"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Wednesday 13 June 2012

ሁለት የወያኔ ባለስልጣናት በአ.አ ስታዲየም ለቡጢ ተገባበዙ




ተጠባባቂ ወንበር ላይ የነበሩት ጀግኖች ልጆቻችን
በብራዚል ለሚደረገው የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያና የመካከለኛው አፍሪካ ብሔራዊ ቡድኖች በአዲስ አበባ ስታዲዮም ባደረጉት ግጥሚያ መሀከል ክቡር ትሪቩን የተቀመጡ የወያኔ ባለሥልጣናት በቦክስ ለመደባደብ ተነስተው በዕለቱ የክብር እንግዳ ገላጋይነት ፀቡ መብረዱን በስፍራው የተገኙ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ምንጮች ገለፁ፡፡
የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ዘገባ እነሆ፦
ምንጮቻችን እንዳስታወቁት ድብድቡ በጠባቂዎቻቸውና በሥፍራው ለጥበቃ የተመደቡ ፖሊሶች ሊበርድ ባለመቻሉ የዕለቱ የክብር እንግዳ ተነስተው ፀቡ እንዲበርድ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በሥፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፁት በዕለቱ የውሃና ማዕድን ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ የእለቱ የክብር እንግዳ፣ የስፖርት ኮሚሽነሩ አቶ አብዲሳ ያደታ፣ የደደቢት ስፖርት ክለብ መሥራችና ፕሬዝዳንት ኰሎኔል አወል ኢብራሂም እና ሌሎች ባለሥልጣናት በእንግድነት ተገኝተው ነበር፡፡ ኰሎኔል አወል ከአቶ አብዲሳ ኋላ ተቀምጠው በስሜታዊነት ተውጠው እየጮሁ ተጫዋቾችን ‹ያዘው! ሩጥ! አቀብል› እያሉ ይጮሁ እንደነበር ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ አቶ አብዲሳ ያደታ ኮሎኔሉን ‹‹እባክህን ጆሮዬን አሞኛል አትጩህብኝ!›› በማለት ሲጠይቋቸው ኰሎኔሉም ‹‹ጆሮህን ካመመህ እዚህ ምን አስቀመጠህ? ሄደህ አትተኛም!›› በማለታቸው አለመግባቱ ተፈጠረ ይላሉ የአይን እማኞቹ፡፡
ስለ ዕለቱ ግጭትም ሲያብራሩም ‹‹አለመግባቱ ተካሮ ሁለቱም ለድብድብ ሲነሱ የባለሥልጣናቱ አጃቢዎችና በሥፍራው ለጥበቃ የተመደቡ ፖሊሶች ፀቡን ለማብረድ ቢሞክሩም ሊበርድ ባለመቻሉ
የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ አለማየሁ ተገኑ ተነስተው ገላጋይ በመሆናቸው ፀቡ ሊበርድ ችሎአል” ሲሉ ገልፀዋል፡፡

No comments:

Post a Comment