"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 27 February 2014

‹‹ ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል ››


ስለታክሲ ጥቅሶች ማውራታችን ካልቀረ እስቲ የታዘብካቸውንና ያነበብኳቸውንና ትንሽ ፈገግ ያደርጋሉ ያልኳቸውን ላካፍላችሁ፡፡

·    የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ·  ሠውን ማመን ተፈራርሞ ነው·  ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
·
   በቴሌቶን ሂሳብ መክፈል ክልክል ነው
·
   ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
·
   ለፀባይኛ ተሳፋሪ የፀባይ ዋንጫ እንሸላማለን
·   ለስራ ነው የወጣነው
·   በመጀመሪያ የጋለ ደምህን ተቆጣጠርና ሀሳብህን ግለፅ
·
    ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
·
   ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
· 
 ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
·   ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
·   ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
·   ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር
·  ሠው ብቻ ነው የምንጭነው በስህተት የገባ ይውረድ
·  ታክሲ ለሚጠቀሙ ብቻ 
·  ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ     አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል::
·  ለሠው ቅን ሁን እንጂ ቅንቅን አትሁን
·  ማስቲካ የሚታደል መስሎአችሁ አፋችሁን እንዳትከፍቱ
·  መስኮቱን በመክፈት ለትራፊክ ፖሊስ አያጋፍጡን!
·  ጤነኛ ካልሆኑ መውረጃዎ ደርሷል
·  በጭነት መኪና መታችሁ እዚህ ትቀናጣላችሁ
·  የክፍለ ከተማ ሠዎች ካላችሁ ሒሳብ በቅድሚያ
·  ኑሮአችሁ ሳይሞላ "ታክሲው አልሞላም?! " ትላላችሁ!·  ጥብቅ ማሳሰቢያ ለክቡራን ሌቦች ሒሳብ ሰብስበን ሳንጨርስ ስራችሁን 
መጀመር አትችሉም! የማይስማማ ሌባ ካለ መውረድ ይችላል፡፡
·  ለዓለም ሙቀት መጨመር መንስዔው ጭቅጭቅ ነው
·  ይህ ታፔላ የሚሉት ከመጣ ፤ ምሳችን በቆሎ ራታችን ቂጣ
·  ታክሲው ሳይቆም መውረድ ይቻላል፡፡
·   እንዴት ጭት አትቃሙ ይባላል፣ ሰርቶ የማይዝናና አህያ ብቻ ነው
·  የበታችነት ከተሰማህ ዛፍ ላይ ውጣ
·  ስልጣን ህዝብን ማገልገያ እንጂ ማስፈራሪያ አይደለም
·  የቤትህን አመል እዛው!!!
·  የሠው ትርፍ የለውም . . . ተጠጋጉ!
·  በታክሲ. . . . .  ህግ አላውቅም
·  ታክሲና መንግስተ ሰማያት ሞልቶ አያውቅም
·  ለታላቅ መልስ አይሰጥም
·  ነገን ለመኖር መጀመሪያ ዛሬን ኑር..በመቃም
·  ‹‹ደሀ›› ከፍ ብሎ የሚታየው ባስ ላይ እና እራሱን ሲሰቅል ብቻ ነው፡፡
·  እባክዎን የአባይ ቃል ስላለብን ጠጋ ጠጋ ይበሉልን
·  ለካፌና ለላዳ ብዙ ይከፍላሉ፤ እኛ ጋ ሲሳፈሩ ለምን ይጨቃጨቃሉ
በመጨረሻ
ተሳፋሪ፡- የሰጠከኝ ልክ አይደለም፤ሒሳብ አትችልም
" ? አልተማርክምደደብ . . . .
ወያላ፡- ጋሼ  ድንጋይ ለመጫን እስከ ሁለተኛ ክፍል መማር በቂ ነው

አበቃሁ፡፡

No comments:

Post a Comment