"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 6 July 2012

“የተማረ ይጥረበኝ” አለች ኮብልስቶን

 (አቤ ቶኪቻው)
እትዬ ፍዳዬንአየሁ ይባላሉ። በሽሮሜዳ አካባቢ ነዋሪ ናቸው። ዋና ስማቸው እንኳ ወርቅያንጥፉ ነበር። ነገር ግን ወርቅ አልተነጠፈላቸውም። ከባለቤታቸው አቶ ሃይለኛው ጋር ሲኖሩ አንድ ልጅ አፍርተዋል። የልጃቸው ስም እንደማንም የደሀ ቤተሰብ ልጅ ተስፋዬ ነው።
ያው እንደሚታወቀው፤ በምስኪን ቤተሰብ ውስጥ የመጀመሪያ ልጅ ሲወለድ የሚወጣለት ስም ተስፋዬ ነው። ምክንያቱም ቤተሰቦቹ ተስፋ የሚያደርጉት ከእግዜር ቀጥሎ ልጃቸውን በመሆኑ ነው።
እትዬ ፍዳዬን አየሁ እና ልጃቸው ተስፋዬ ባለቤታቸው አቶ ሃይለኛው በህይወት እያሉ እንደምንም ለእለት ጉርስ ለአመት ልብስ የማይቸገሩትን፤ እርሳቸው ከሞቱ በኋላ ግን የእነ ተስፋዬ ተስፋ አደጋ ላይ ወድቆ ነበር።
በዚህም የተነሳ ጎረቤት፤ “አሁንማ ጎርምሷል ሊስትሮ ሰርቶም ቢሆን ያግዝሽ እንጂ!” የሚል ሃሳብ ማቅረብ ቢጀምርም እትዬ ፍዳዬን አየሁ ግን “እምቢኝ እኔ በህይወት እያለሁ ልጄ ለስራ ሳይደርስ አደባባይ አይወጣም ተምሮ ጥሩ ደረጃ እንዲደርስልኝ ነው ምኞቴ” ብለው ወይ ፍንክች አሉ። እናም ያለ አባት የቀረው፣ ተስፋ ይሆነኛል ብለው ተስፋዬ ያሉት ልጃቸውን ምንም እንዳይጎድልበት ጥረት ማድረግ ጀመሩ።

የኢሕአፓ ወጣት ሊግ በባዶ ስታዲየም እየተደረገ ያለውን የአላሙዲ (ወያኔ) እግር ኳስ አዲስ ቪድዮ ለቀቀ

Thursday, July 5th, 2012 | Posted by zehabesha
የኢሕአፓ ወጣት ሊግ በባዶ ስታዲየም እየተደረገ ያለውን የአላሙዲ (ወያኔ) እግር ኳስ አዲስ ቪድዮ ለቀቀ

የኢሕአፓ ወጣት ሊግ በባዶ ስታዲየም እየተደረገ ያለውን የዲሲውን የአላሙዲ (ወያኔ) እግር ኳስ የሚያሳይ አዲስ ቪድዮ ለቀቀ። ቪድዮውን ለዘ-ሐበሻ ልከዋል፤ እንደሚከተለው አስተናግደነዋል።

Thursday 5 July 2012

Jah Lude the New Ethiopian Reggae Star



Jah Lude the New Ethiopian Reggae Star
Posted by admin on July 3, 2012 0 Comment


With a unique melody and ferocious singing style, Jah Lude is able to capture many people’s heart. Even though the album was recently released, he was able to get appreciation and admiration from many. Fans believe that with the new album, ‘Yachin Neger’, he has imprinted a new style in Ethiopian reggae music.

Since he is a new upcoming artist many fans are highly anticipating his concert and, as a response, a concert is going to kick off on July 7 at Lafto Mall. Entitled ‘Digis’ it will be the first concert after the album.
 “I want to reach many countries through art and this concert is a start”, is what Jah Lude said when he talked about representing Ethiopia, promoting the country, and that is why he chose reggae music to use it as a platform to pass the message.

Since the concert is going to be held after a week, his schedule has been also tight. With his band Zanta, they rehearse seven days a week starting from midday until midnight. Even though music has been part and parcel of his life when he spends quite a lot of time, he does not hide the fact these weeks have been pretty tight, but getting tired is not his thing. He says he sees music as some sort of enjoyment and that is why he fully immersed himself in doing music.

በማር የተለወሰ መርዝ (በኢቲቪው ዶኩመንታሪ ላይ ያተኮረ ሒስ)





በነስሩዲን ዑስማን (ከአዲስ አበባ)

‹‹ምን ያቀርቡ ይሆን?›› በሚል በጉጉት የጠበቅሁትን ‹‹አንዲት ሐገር ብዙ ሃይማኖቶች›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የኢቲቪ ዶኩመንታሪ በጥሞና ተከታተልሁት፡፡ የፕሮግራሙ ዓላማ አክራሪነትን ማውገዝ፣ የሃይማኖት መቻቻልን ማጎልበት ይመስላል፡፡

የኢቲቪ ዶኩመንታሪ ብዙ ጊዜ በሾላ ድፍን ‹‹አክራሪ ቡድኖች›› እያለ ስለሚያወሳ በትክክል ማንን ማለቱ እንደሆነ ወይም ማንን ዒላማ እያደረገ እንደሆነ ለእኔ ግልጽ አልሆነልኝም፡፡ ስለዚህም በዚህ ረገድ በአጠቃላይ የፕሮግራሙ ይዘት ላይ የማቀርበው ድፍን እና ጭፍን ተቃውሞ የለም፡፡ በፕሮግራሙ ላይ በቀረቡ ሰዎች የተሰጡ አስተያየቶችንም በፀጉር ስንጠቃ ደረጃ መተቸት አልፈልግም – ብዙ ሊተቹ የሚችሉ ሐሳቦች ቢኖሩም፡፡ ነገር ግን ላልፋቸው የማይገቡኝ የዝግጅቱ ግዙፍ ነውሮች እና ህፀፆችን በማያሻማ ቋንቋ ለመተቸት እፈልጋለሁ፡፡ ይህንን ለማድረግ የተገደድሁት እነዚህ ‹‹ግዙፍ ነውሮች›› እና ‹‹ሕፀፆች›› በማር የተለወሱ መርዞች ሆነው ስላገኘኋቸው ነው፡፡ ጽሑፌን በሦስት ርዕሶች ከፋፍዬ የማቀርብ ሲኾን እስከመጨረሻው ታነቡት ዘንድ እጋብዛለሁ፡፡ …

Wednesday 4 July 2012

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት የዋልደባ ገዳምን ለማፍረስ የተሰማሩ የወያኔ ቡል ዶዘር መኪኖችን ሙሉ ለሙሉ አጋየ።



ይህንን ተከትሎም መላው የአካባቢው ምዕመናን ለኢ.ሕ.አ.ግ ሰራዊት ያላቸውን አድናቆት እየገለጹ ይገኛሉ።

የአርበኞች ድምጽ፡ ቀድሞም ለሕዝቡና ለሀገሩ ሕልውና ሲል ውድ ሕይወቱን ቤዛ እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ከወያኔ መከላከያ፤ የፖሊስና ልዩ ሃይል ታጣቂዎች ጋር እልህ አስጨራሽ የሆኑ አውደ-ውጊያዎችን በመፈጸም የወገን ጥቃት መላሽነቱን በማረጋገጥ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል።

አናሳው የወያኔው ቡድን የገዳሙን ሕልውና መፈታተን ከጀመረበት እለት አንስቶ ከሃገሬው እስከ ውጭ ሀገር የሚኖረው መላው ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን የገዳሙን ሕልውና ለማስጠበቅ በጸሎት፣ በተቃውሞና ከዚህም ባለፈ የአካባቢውን ምዕመናን በስርዓቱ የማፈኛ ጣቢያዎችን በአስፈጻሚ የዳኝነትና የፖሊስ አባላት ላይ ቁርጠኝነት እርምጃዎችን እየወሰዱ ቢሆንም አምባገነኑ የወያኔው ቡድን ከጀመረው የጥፋት ተልዕኮ ሊታቀብ አለመቻሉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ይንን ተልዕኮ በአካባቢው ተሰማርቶ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም ወያኔ ገዳሙን ለማፍረስ ባሰማራባቸው ቡል ዶዘር መኪኖች ሙሉ ለሙሉ በማጋየት ለወራት ያህል አንጀቱ እያረረ የቆየውን የመላው ሕዝብ ክርስትያን ምዕመናን እምባ በማበስ ግንባሩን የሕዝብና የሀገር ተቆርቋሪነቱን ማስመስከሩ እንደቻለ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት ባለፈው ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም በወያኔ ተሽከርካሪ ዶዘር መኪኖች ላይ የፈጸመውን የማጋየት እርምጃ ተከትሎ መላው የአካባቢው ምዕመናን ለግንባሩ ሰራዊት ያለውን አድናቆት እየገለጸ ከመሆኑም ባሻገር ከግንባሩ ጎን በመሰለፍ ይህን ታሪክ አውዳሚ ስርዓት ለማስወገድ ከፍተኛ የሆነ ወኔና መነሳሳትን ፈጥሮልናል ሲሉ ብዛት ያላቸው ወገኖች እየገለጹ ይገኛሉ።

የኢሕአግ ሰራዊት የዋልድባ ገዳም ለማፍረስ በተሰማሩ ዶዘሮች ላይ በወሰደው የማጋየት እርምጃ የተነሳ ለዚሁ የማፈረስ ተልዕኮ የተሰማሩ ሹፌሮች በሁኔታው ተደናግጠው በመሸሻቸው ስራው ተቋርጦ እንደሰነበተም ለማወቅ ተችሏል።

በዚህ መሰረት ከፍተኛ ድንጋጤ የገባው የወያኔ ቡድን ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት የተወሰደበትን እርምጃና ኪሳራ በአፀፋ ለመመለስ በጀመረው እርምጃ ቁጥራቸው አራት የሚደርሱ የገዳሙ አባቶችን ጨምሮ ሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች አፍኖ ለጊዜው ወደ አልታወቀ እስር ቤት እንደወሰዳቸው የምንጮቻችን መረጃ ይጠቁማል።
 አናሳውና ጠባቡ የወያኔ ቡድን ከዚህ ቀደም የሕዝቡን የተቃውሞ ስሜት በመገንዘብ ብዛት ያለው የጦር ሰራዊት በገዳሙ ዙሪያ ያከማቸ መሆኑ ሲታወቅ ሰሞኑን ዳግም በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት የተወሰደበትን የጥቃት እርምጃ ተከትሎ ተጨማሪ ጦር ወደ አካባቢው በማጓጓዝ ላይ መሆኑን የአይን እማኞች አረጋገጡ።

እንደ ምንጮቻችን መረጃ ከሆነ በአሁኑ ሰዓት በዋልድባ ገዳም ላይ እየታየ ያለው ውጥረት ከምንጊዜውም በላይ እየበረታ መሆኑን ምንጮቹ ገልፀው የአካባቢው ምዕመናንም ወያኔ ከዚህ እኩይ ተግባሩ ካልተቆጠበና የታሰሩት የገዳሙ አባቶችና የአካባቢው ነዋሪዎችን እስካልፈታ ድረስ የጀመሩትን ተቃውሞ እንደሚገፉበትና መላው ኢትዮጵያዊያን ከጎናቸው እንዲሰለፉ ጥሪ እያደረጉ መሆኑን የምንጮቻችን መረጃ ያመለክታል።

Tuesday 3 July 2012

ዕሁድን በቃሊቲ – ከርዕዮት ኣለሙ ጋር“የሞትንም እኛ ያለንም እኛ”


Posted by admin on July 3, 20120 Comment

በጋዜጠኛ ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን (አዲስ አበባ)
ዕለተ ሠንበት ነው ፡- ዕሁድ፡፡ ሰኔ 17 ቀን 2004 ዓ.ም፡፡ ረፋዱ ላይ ከጥቂት የቀድሞው ነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ጓደኞቼ ጋር የሆድ የሆዳችንን ለማውጋት ተቀጣጥረናል፡፡
ስድሰት ኪሎ፡- ከአንበሳ ግቢ ትይዩ አምስት ያህል ካፌዎች አሉ፡፡ ሁሉም ካፌዎች ከቤታቸው ውጪ በረንዳቸው ላይ፣ ከበረንዳቸው አልፈው እስከ አስፋልቱ ጠርዝ ድረስ ባለዣንጥላ ጠረጴዛ ዘርግተው አገልግሎት ይሠጣሉ፡፡ በርካታ ተገልጋዮች አሏቸው፡፡
አብዛኞቹ ተስተናጋጅ ካፌው ውስጥ ዘልቀው ከመስተናገድ ይልቅ ውጪ መቀመጥን ይመርጣሉ፡፡ እኛም እንዲሁ ለአስፋልቱ ቀረብ ብሎ የተዘረጋውን ጠረጴዛ ከብበን ተቀምጠኛል፡፡ ቡናችንን አዝዘን ወግ እየጠረቅን ሳለ አንድ ጋዜጣ አዟሪ በክንዱ ከያዛቸው ጋዜጦችና መፅሔቶች አንድ አንድ መርጦ አቀበለን፡፡
Reeyot Alemu
እዚያ ቦታ አብዛኛው ተስተናጋጅ ከሻይ ቡና ባሻገር ከመፅሔትና ከጋዜጣ መረጃ ለመቃረም የሚመጣ መሆኑ ያስታውቃል፡፡ በየጠረጴዛው ጋዜጣ ወይም መፅሔት የማያነብ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ካፌዎቹ የላይብረሪ አገልግሎት ጭምር የሚሰጡ ናቸው ቢባል ግነት አይሆንም፡፡

Ethiopia Refining Internet Censorship

AP (Johannesburg) – The Committee to Protect Journalists says it appears Ethiopia is extending and refining its censorship of Internet news with a sophistication that could encourage other authoritarian regimes in Africa.
Prime Minister Meles Zenawi’s government has been blocking major news sites and blog hosts since disputed general election results in 2005 led to violent protests. Voice Over Internet Protocol such as Skype also is blocked, forcing people to use the state telephone system.
A CPJ statement Monday says “the rollout of a far morepervasive and sophisticated blocking system” started in April to include smaller blogs by exiles and news services, and even individual Facebook pages.
“The gap through which undetected, uncensored news gets in and out of Ethiopia is definitely narrowing,” encouraging similar action from authoritarian regimes such as Sudan.

በላሽው አንጀቴን በላሽው ጭር ባለው ሜዳ ዲሲ ላይ ያለሽው

  – ከአቤ ቶኪቻው
ከትላንት ወዲያ ጁላይ 1 ቀን 2012 የተጀመረው በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርት እና ባህል ፌስቲባልን በያለንበት ሆነን በፎቶም በቪዲዮም አይተነው ነበር።
በነገራችን ላይ ይሄ በርካታ አመታትን ያስቆጠረው አንጋፋ የፌስቲቫል ዝግጅት ESFNA በሚል መጠሪያ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ባለፉት ሰሞናት ከፍተኛ የይገባኛል ውዝግብ እና ክርክር ሲደረግበት ቆይቶ፤ ዛሬ ዳላስ ላይ የከተሙት ዋናውን ስያሜ ሲይዙ፤ በሼክ መሃመድ አላሙዲን የሚመሩት “ሃብታሞቹ” ደግሞ የፈጀውን ይፍጅ ብለው ESFNA የሚለው ላይ ONE የሚል ጨምረውበት የራሳቸውን ቡድን በማዋቀር ዲሲ ላይ ከትመው ነበር። (አክትመው ብል ይሻላል መሰለኝ… እንዴት? ማለት የጨዋ ደንቡ ነውና እንዴት ብለውኝ ይምጡ በአዲስ መስመር…)
ፌስቲባሉ በዳላስ እና በዲሲ እኩል ነበር የተጀመረው። በመጀመሪያ በዲሲ የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ፎቶግራፍ በፌስ ቡክ ላይ ተለጥፎ ተመለከትኩ። ስታድየሙ ባዶ ከመሆኑ የተነሳ የሚከራይ ቤት ነበር የሚመስለው። እውነቱን ለመናገር አንዱ ተንኮለኛ ዝግጅቱ ከመጀመሩ በፊት ሄዶ ባዶውን ስታድየም ፎቶ አንስቶ የለጠፈልን ነበር የመሰለኝ። ትንሽ እናጋነው ብንል፤ የዲሲ ስታድየም ራቁቷን የቆመች አዕምሮዋ የተናወጠ ሰው መስላ ነበር።

Welcome Dictator!


Welcome Dictator!
Published 02 07 2012                        Marielle Leraand
Ethiopia is a military dictatorship that persecutes and kills dissidents. People "disappear", imprisoned without trial and tortured in prisons. But Norwegian authorities close their eyes shut.

Former International Development Erik Solheim stressed the great economic progress Ethiopia has seen in recent years.

Yes, Erik Solheim, it is actually possible for a country to achieve economic growth of 11% a year without democracy. It is possible to see a thriving business, innovation and balance the state budget, while prisons and torture.

Human Rights Watch and Amnesty International has documented abuses against dissidents increases, and several of those Norwegian immigration authorities have cleared to return, the lists of the Ethiopian intelligence service. Despite these reports of gross violations of human rights and persecution of dissidents, it is unlikely to trouble the Norwegian government to break out of the West "block" and recognize that etparti State Ethiopia is not a leader.

Monday 2 July 2012

Who jailed Eskinder and the rest?


 By Yilma Bekele

July 2nd, 2012  Print   Email Goto commentsLeave a comment
The headlines screamed ‘Ethiopian court convicts 24 of terrorism charges’. As usual it was a misleading and incorrect statement. There is no such animal called Ethiopian court. There is a TPLF controlled judicial arrangement in Ethiopia. Prime Minster Meles and his politburo are the directors behind the scene of this farce. For the last twenty-one years they have been using the power of the state to marginalize, terrorize, demean and undermine the Ethiopian citizen. We are so used to their bullying the average Ethiopian does not even dwell on it. We make that peculiar noise with our lips you know that hissing sound and move on.

Our brothers Eskinder Nega, Andualem Arage, Wubshet Taye our sister Reyot Alemu and the others whose names are not publicized were convicted for exercising their right to speak and write freely. They only used their voice and their choice of weapon was the pen and paper. There was no evidence to show otherwise. Ato Eskinder has the audacity to speculate the chance of Arab Spring migrating to Ethiopia. Ato Andualem was simply trying to organize and recruit people to his legally recognized party. Reyot and Wubshet were doing their job as journalist and reporter. In any other country this is a normal and routine kind of job. But we are not like any other country or any other people. Our Ethiopia has always been different. Not only we got strange and bizarre leaders but we also have a different breed of people.

መንግስት የጠላው ህዝብ
ከዳዊት ዋስይሁን, ጁላይ 02\2012
ይህ የምትመለከቱት ፎቶ እየጸለዩ ለመሆኑ ምንም ማብራሪያ አያስፈልገውም፣
ታዩታላችሁና ነው፣ ነገሩ ግን እየጸለዩ ያለው የእምነት ተቋም ውስጥ ነው ብላችሁ
እንዳትደመድሙ፣ ወይም የተመቻቸ ቦታ ላይ ሆነውም አይደለም፣ አንድ አይነት
እምነትም የላቸውም፣ ክርስቲያን ሙስሊም ሌላም ሌላም ሆነው ነው የሚታዩት፣
ጸሉታቸውን የሚመራ የሃይማኖትም አባት የላቸውም ሁሉም ባንድነት ሆኖ ያነባል፣
ይቃትታል፣ ያለቅሳል ወደፈጣሪ።
እነኝህ ከሞት መንጋጋ የተረፉ ኢትዮጵያውያን ለነሱና ከጎናቸው ስለተለዩአቸው 43
ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ያለቅሳሉ ለኢትዮጵያም መከራና ስቃይ ኡኡኡ ይላሉ ቀይ
መስቀል ለጊዜው እንዲጠለሉበት ከሰጣቸው አዳራሽ ውስጥ ሆነው!!!!!!
በአለፈው ወራቶች ውስጥ ከሰማናቸው አስከፊ የወገኖቻችን ሰቆቃዎች መሃል
 በሰኔ 20፣ 2012, 60 ኢትዮጵያውያን በሌክ ማላዊ ውስጥ ሰምጠው መሞታቸው፣
 ንጹኃን እህቶቻችን በመካከለኛው ምስራቅ ለአስከፊ እንግልትና ውርደት መጋለጣቸው፣
 1700  በላይ የሚሆኑ የአገራችን ዜጎች በሳውዲ አረቢያ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ
መሆናቸው፣
 43  ወገኖቻችን ወደታንዛኒያ በኮንቴይነር ተጭነው ሲጓዙ በአየር ማጣት ታፍነው
በስቃይ ህይወታቸው ማለፉን፣
 ይህ አልበቃ ብሎን ከ50000  በላይ እህቶቻችን አሁንም ለባርነት በመንግስት ይሁንታ
ባለፈው ሁለት ወር ብቻ ወደ መካከለኛው ምስራቅ መላካቸው፣ይህ እንግዲህ የታየውንና የተሰማውን በጥቂቱ ለመጥቀስ በማሰብ ብቻ ነው ጉዳዩ ግን
ከምንገምተው በላይ ከመሆኑ የተነሳ ዛሬ ወገኖቻችን በየትኛውም የአለማችን ክፍል
በተበተኑበት ቦታ ሁሉ የመጀመሪያው የስደት መከራ ቀማሽ እየሆኑ ይገኛሉ።
ዛሬ የአለም አቀፍ ድርጅቶች መረጃ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያውያን አገራቸውን እየለቀቁ
በመሰደድ ግንባር ቀደም እየሆኑ መጥተዋል፣ ነገር ግን የኢትዮጵያ መንግስት በዛች አገር
ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እድገትና ለውጥ ማስገንዘቡን ህዝቡ ከመብላት አልፎ ሃብት
በሃብት መሆኑን በኢትዮጵያ የሚመረቱ ቁጥሮች ያሳዩናል።
የኢትዮጵያ መንግስት ቁጥርን በማምረት የሚወዳደረው የለም በሁሉም ዘርፍ ቁጥሩ
ትልልቅ ነው እውነቱ ግን የተገላቢጦሽ ነው። ከሰሞኑ አንድ የወያኔ ጽንፈኛ አቀንቃኝ
’’ለምን ቁጥር ይነግሩናል መለስ ዜናዊን አታለውታል ውነታው መርካቶ ሄዶ የጤፍና
የቅቤ ዋጋ መጠየቅ ነው ለምን መለስ ወረድ ብሎ ዞር ዞር ብሎ አይጠይቅም’’ በማለት
በተስፋ መቁረጥ ሲብከነከን ተስምቷል፣ እንግዲህ እውነቱን ራሳቸውም አልካዱት።
አንድ የሚጣረስ ነገር ይታየኛል ይህ ምናምን ፐርሰንት እየተባለ የሚነገረን ለማን ነው
እድገቱ ለህዝቡ ከሆነስ፣ ለየትኛው? ለምንስ ይሰደዳል?  ወይስ ለአቶ መለስ ቡድንና
ኃገሪቷን እየተቆራመቷት ላሉ ህንዶች፣ ቻይናዎችና አረቦች። ህዝቡማ በየቦታው ከቀየው
እየተፈናቀለ ጭሰኛ እና ስደተኛ እየሆነ በየደረሰበት ህይወቱን እያጣ ያለበት እውነታ ነው
የሚታየው።
ለምን አቶ መለስ አንዴ ረጋና ሰከን ብለው አያስቡም የዛች አገር ችግሯ ከቀን ወደቀን
እየከፋና ሁኔታዎች እየተወሳሰቡ እየሄዱ እንዳለ የፖለቲካ ተንታኝ መሆን አያስፈልግም
እዚህም እዚያም የመመረርና የአመጽ ምልክቶች ሲታዩ በመደብደብ፣ በማሰር እንዲሁም
በመግደል ለማፈን እየተሞከረ ነው በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአፋር፣ በጋምቤላ፣ በደቡብ፣
በኦጋዴን በሌሎችም የየለት ክስተት ከሆኑ ሰንበትበት ብሏል፣ ግን እኮ ይህ ሕዝብ የማን
ነው ለምንስ እንዲህ ሊጠላ ተፈለገ?  ያላሰቡበትና ያልተዘጋጁበት አደጋ ግን ሁሉም
በአንዴ በቃኝ ያለለት ውጤቱ የከፋ ይሆናል ለዚህም ነው ታላቁ መጽሃፍ ክፉ የሚባሉ
ቀኖች ሳይመጡ ….. ይላል፣
አሁን አልመሸም አብዮቱ ጎረቤት አገሮችን እያንኳኳ ነው ሰለዚህ ህዝብ ይደመጥ፣
ይከበር እንዲሁም ይወደድ፣ በኢንቬስትመንት ስም ህዝብ አይፈናቀል፣ የትውልድ ቅርስ
የሆነው የእምነት ቦታ አይነካ፣ የኃይማኖት ተቋማት ውስጥ የገቡ እጆች ይውጡ፣ በየስር
ቤት የታጎሩ ንጹሃን ዜጎች ይፈቱ፣ እርሶም በቃዎት ስልጣን ይልቀቁና ለህዝብ ያስረክቡ፣
በመቀጠልም መጽሃፍዎን ያንብቡ ካለበለዛ ይህ እድልም ሊያመልጥዎ ይችላል ያስቡ
ለዚህ ያልታደሉ አብዮቱ የበላቸው መሪዎች አሉና!!!
የሚገርመውና የሚያሳዝነው የተገለጠው እውነት የህዝቡ ድህነት፣ የመጎሳቆሉ መጠን
እንዲሁም ነጻነት የማጣቱ ጉዳይ ሲሆን፣ ነገር ግን ሁሌ ተቃራኒው ይነገረዋል። ምንያህል
እንደተንበሸበሸና እንደተትረፈረፈ፣ እንደፈለገ መሪዎቹን መምረጥ እንደሚችል፣ ኑሮውእንዴት እንደተቀየረ 24 ሰአት በኢቲቪ አላፊነት የጎደለው ፕሮፖጋንዳ ይጋታል ስለዚህ
በኢትዮጵያ ቴሌቪዢን ያለችው የበለጸገችውንና የተነገረላትን ኢትዮጵያ ፍለጋ ይሰደዳል።
መንግስት እንደመንግስት ህዝቡን የመጠበቅና የማስተዳደር አላፊነት ተጥሎበታል በዚህ
መስፈርት የአቶ መለስ መንግስት በተቋም ደረጃ የራሱን ህዝብ የሚጠላ፣ የሚዋሽ፣
የሚያስር፣ የሚገል እንዲሁም የሚያሰድድ ለመሆኑ ማጣቀሻ መስጠት አያስፈልግም ዜጎቹ
በገፍ ሲሰደዱ ምክንያቱ አጥንቶ ለዜጎቹ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ በመንግስት እቅድ
ተይዞ ዜጎች አገራቸውን ለቀው እንዲሰደዱ ይገፋፋል፣ ያበረታታል፣ ዜጎች በተሰደዱበት
ቦታ መከራና ስቃይ ሲበዛባቸው ቀድሞ ከመድርስና መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ
ተጠያቂነቱን ወደስደተኛው ወርውሮ አላስፈላጊ ስም ሲሰጥ ይታያል፣ ዜጎች በየትም ቦታ
አደጋ ቢደርስባቸው \ነፍስ ማጣትንም ያጠቃልላል\ የሚያስፈልገው መስዋእትነት ተከፍሎ
ላገራቸው ምድር እንዲበቁ ሲደረግ አይታይም ይልቁንም የፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ
ያደርጉታል፣ ታዲያ የአቶ መለስ መንግስት ለማን ነው የቆመው ወይስ ’’ሁሉም እኩል
ናቸው እንዳንዶች ከእኩሎች በላይ ናቸው’’ ነው ጉዳዩ?።
ጽሁፌን ሳጠናቅቅ በመላው አለም በግፍና በታላቅ ስቃይ ላይ ያሉ ስደተኛ ወገኖቼ
የመጽናኛችንን ግዜ እግዚያብሄር አቅርቦ ሁላችንም በአገራችን የሰላም አየር
የምንተነፍስበትን ግዜ በመመኝት ሲሆን በሌክ ማላዊ፣ በአረብ አገራት አንዲሁም
በታንዛኒያ የተከበረ ህይወታቸውን ላጡ በገኖቼ የህሊና ጸሎት በማድረግ ጭምርም ነው።
በተለይ በታንዛኒያ ህይወታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ያለፈው 43  ወገኖቻችን የቀብር
ስነስርአት ከሚናፍቋትና ከሚወዷት አገራቸው ውጪ፣ 22ቱ በሞርጎጎ ቀሪዎቹ በዶዶማ
ተከናውኗል በስነስርአቱም ወቅት ከአደጋው የተረፉ ወገኖቻችን የመረረ ሃዘናቸውን
በቁጭትና በለቅሶ ገልጸዋል፣ በዚህ በተጠቀሱ አደጋዎች ሁሉ የአቶ መለስ መንግስት
ዜጎቹን ለመታደግም ሆነ አደጋው ከደረሰ በኋላ አስፈላጊውን እርዳታ ከማድረግና ፈጥኖ
ከመድረስ ይልቅ እንዳልሰማና እንዳላየ የዜጎቹን ጉጋይ ከመጤፍ ሳይቆጥር ዝምታንና
ማሰደድን ስራዬ ብሎ ይዞታል።
ጸሃፊውን ለመገናኘት፦zoloaba112@yahoo.com

ኳስና ቅሪላ ፤ ሆድና ሕሊና


                                                  ኳስና ቅሪላ ፤ ሆድና ሕሊና
                                              ከቴድሮስ ሐይሌ(tadyha@gmail.com)
                                      ‘’መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥
                                     አሳባቸው ምድራዊ ነው ፥መጨረሻቸው ጥፋት ነው ።’’ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፥19
                                                  ዋሽቶ ለመኖር ልቤ አይችልም ከቶ፤ 
                                                      ታምኖ ይኖራል እንጂ ያለውን በልቶ። 
                                                   ደልቶኝ የሞላ ኑሮ መኖር ባልጠላም፤ 
                                                     ይህን ለማግኘት ብዬ እኔ አላጣም ሰላም ። 
                                                 …ሕሊና ሲያጣ ሰላም ወርቅ አልማዝ ሞልቶ ፤ 
                                                    ሳይተኙ መኖር ሊኖር  ከራስ ተጣልቶ ፤ 
                                                   አስኮንኛት ነብሴን እኔ አልሞላም ኪሴን!!! 
በሙያው የህዝብ ልጅነትን ከእድሜው በላይ መከበርን በሚሊዮኖች መፈቀርን በህፃን በአዛውንቱ መወደስን
የተቸረው ብላቴናው የሙዚቃው ኮከብ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከዚህ በላይ የቀረበውን ስንኝ ያዘለውን አስተማሪ
መንፈሳዊና መካሪ በሆነው በዚህ ዘፈኑ ላይ በሐሰት ከሚገኝ ገንዘብ ይልቅ የሕሊና ሰላም ምንኛ የተሻለ እንደሆነ ያሳየበት
ከቤተመንግስቱ እስከ ቤተክህነቱ በንዋይ ፍቅር የእውነትን ዋጋ በሚያቃልሉበት ሃብት ሞልቶ የተተትረፈለት ከበርቴ
ከረሐብተኛ ሕዝብ መከራ ላይ የበለጠ ትርፍ ለማጋበስ ከማፍያና ወንጀለኛ አገዛዝ ጋር ተባብሮ ወገኑን ሲያስጨቁን
የሚታይበትን ‘’ምን አይነት ዘመን ነው የተገላቢጦሽ አህያ ወደ እርሻ ውሻ ወደ ግጦሽ ‘’ አበው እንዲሉ የኛ የኢትጽያውያን
ሁኔታ እንደምሳሌው እየሆነ ያ የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ በሚል ከባድ የቃልኪዳንን አክባሪ ከነበረ ማሕበረሰብ
የፈለቀ ወገን

በዳላስ የኢትዮጵያውያን እግር ኳስ ውድድር በደመቀ ሁኔታ ተከፈተ





Sunday, July 1st, 2012 | Posted by zehabesha
በዳላስ የኢትዮጵያውያን እግር ኳስ ውድድር በደመቀ ሁኔታ ተከፈተ
80Share

(ዘ-ሐበሻ):- ለ29ኛ ጊዜ የሚደረገው የኢትዮጵያውያን የባህልና የስፖርት ፌስቲቫል በሰሜን አሜሪካ በዳላስ ከተማ በደመቀ ሁኔታ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት ተከፈተ። በዚህ ደማቅ የመከፈቻ ስነ- ሥርዓት ላይ ከአሜሪካ እና ከካናዳ የመጡት የ እግር ኳስ ቡድኖች ከፍተኛ አቀባበል ተደርጎላቸው ከሕዝብ ጋር ተዋውቀዋል።
 ከዳላስ ፎቶግራፎች ደርሰውናል ይመልከቷቸው፤ ቪድዮዎችም ይቀጥላሉ።
 ይህ በ እንዲህ እንዳለ በዳላስ በ29ኛው የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል ላይ የጋዜጠኞች እና የአርቲስቶች ቡድን እንደሚጋጠሙ ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል። ምናልባትም የጋዜጠኞ ቡድን መጠሪያ “እስክንድር ነጋ” ሊባል ይችላል እየተባለ ነው። የዘ-ሐበሻ ጋዜጣና ድረ ገጽ አዘጋጆች ለጋዜጠኞች ቡድን ተሰልፈው ይጫወታሉ።






Sunday 1 July 2012

Ethiopia.u.s state departmene daily press berifing , ethiopa


QUESTION: On Ethiopia, last night’s statement on Ethiopian conviction of journalists and political opponents under an anti-terrorism proclamation raised questions about the government’s intent for that proclamation. As you’ll recall, Prime Minister Meles was just here for the G-8 summit. Were those questions about the government’s intent of the anti-terrorism proclamation raised with him at that time? And if not, how does that fit into the concern that you have?

MS. NULAND: Well, as you say, he was a guest of the President for the G-8 summit, so with regard to what may have occurred in White House meetings, I’m going to refer you to them. But in the Secretary’s meetings with Ethiopian leaders, the whole question of press freedom, of creating and maintaining space for the political opposition, is always underscored, something that we raise at every turn.

QUESTION: Why host such a head of state whose government appears to pursue policies, at least according to your statement, directly at variance with what the United States would like to see in terms of freedom of the press and so on, at an event as high profile as the broader G-8 meeting? Why do that? I mean, don’t you try to exclude countries where you – North Korea doesn’t get invited to the G-8 meetings. Why have included them?

የዋልድባ ሰቋር ኪዳነ ምሕረት ገዳም በፌዴራል ፖሊስ ተከቧል፤ 4 መነኮሳት በፖሊስ ተወሰዱ


አራት መነኰሳት በፖሊስ ተይዘው ተወስደዋል፤ ሌሎቹ መነኰሳት እየተደበደቡ ተበታትነዋል።

የገዳሙ የሱባኤ ወቅት በፖሊስ የኀይል ርምጃ እየታወከ ነው።

በዛሬማ ወንዝ ላይ የሚገነባውን የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክትግድብ የሚሠራው ሱር ኮንስትራክሽን ለቆ መውጣቱ እየተነገረ ነው፤

በምትኩ የቻይና ተቋራጭ የገባ ቢኾንም በእርሱም ላይ ተቃውሞው መቀጠሉ ተሰምቷል።

(ደጀ ሰላም) በሰሜን ጎንደር ሀ/ስብከት ዓዲ አርቃይ ወረዳ የዋልድባ ሰቋር ኪዳነ ምሕረት ገዳም ከማይ ፀብሪና ዓዲ አርቃይ ወረዳዎች በአምስት መኪና ተጭነው በመጡ የፌዴራል ፖሊስ ኀይሎች ሥምሪት ውስጥ እንደሚገኝ የስፍራው ምንጮች ለደጀ ሰላም ገለጹ፡፡

ትናንት፣ ሰኔ 23 ቀን 2004 ዓ.ም፣ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ ገዳሙን በተቆጣጠረው የፖሊስ ኀይል አራት የገዳሙ መነኰሳት ተይዘው ወደ ወረዳው ፖሊስ ጣቢያ የተወሰዱ ሲኾን ሌሎቹ መነኰሳት ደግሞ ለሱባኤ (ሕርመት) ከተሰበሰቡበት በቆመጥ እየተደበደቡ መበታተናቸው ተጠቁሟል፡፡
ከአራቱ መነኰሳት መካከል ሦስቱ፣ አባ ኀይለ ኢየሱስ፣ አባ ግርማይ፣ አባ ገብረ እግዚአብሔር እንደሚባሉ ተረጋግጧል፤ የአራተኛውን መነኰስ ስም ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ማኅበረ መነኰሳቱን የማሳደዱ ተግባር ከገዳሙ ውጭም የቀጠለ ሲኾን ፖሊስ አባ ገብረ ሕይወት የተባሉ ሌላ የገዳሙ መነኮስን ለመያዝ በደባርቅ ከተማ አሠሣ እያደረገ መኾኑ ተገልጧል፡፡ የአሠሣው እና ስምሪቱ መጠናከር ምክንያት፣ ከግንቦት 22 ቀን አንሥቶ የዋልድባ ሰቋር ኪዳነ ምሕረት ገዳም ሴት መነኰሳዪያት፣ የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት በገዳሙ ላይ የሚያደርሰውን አካባቢያዊና ማኅበራዊ ጉዳት በመቃወም “ኑና ገዳሙን ተረከቡ፤ እኛ መሰደዳችን ነው” በሚል ለሕዝቡ ጥሪ ካስተላለፉ በኋላ በተለይም በዛሬማ ቀበሌና በእንዳባጉና ወረዳ ዲማ ቀበሌ እየተጠናከረ የመጣው የተቃውሞ እንቅስቃሴ መኾኑ ተመልክቷል፡፡

ዛሬ በአ. አ. ከሯጩ ቁጥር ይልቅ የፌደራል ፖሊሱ ቁጥር የማይተናነስበት የሩጫ ውድድር ተደረገ


 | 

ዛሬ በአ. አ. ከሯጩ ቁጥር ይልቅ የፌደራል ፖሊሱ ቁጥር የማይተናነስበት የሩጫ ውድድር ተደረገ


(ዘ-ሐበሻ)፦ ከፍተኛ የሕዝብ ድጋፍ እየከዳው ያለው የአቶ መለስ አስተዳደር ትናንሽ ድሎችን ለማጣጣምና የሕዝብ ድጋፍ አለን በሚል ራሳቸውን ለማታለል ከፍተኛ ወጪ በማውጣት በአዲስ አበባ ለአባይ ግድብ ድጋፍ በሚል የሩጫ ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ አደረጉ። 4 ሚሊዮን የተመዘገበ አባል አለኝ የሚለው ኢሕአዴግ በቀበሌ ካድሬዎቹ አማካኝነት፣ በየሰፈሩ ለእናቶች እና ለስራ አጥ ወጣቶች የቀን አበል በመስጠትና “ስራ ታገኛለህ፣ ብድር ይሰጥሃል፣ ከስራ ትባረራለህ” በሚል ድለላና ማስፈራሪያ ሕዝቡን ሰላማዊ ሰልፍ ቢያስወጡትም፤ በሰልፉ ላይ የተገኘው ሕዝብ ግን አራት ሚሊዮን አባል ካለው ድርጅት የሚጠበቅ አይደለም።
እንደ ዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ምንጮች ገለጻ ከሆነ የአቶ መለስ መንግስት የደረሰበትን የፖለቲካ ኪሳራ በትርፍ ለማካካስ የፈለገ ጥረት ቢያደርግም እየተሳካለት አይመስልም። “ሕዝቡ ጥርሱን ብቻ እንጂ ልቡን ለኢሕአዴግ እንዳልሰጠ በሰልፉ ላይም አሳይቷል” ያለው የዘ-ሐበሻ ምንጭ ዛሬ መንግስት በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኘው አብዛኛው ሕዝብ የወያኔ የፓርላማ አሻንጉሊቶች፣ የቀበሌ ካድሬዎችና በጥቅም የተደለሉ ወጣቶች ናቸው። በዚህ ዛሬ 10 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የ”እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን”ሩጫ ውድድር ላይ ከማረሚያ ቤት፣ ከፌደራል ፖሊስ የተውጣጡና በመንግስት ደመወዝ የሚከፈላቸው አትሌቶች ሳይወዱ በግዳቸው እንዲገኙ ተደርገዋል ያለው ምንጩ በዚህ ሰልፍ ላይ አልገኝም ያለ ማንም ሰው ለምን እንዳልተገኘ ሰኞ ጠዋት በሚሰራበት ቦታ ሪፖርት እንዲያቀርብ በካድሬዎች ማስፈራሪያ ተደርጓል። ሥራውን ቢያጣ ምን ሊሆን እንደሚችል የሚያስበው ሕዝብ ሳይወድ የግዱ በዚህ ሰልፍ ላይ ተገኝቷል።
በሩጫው ስፍራ ከፍተኛ ብጥብጥ ይነሳል በሚል ከሯጩ ቁጥር የማይተናነስ የፌደራል ፖሊስ ሩጫው የሚደረግበትን ቦታ አጥሮ እንደነበር የገለጸው ዘጋቢያችን፤ በሩጫው ላይ የተሳተፉትን አንዳንድ የክፍለከተማና የማዘጋጃ ቤት ባልሰልጣናትን ለማጀብም ስፍር ቁጥር የሌለው ሰምቶ አዳሪ (ሰላይ) በሩጫው እንዲሳተፍ መደረጉን ገልጾ ታዛቢዎች ሩጫው በመለስ ካድሬዎች የተደረገ እንጂ የኢትዮጵያ ሕዝብን ያማከለ አይደለም ብለዋል። ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ከቤት ውጭ ስብሰባን በተከለከሉበት ሃገር ኢሕ አዴግ ብቻውን ትናንሽ ድሎችን ፍለጋ ብዙ ወጪ አውጥቶ እንዲህ ያለውን ሰልፍ ማዘጋጀቱ ያስተዛዝባል የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች ይህ ሩጫ አላማውን የሳተ ነው ሲሉ ተችተውታል።
የመለስ መንግስት አባይ በሚል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ያነሳው ጥያቄ በህዝብ ዘንድ እንደ ድራማ የሚታይ በመሆኑ ይህን ድራማቸውን ለማሳመን የማይምሱት ጉድጓድ ባይኖርም ሕዝብ ከዝንብ ማር አይጠብቅም የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።
የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር አቶ በረከት ስምኦን የግድቡን ሥራ ለማቀላጠፍ በቅርቡ ከፍተኛ የግንባታ መሳሪያዎች ወደ ሥፍራው መንቀሳቀሳቸውንና ተጨማሪ የሰው ኃይል ተልኳል፤ ለዚህ ግድብ
ግንባታ ገቢ ለማሰባሰብ በሩጫው የተሳተፉ የፓርላማ አባላትን እና የመንግስት ባለስልጣናትን ማድነቃቸውን ተያይዞ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።