የደረሰላትን ሕዝብ ክዳ ዛሬ ከደም መጣጭ ወያኔዎች ጋር ሆና ለሆዷ መሰለፏ አሳፍሮኛል። ከዚህ በኋላ በዚህች አርቲስት ዝግጅት ላይ አልገኝም” ሲል አስተያየቱን የቀጠለው ስንታየሁ “ኩሪ ስሟን ቀይራ እፈሪ ብትባል ይሻላል” ብሏል።
በወያኔና በአላሙዲ ገንዘብ ዋናውን ESFNA በእጃቸው ማስገባት ያቃታቸው ተላላኪዎች ተገንጥለው በመውጣት ተለጣፊ የስፖርት ፌዴሬሽን በማዘጋጀት በዋሽንግተን ዲሲ የስፖርት ፌስቲቫል ቢያዘጋጁም፤ ከወያኔ በስተቀር የትኛውም ሕዝብ አልተቀበላቸውም። በድፍረት ድምጻዊ ነኝ ትበል እንጂ እኛ በውዝዋዜዋ የምናውቃት ኩሪባቸው ወልደማርያም ለሆዷ በማደር አርቲስቶቹን ዳላስ ላይ ከሚከፈላችሁ ገንዘብ የበለጠ ይከፈላችኋል በማለት ዘፋኞችን ልታባብል ብትሞክርም አልተሳካላትም። ለዘፋኞች በዋሽንግተኑ ኮንሰርት ተሳተፉ በሚል የፊርማ ወረቀትና የ$3000 በስማቸው የተጻፈ ቼክ ይዛ ብትዞርም ዘፋኞች ሁላ እምቢ ብለዋታል።

Wednesday 13 June 2012

ሁለት የወያኔ ባለስልጣናት በአ.አ ስታዲየም ለቡጢ ተገባበዙ




ተጠባባቂ ወንበር ላይ የነበሩት ጀግኖች ልጆቻችን
በብራዚል ለሚደረገው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያና የመካከለኛው አፍሪካ ብሔራዊ ቡድኖች በአዲስ አበባ ስታዲዮም ባደረጉት ግጥሚያ መሀከል ክቡር ትሪቩን የተቀመጡ የወያኔ ባለሥልጣናት በቦክስ ለመደባደብ ተነስተው በዕለቱ የክብር እንግዳ ገላጋይነት ፀቡ መብረዱን በስፍራው የተገኙ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ምንጮች ገለፁ፡፡
የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ዘገባ እነሆ፦
ምንጮቻችን እንዳስታወቁት ድብድቡ በጠባቂዎቻቸውና በሥፍራው ለጥበቃ የተመደቡ ፖሊሶች ሊበርድ ባለመቻሉ የዕለቱ የክብር እንግዳ ተነስተው ፀቡ እንዲበርድ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በሥፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፁት በዕለቱ የውሃና ማዕድን ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ የእለቱ የክብር እንግዳ፣ የስፖርት ኮሚሽነሩ አቶ አብዲሳ ያደታ፣ የደደቢት ስፖርት ክለብ መሥራችና ፕሬዝዳንት ኰሎኔል አወል ኢብራሂም እና ሌሎች ባለሥልጣናት በእንግድነት ተገኝተው ነበር፡፡ ኰሎኔል አወል ከአቶ አብዲሳ ኋላ ተቀምጠው በስሜታዊነት ተውጠው እየጮሁ ተጫዋቾችን ‹ያዘው! ሩጥ! አቀብል› እያሉ ይጮሁ እንደነበር ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ አቶ አብዲሳ ያደታ ኮሎኔሉን ‹‹እባክህን ጆሮዬን አሞኛል አትጩህብኝ!›› በማለት ሲጠይቋቸው ኰሎኔሉም ‹‹ጆሮህን ካመመህ እዚህ ምን አስቀመጠህ? ሄደህ አትተኛም!›› በማለታቸው አለመግባቱ ተፈጠረ ይላሉ የአይን እማኞቹ፡፡
ስለ ዕለቱ ግጭትም ሲያብራሩም ‹‹አለመግባቱ ተካሮ ሁለቱም ለድብድብ ሲነሱ የባለሥልጣናቱ አጃቢዎችና በሥፍራው ለጥበቃ የተመደቡ ፖሊሶች ፀቡን ለማብረድ ቢሞክሩም ሊበርድ ባለመቻሉ
የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ አለማየሁ ተገኑ ተነስተው ገላጋይ በመሆናቸው ፀቡ ሊበርድ ችሎአል” ሲሉ ገልፀዋል፡፡

የውሸት ችርቻሮ ይቁም! በአንዲት ዜና 15 ውሸቶች


የውሸት ችርቻሮ ይቁም! በአንዲት ዜና 15 ውሸቶች


በአበበ ገላው
በኢትዮጵያ የሚታተመውና በድረ ገጽ አማካኝነት የሚነበበው “አዲስ አድማስ” በመባል የሚታወቀው ሳምታዊ ጋዜጣ እጅግ ሃላፊነት የጎደለው የፈጠራ ወሬ በዜና መልክ ሰሞኑን አስነብቧል። በዘባው መሰረት ለደህንነቴ ስለሰጋሁ ቤቴን ለቅቄ ከዋሽንግተን ዲሲ እርቄ በሁለት የደርግ አየር ወለዶች እየተጠበኩ በአንድ “ቪላ” ውስጥ እንደምኖር ይሄው “ጋዜጣ” ነግሮናል። ከዚህም በተጨማሪ 250ሺ ዶላር በሽልማት ቃል እንደተገባልኝና ከዚሁም 120ሺ ዶላር ባንክ ማስገባቴን “ዜናው” ያትታል። ዜና ተብዬዋ ከአስራ አምስት በላይ ውሸቶችን በማካተት ወደር ያልተገኘላት ልብ ወለድ መሆንዋ ብዙም አያጠያይቅም።
እውነታው ግን ህወሃቶች በአሜሪካን ሀገር አንገት አቀርቅረው ተሸማቀውና ከህዝብ አይን ተደብቀው መኖራቸው የአደባባይ ሚስጢር ነው። እኔ በዚች ታላቅ ሃገር ተደብቄ ሳይሆን በነጻነትና በኩራት ነው የምኖረው።
ሰሞኑን በተቀነባበረ መንገድ በህወሃት የዜና አውታሮች እየተፈበረከ ካለው የሀሰት ውንጀላና በሬ ወለደ ወሬ አንጻር የአዲስ አድማሱም ዘገባ ሆን ተብሎ ዋናውን ጉዳይ በርካሽ ውሸትና ወሬ ለማድበስበስ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ማንም ሊዘናጋ እይገባም። ጥያቄው የገንዘብ፣ የቪላ፣ የአጃቢና ተራ መሰል ጉዳዮች አለመሆኑ በግልጽ እየታወቀ በአለም መሪዎች ፊት የተስተጋባው የኢትዮጵያ ህዝብ መሰሪ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ማሰራጨት የፋሺስታዊው ስራትን ኪስራ የበለጠ ከማጋለጥ ያለፈ ፋይዳ የለውም። የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የመብትና የክብር መሆኑ ግልጽ ነው።
በቅርቡም የNational Press Club አባልነቴና “የጋዜጠኛ ፈቃዴን” መሰረዙ፣ የአሜሪካ መንግስት በአቶ መለስ ላይ ያሰማሁት ተቃውሞ እንዳበሳጨው በህወሃት የተፈበርኩ ዜናዎች በሙሉ ሃሰት መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል። በአሜሪካ ትልቁ የጋዜጠኞች ማህበር ናሽናል ፕሬስ ክለብ ፕሬዚዳንት የሆኑት ቴሬሳ ዌርነር በስርአቱ ደጋፊዎች በኔ ላይ የቀርቡላቸውን በርካታ ውንጀላዎች መርምረው ውድቅ ማድረጋቸውን ይፋ አድርገዋል። ማህበሩም የኔን እውነተኛ ጋዜጠኛነት ጥያቄ ውስጥ እንደማያስገባና ከጎኔ እንደሚቆም አረጋግጠውልኛል።

የ‹‹አራት ኪሎው›› እና ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› ወግ


የ‹‹አራት ኪሎው›› እና ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› ወግ




ተመስገን ደሳለኝ
ሲሳይ አጌና በቅርቡ በመጀመሪያ በጀርመን፣ ቀጥሎ በአሜሪካን ሀገር ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› የሚል ርዕስ ያለው መፅሐፍ አሳትሟል። በእርግጥ መፅሐፉ እስከአሁን ሀገር ቤት መግባት አልቻለም (ምናልባት ወደፊትም ላይገባ ይችላል)
ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በኢትዮጵያ የነፃ ፕሬስ ታሪክ የጎላ አሻራ ካላቸው ጥቂት ጉምቱ እና ትንታግ ጋዜጠኞች አንዱ ነው። ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ በድህረ ምርጫ 97 በተነሳው አለመግባባት ስራ እስካቆመበት ዕለት ድረስ ‹‹ኢትኦጵ›› እና ‹‹አባይ›› የተባሉ ጋዜጦችን በባለቤትነት ይመራ ነበር። በተለይ ኢትኦጵ ጋዜጣ በእጅጉ ተወዳጅ ከመሆኗም ባሻግር በስርጭትም ግንባር ቀደም እንደነበረች ይታወሳል።
ጋዜጠኛ ሲሳይ ከቅንጅት መሪዎች ጋር አብሮ ታስሮ ነበር። የተለቀቀውም ልክ እንደእስክንድር ነጋ ፍርድ ቤቱ ‹‹ነፃ ነህ›› ብሎት ነው፡፡ ይህ አንድ እውነት ቢሆንም ብሮድካስት ኤጀንሲ የተባለ ‹‹ፍቃድ ሰጪ እና ፍቃድ ነሺ›› መስሪያ ቤት ወደ ፕሬሱ እንዳይመለስ በመከልከሉ ዛሬ በአሜሪካን ሀገር በስደት ይኖራል። ‹‹የቃሊቲው መንግስት›› የሚል ርዕስ የሰጠውን መጽሐፉንም ያሳተመው በዛው በስደት አለም ነው። (በነገራችን ላይ ይህ ፅሑፍ የመፅሐፉ ዳሰሳ /Book review/ ባለመሆኑ ስለመፅሐፉ ይዘት፣ ጠንካራ እና ደካማ ጎን አንነጋገርም። የምንነጋገርበት አብይ ጉዳይ በመጽሐፉ ላይ ስለተገለፀው የፍትህ ስርዓቱ ሹቀት፣ የፀጥታ አስከባሪዎች ገለልተኛ ያለመሆን፣ ስለእስረኛ አያያዝ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ብቻ ነው። ይህንን መንገድ የመረጥኩበት አንዱ ምክንያት የሚመለከተው ክፍል ቢያንስ በዋና ዋና ጉዳዮቹ ላይ መልስ ይሰጥበታል በሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከመጋረጃው ጀርባ ያለውን የኢህአዴግን ፖለቲካ ‹‹ፈገግ›› በሚያደርጉ ገጠመኞች ታጅበን ለማየት እንዲያስችለን ነው) በቅድሚያ ሲሳይ አጌና ይህንን መፅሐፍ ለምን እንዳዘጋጀ በመግቢያው ላይ ከገለፀው ጨርፈን እንይ፡-

ሳላዲን እየታከመ ነው – መሪነታችን ይቀጥል ይሆን ወይስ እንደትላንቱ


 (ገነነ መኩሪያ ሊብሮ)

ወደ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ዘገባ ከመሄዳችን አስቀድሞ ኢሳት ቲቪ ላይ ኤርሚያስ አማረ ስለ ሴቶች እና ወንዶቹ ብሄራዊ ቡድናችን እንዲሁም ስለዩሮ 2012 ያቀረበውን ዘገባ ቪዲዮ እንከታተል።

(ሊብሮ) ሳላዲን ሰኢድ በትላንቱ ጨዋታ በመጎዳቱ ለሚቀጥለው ጨዋታ ይደርሳል ወይስ አይደርስም እየተባለ ነው፡፡ ይሳቅ ጋር እየታከመ ነው፡፡ ጥሩ ህክምናም እየተደረገለት እንደሆነም ይነገራል፡፡ በልምምድ ላይ ይታይና ለሚቀጥለው ጨዋታ ይደርሳል አይደርስም የሚለው ይወሰናል፡፡ በነገራችን ላይ ሁሉም ከኳስ ሲይዝ ሳላዲንን ነው የሚፈልገው፡፡ የቡድን ስራ የሚባል ነገር እየጠፋ ነው፡፡ ተጫዋቹ ከተጎዳ ማን ላይ ሊያተኩሩ ነው፡፡ ትላንት ሳላዲንን ፍለጋ በረጅሙ የተላኩ ኳሶች አብዛኞቹን ሴንትራል አፍሪካ ወስዷቸዋል፡፡ እነሱም ሰላዲን ነን እያሉ ነው የሚቀበሉት? ቡድናችን ለአፍሪካ ዋንጫ ቤኒንን ለመግጠም አርብ ይጓዛል፡

Tuesday 12 June 2012

ቂ.ቂ.ቂ.ቂ..ቂ.. መለስ ዜናዊ አኬልዳማ ፊልምን በአበበ ገላው ላይም አሠሩ

(ከሮቤል ሔኖክ)
አቶ መለስ የአእምሮ ኪሳራ እንደደረሰባቸው የሚያሳይ ዜና ነው ዋልታ ያስደመጠን። አበበ ገላው በአሜሪካ መንግስት በየትኛውም ስብሰባ ላይ እንዳይገኝ ታገደ ይልና ዜናው ዝርዝሩ ላይ ሲገባ ደግሞ አቶ ብርሃኔ ገብረክርስቶስ (የሰሎሜ ታደሰ…) “እኔን እንደሚገባኝ… የአሜሪካ መንግስት በሚያዘጋጃቸው ስብሰባ ላይ አበበ እንዳይገኝ ታግዷል” ይሉናል። አቶ ብርሃኔ የመለስ ታማኝ ቡችላ ምን ማለታቸው ይሆን እርሳቸውን የገባቸው እኛን ያልገባን የአበበ መታገድ? ነው ወይስ ለወያኔዎች የሚገባቸው እንግሊዘኛ እና ለኛ የሚገባን እንግሊዘኛ ይለያል። እስኪ እንሳቅ። አቶ መለስ ሽንፈታቸውን ለማሸነፍ ብለው ቢያሰሩበትም ግን የተሸነፉበትን ቪድዮ አብረን እያየን አብረን እንሳቅባቸው። ቂ.ቂ.ቂ.ቂ.ቂ…
 | 

አበበ ገላው መልስ ሰጠ

(ዘ-ሐበሻ) ከሰሞኑ በወያኔ ሚዲያዎች በአበበ ላይ የተጀመረውን ዘመቻ በማስመልከት ጋዜጠኛው መልስ ሰጠ። አዲስ አድማስ ጋዜጣን ጀምሮ የተለያዩ የወያኔ ደጋፊ ሚድያዎች ስለ ጋዜጠኛው የተሳሳቱ መረጃዎችን ለሕዝብ በማድረስ ላይ መሆናቸውን አበበ “በጣም አሳፋሪ ነው” ብሎታል። አቶ መለስ ዜናዊ አንገታቸውን በአደበባይ ሲደፉ፤ ደጋፊዎቻቸው ጭምር የሚገበት አጥተው አንገታቸውን የደፉ ቢሆንም አንገታቸውን ቀና ለማድረግ 21 ዓመት ሙሉ የሰለቸንን ፕሮፓጋንዳቸውን በአበበ ላይ ቀጥለዋል። የአበበን ምላሽ እነሆ በቪድዮ፦
Short URL: http://www.zehabesha.com/?p=7683

ሳላዲን ጥቁር ሰው! አበበ ጥቁር ሰው! አስክንድር ጥቁር ሰው… እኛስ!? (አቤ ቶኪቻው)


 | 

ሳላዲን ጥቁር ሰው! አበበ ጥቁር ሰው! አስክንድር ጥቁር ሰው… እኛስ!? (አቤ ቶኪቻው)


የዛሬ ሳምንት ከደቡብ አፍሪካ ባፋና ባፋናዎች ጋር በሳላዲን ሰይድ ጎል አቻ ተለያይቶ መነጋገሪያ የነበረው ብሄራዊ ቡድናችን ትላንት ደግሞ አሁንም በማይጨበጠው አጥቂ ሳላዲን ሰይድ ሁለት ጎሎች አስቆጥሮ፤ ሁለት ለምንም በሆነ ውጤት መካከለኛው አፍሪካን አሸንፏል። በስታድየም፣ በቴሌቪዥን እና በኢንተርኔት ስንከታተል የነበርን በርካቶችም ፈንድቀናል።
ሳላዲን ሰይድም ከስታድየሙ ታዳሚ “ጥቁር ሰው” የሚል ማዕረግ ተሰጥቶታል። እንደውም አንድ የፌስ ቡክ ወዳጃችን እንዲህ ብሎ ለጥፏል።
“ብራዚል ሊሄድ ሳላዲን ኑ ካለ
አረ አይቀርም በኢትዮጵያ ስለማለ
ታድያ ልጁስ ሲጠራው ምናለ….
ወ….ይ…
ወይ ባለለው ያኔ
አዝናብኝ ነበር ሀገሬ”
እንግዲህ ሀገሩን የሚያኮራ የጀግና ስራ የሚሰራ ሁሉ በአሁኑ ግዜ “ጥቁር ሰው” የሚል ማዕረግ የሚያገኝበት ሁኔታ ነው ያለው! (እንዲህ ነው እንጂ የኔ ኢቲቪ አይሉኝም!)
እዝች ጋ ውድ ቴዲ መለኪያ ሰጥተከናል እና እግዜር ይስጥህ! ብለን ማመስገን ይገባናል። እውነቱን ለመናገር ራስህም “ጥቁር ሰው” ነህ ብዬ ደፍሬ ለመናገር እወዳለሁ። እንዴት…? የሚል ካለ ምንም እንኳ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ሚኒሊክ ሲባል ደማቸው ቢንተከተክም የመጣው ይምጣ ብሎ “ጥቁሩን ሰው” አሞካሽቷልና… እደግመዋለሁ ቴዲም “ጥቁር ሰው” ነው!

Monday 11 June 2012

ኢትዮጵያ ውስጥ ስካይፒ ወይንም ቮፕ መጠቀም 15 አመታት በህግ ያስቀጣል መንግስት ኔትዎርኮችን በሙሉ አገደ!


GOVERNMENT STEPS UP CONTROL OF NEWS AND INFORMATION ኢትዮጵያ ውስጥ ስካይፒ ወይንም ቮፕ መጠቀም 15 አመታት በህግ ያስቀጣል መንግስት ኔትዎርኮችን በሙሉ አገደ! 



SHARE THIS
TAGS
Share in top social networks!
Ethiopia’s only ISP, state-owned Ethio-Telecom, has just installed a system for blocking access to the Tor network, which lets users browse anonymously and access blocked websites. At the same time, the state-owned printing presses are demanding the right to censor the newspapers they print. Reporters Without Borders is very worried by these attempts to reinforce government control of news and information.
Danger that printers will censor newspaper content
Reporters Without Borders accuses the biggest state printer, Berhanena Selam, which almost has a monopoly on newspaper and magazine printing in Ethiopia, and other state owned printers, of trying to impose political censorship on media content before publication.
In a proposed “standard contract for printing” recently circulated by state printers, they assume the right to vet and reject articles prior to printing.

Sunday 10 June 2012

ለዳያስፖራ ኢትዮጵያዉያን በያላችሁበት!


ለዳያስፖራ ኢትዮጵያዉያን በያላችሁበት!

ዓመታዊዉ 29ኛ ዓመት የኢትዮጵያ የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል በዳላስ ቴክሳስ ከጁላይ 1 እስከ ጁላይ 7 ቀን 2012 ድረስ ይካሄዳል።
ይህንን በዉጭ አገር የሚገኙ የኢትዮጵያዉያን የጋራ መድረክ ለማፍረስ ጥቂት ግለሰቦች ያደረጉት ሙከራ ይታወሳል። ይሁን እንጂ፣ ተልእኮዋቸዉ ከሽፎ በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን (ESFNA) የበለጠ ተጠናክሮ ወጥቷል።
ሆኖም፣ በሼህ አላሙዲን ገንዘብ የሚተነፍሱ ግለሰቦች ዛሬም ቢሆን እርኩስ ተልእኮዋቸዉን ለመወጣት ከመሞከር አልታቀቡም።
ቡድኑ በአንጋፋዉ (ESFNA) ስም ላይ (ONE) በመቀጠል እኔ ነኝ “አንጋፋዉ” ለማለት የፈጸመዉ ተንኮል በፍ/ቤት ሳይቀር ተበይኖበት ስሙን እንዳይጠቀም ተገዷል። በዚህም ሳያበቃ፣ የሁሉም ኢትዮጵያዉያን የስፖርት ማሕበር አንድ (AESAONE) በሚል ስያሜ በዋሽንግተን ዲሲ ከጁላይ 1 እስከ ጁላይ 7 ቀን 2012 ድረስ የሰፖርት ፌስቲቫል አዘጋጃለሁ ብሎ ተነስቷል። አዘጋጅቻለሁ የሚለዉ ፌስቲቫል ቀናት፤ በዳላስ ከሚካሄደዉ የአንጋፋዉ ESFNA ታላቅ የሰፖርትና የባሕል ፌስቲቫል ዝግጅት ቀናት ጋር ተመሳሳይ እንዲሆን በማድረግ ያሰራጨዉ ጥሪ የቡድኑን መሰሪ ተልእኮ በግልጽ የሚያስረዳ ይመስለናል።

የጠፋው ትውልድ እና የታህሪር ናፍቆት – ተመስገን ደሳለኝ

 | 

የጠፋው ትውልድ እና የታህሪር ናፍቆት – ተመስገን ደሳለኝ


(ከርዕሰ ጉዳያችን በፊት ጥቂት ‹‹ስለ ጥቁር ሰው››)
ኢትዮጵያ ሀገሬ የአፍሪካ መገኛ ናት
የነፃነት አርማ የሉአላዊነት
ያናብስቶች ምድር የአርበኞች ተራራ
በአለም አደባባይ ግርማሽ የተፈራ
የጥበብ ምልክት የፍቅር ማደሪያ
ኑሪ ለዘላለም ቅድስት ኢትዮጵያ
ዳግማይ ምኒሊክ፣ ዳግማይ ምኒሊክ
ምኒሊክ፣ ምኒሊክ፣ ዳግማይ ምኒሊክ…
(እነዚህን ስንኞች ያገኘሁት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ‹‹ጥቁር ሰው›› ለተሰኘው ሙዚቃው የሰራውን የቪዲዮ ክሊፕ (ስዕል ለበስ ሙዚቃ) ከሁለት ቀን በፊት በሂልተን ሆቴል ባስመረቀበት መድረክ ከበርካታ አጃቢዎች ጋር ለበአሉ ድምቀት ይሆን ዘንድ ከዘመረው አዲስ መዝሙር ነው)
በዕለቱ በአዳራሹ የነበረው ድባብ እና ሀገራዊ መነቃቃት ልብን ከማሞቅም አልፎ ብርታትን የሚሰጥ ነበር። በዚህ በተዋጣለት ዝግጅት ላይ አባት አርበኞች በእንግድነት ከመገኘታቸውም ባሻገር፣ መድረክ ላይ ወጥተው የሀገር አንድነት ያስከበሩበትን ‹‹ወኔ ቀስቃሽ›› ፉከራ /ቀረርቶ/ ለታዳሚው አቅርበዋል። አባት አርበኞችን ባሰብኩ ቁጥር የሚገርመኝ ኢህአዴግም ሆነ የቀድሞዎቹ ሁለቱ መንግስታት አባት አርበኞችን ለፖለቲካ ትርፍ ካልሆነ በቀር በመንግስታቸው አስበዋቸው አለማወቃቸው ነው፡፡ ቴዲ አፍሮ ግን በግሉ አስቧቸዋል፡፡ የክብር እንግዳም አድርጎ ለውለታቸው ያለውን አክብሮት ገልጿል፡፡ ‹‹የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ›› ሲል ምን ማለቱ እንደሆነም የኋለኞቹን ወደፊት አምጥቶ ለማሳየት ሞክሯል፡፡