"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 17 January 2013

“ፍቅረኛሞቹ” አዜብና ብርሃነ – (ከኢየሩሳሌም አርአያ



አዜብ መስፍንን ከሱዳን አምጥቶ ሕወሓትን እንዲቀላቀሉ ያደረገ ነው። የፍቅር ግንኙነትም ነበራቸው። ይህ ሰው ብርሃነ ኪዳነማርያም (በቅፅል ስሙ ብርሃነ-ማረት) ነው። አዜብና ብርሃነ ድርጅቱን ሲቀላቀሉ የተቀበሏቸው አቶ አስገደ ገ/ስላሴ (አሁን የአረና አባል) ነበሩ። ጥቂት የበላይ አመራሮች በሁለቱ የፍቅር ግንኙነት ዙሪያ መከሩ። ከዛም የብርሃነና የአዜብ ግንኙነት እንዲቋረጥ በማድረግ ከለያዩዋቸው በኋላ ከመለስ ዜናዊ ጋር አዜብ እንዲጠቃለሉ ሆነ። (በነገራችን ላይ አንዳንድ ወገኖች አዜብና ሟቹ ክንፈ ገ/መድህን በጫካ ግንኙነት እንደነበራቸው ተደርጎ የሚነገረው ከእውነት የራቀ እንደሆነ የቅርብ ታማኝ ምንጮች ይገልፃሉ፤)
ወደ ዋናው ርዕሰ ጉዳይ እናምራ፥ በሕወሓት ውስጥ አድፍጠው መሰሪ ተግባር ከሚፈፅሙት አንዱ ነው ተብሎ በፓርቲው ወገኖች የሚፈረጀው ብርሃነ ኪ/ማርያም (ብርሃነ-ማረት) ማንነትና አደገኛ አካሄድ ምን እንደሚመስል ከላይ የተገለፀውን መንደርደሪያ ያስቀደሙ ታማኝ ምንጮች ተከታዩን ይላሉ።
ፓርቲው ወደ ስልጣን ሲመጣ አቶ ብርሃነ የተመደበው በመቀሌ ማዘጋጃ ሃላፊ ተደርጎ ነበር፤ መንግስት የከተማውን አስፋልት መንገድ ለማሰራት እንዲውል የመደበውን አምስት ሚሊዮን ብር « ቅርጥፍ» ያደርጋል። በወቅቱ የክልሉ ፕ/ት የነበሩት ገብሩ አስራት በወሰዱት እርምጃ ብርሃነ እንዲባረር ሲደረግ፥ ሁለት ግብረ-አበሮች የተባሉ ደግሞ ይታሰራሉ። የተባረረው ብርሃነ አዲስ አበባ ይመጣል። አዜብን ለማግኘት ብዙ ጥረት ካደረገ በኋላ ተሳካለት። ከዚያም አዜብ የቀድሞ « ፍቅረኛቸው»ን ለመታደግ ሲሉ ብርሃነ በሲቪል ሰርቪስ ኰሌጅ እንዲገባ ያደርጋሉ። ለረጅም አመት ድምፁን አጥፍቶ በኰሌጁ ቆየ። የኢትዮ- ኤርትራን ጦርነት ተከትሎ ለብርሃነ «ጥሩ» አጋጣሚ ፈጠረለት። ከቤተ መንግስት የማይጠፋ ሆነ፤ ከመለስ ጋር ቀን-ከሌሊት ምስጢራዊ ምክክሩ ቀጠለ። ታማኝና ቀኝ እጅ መሆኑን ለማሳየት በተግባር ተንቀሳቀሰ።
በ1993ዓ.ም ፓርቲው ለሁለት ከመሰንጠቁና ይፋ ከመውጣቱ በፊት « ጥንስሱን » ያውቁ የነበሩት አቶ መለስና ብርሃነ ነበሩ። ብርሃነ ታህሳስ 1993ዓ.ም ከፍተኛ ባጀት ተመድቦለት ወደ አሜሪካ መጣ፤ በወቅቱ በፓርቲው ውስጥ ገና ክፍፍል አልተፈጠረም፤ በተባራሪዋቹም በኩል የታወቀ ነገር አልነበረም። ብርሃነ በአሜሪካ ፥ ላስቬጋስ፡ ቴክሳስ፡ቦስተን፡ አትላንታ፡ ሲያትል…ከተሞች እየተዘዋወረ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ቅስቀሳ በማካሔድ በሕወሓት መከፋፈል መፈጠሩን በይፋ ለድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች ገለፀ። ጎን ለጎን ሰዎችን በመመልመል ከአቶ መለስ ጎን እንዲቆሙ አደረገ። በኢምባሲ የተመደቡትን ሳይቀር እያስፈራራና እየዛተ ድጋፍ እንዲሰጡ አዘዘ። በቅስቀሳው ላይ የሚባረሩትን፡ የሚታሰሩትን አመራሮች በስም እየጠቀሰና በስድብ እያብጠለጠለ ነበር ቅስቀሳውን ያካሂድ የነበረው። በተለይ የገብሩ አስራትን ስም በማንቑዋሸሽ… ዘመቻ አካሂዶዋል።« ግዳጁን » በአግባቡ በመፈፀሙ…የፓርቲው ማ/ኰሚቴ አባል ተደርጎ የተመረጠው ወዲያው ነበር።
በሙልጌታ አለምሰገድ ይመራ የነበረውንና በፓርቲው መሰንጠቅ ማግስት የተቋቋመው የፌደራል ደህንነት ቢሮን ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አንዱ የሆነው ብርሃነ፥ ተግባሩን ሲጀምር..የአፈናና ስቃይ ሰለባ ያደረጋቸው ከፓርቲው የተወገዱ አመራሮች – ጠባቂዎችን ነበር። የገብሩ አስራትን ጠባቂዎች (ታጋይ የነበሩ) ጨምሮ በጅምላ እንዲታሰሩ አደረገ። ግርማይ (ማንጁስ) ከተባለ የፌዴራል ፖሊስ ኮማንደር ጋር በቅንጅት ሆነው ጠባቂዎቹን በደም እስኪታጠቡ አሰቃዩዋቸው፤ እነ ገ/መስቀል የተባሉ የቀድሞ ታጋዮች እጅና እግራቸው በብረት ሰንሰለት ታስሮ ከተሰቃዩ በኋላ ወደ ትግራይ ተወስደው..በአደገኛ ቦዘኔነት ክስ እንዲመሰረትባቸው አደረጉ። በስቃይ ብዛት ገ/መድህን የተባለ ህይወቱ አለፈ። ለረጅም ወራት ታስረው ከተፈቱ በኋላ በመቀሌና ማይጨው የቁም እስረኛ ተደረጉ። ምንም ስራ መስራት አይችሉም፤ ወደየትም ስፍራ መንቀሳቀስና ሌላ አካባቢ መሄድ አይችሉም፤..ይህ ሁሉ በብርሃነ የተፈፀመ ነበር።
በሌላ በኩል ደግሞ የዚህን ሰው አደገኛና መሰሪ አካሔድና ተግባሩን ከማንም በተሻለ ጠንቅቀው የሚያውቁና የእርሱ ወጥመድ «ሰለባ» የሆኑ የቀድሞ የፓርቲው አመራር አባላት ምንም ትንፍሽ አለማለታቸውና አለማጋለጣቸው አስገራሚ ነው። ምክንያቱም እነዚህ አካላት በአገር ውስጥ እንዴት እንደታፈኑ ብቻ ሳይሆን ..በዚህ ሰው እንዴት እንደተሰቃዩ ያውቁታል፤ ያስታውሱታል…ሲሉ ምንጮቹ ትዝብታቸውን ሳይጠቁሙ አላለፉም።..
በውጭ አገራት የሚኖሩ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች ማንነትና የሚያራምዱት አቋም በተመለከተ መረጃ አለው። በተመሳሳይ በተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ደጋፊዎች ዙሪያ መረጃ ማነፍነፍ የየዕለት ተግባሩ ነው። በተለያዩ አገራት የሚመደቡ አምባሳደራት በዚህ ሰው ጥብቅ ክትትል ይካሄድባቸዋል። ሲፈልግ አምባሰደራቱን በስድብ እያብጠለጠለ ያስፈራራል። አንዳንዶች ደግሞ የፈጣሪያቸው ያክል « ጠብ እርግፍ » እያሉ ይሰግዱለታል። በአውሮፓና አሜሪካ ሲዘዋወር በአስር ሺዎች የሚቆጠር ዩሮና ዶላር ተመድቦለት ነው የሚንቀሳቀሰው።..( በነገራችን ላይ አሜሪካ-ዲሲ የከተሙ የብርሃነ ጋሻ ጃግሬዎች አሉ፤ አንዳንዶቹ በፖለቲካ አሳበው ጥገኝነት የጠየቁ ናቸው። ግን ስራቸው ፓርቲውን በምስጢር ማገልገል፡ በየጊዜው ኢትዮጲያውያንን እየሰለሉ ለብርሃነ መረጃ ማቀበል ነው፤ የአሜሪካ ዜግነት ወስደው ይህን እየሰሩ የሚገኙትን በተመለከተ በቀጣይ እመለስበታለው፤ ማንነታቸው ይጋለጣል።)…
.አደገኛው የፓርቲው ሰላይ ብርሃነ ከወራቶች በፊት በአሜሪካ በተከሰተው ሁኔታ ውስጥ ነበር፤ ይኸውም አቶ መለስ በተገኙበት ስብሰባ ላይ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ጠ/ሚ/ሩን ሲቃወም …ብርሃነ በአዳራሹ ነበር። ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ለጠ/ሚ/ሩ አጃቢዎች ትዕዛዝ ይሰጥ ነበር። ..
ከፓርቲው ሊቀመንበር ህልፈት በኋላ፥ ብርሃነ የፓርቲው የጀርባ « አጥንት » በመሆን ማሽከርከሩን ተያይዞታል። በተጨማሪ ከአሁኑ ጠ/ሚ/ር ጀርባ አድፍጦ የመሪነት ሚና መጫወቱን ቀጥሎበታል። በሌላም በኩል ሽማግሌው ስብሃት ነጋ በየመድረኩ የሚፈነጩት ያለምክንያት አይደለም፤ ይህን ሰው ይዘውና ተማምነው ነው። ምስጢሩ ደግሞ ሁለቱ ማለትም ብርሃነና ስብሃት በጋብቻ የተሳሰሩ በመሆናቸው ነው። በተጨማሪ የፌዴራል ደህንነት በፀጋይ በርሔ ነው የሚመራው ይባል እንጂ ከፍተኛ ሚና የሚጫወተው ብርሃነ ነው። ሁለቱም ከስብሃት ጋር በጋብቻ የተሳሰሩ ናቸው። …ሽማግሌው ስብሃት በአዜብ ዙሪያ « መፈንቅለ ኤፈርት » ደግሰው « ጥንስሱን » ተግባራዊ ለማድረግ ሩጫቸውን ገፍተውበታል። ..ብርሃነ በቀድሞ « ፍቅረኛው » ላይ የሽማግሌውን የሴራ በትር ያሳርፋል?…በቀጣይ የሚታይ ይሆናል፤..ብለዋል ምንጮች።
በሚቀጥለው መጣጥፍ.. በ40 ሚሊዮን ብር ህንፃ ስለተገነባለት የአዜብ ውሽማ…የምንለው ይኖራል፤

No comments:

Post a Comment