"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Wednesday 15 August 2012

(ሰበር ዜና) በኩክ የለሽ ማርያም ቤ/ክ አካባቢ በደረሰ ፍንዳታ ምእመናን ሞቱ


Share
(ዘ-ሐበሻ) ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ አሁን ከኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ደብረብርሃን ከተማ አካባቢ በተለምዶ ኩክ የለሽ ማርያም ተብሎ በሚጠራው ቤ/ክ አካባቢ ምንነቱ ባልታወቀ ፍንዳታ ለሱባዔ የገቡ ምዕመናን ሞቱ፤ በርከት ያሉ ሰዎችም እንደቆሰሉ የምንጮቻችን ዘገባ አመለከተ። ምንጮቻችን በኩክ የለሽ ማርያም አካባቢ የፈነዳውን ማን እንዳጠመደው እንዳልታወቀ ገልጸው፤ የሞቱት ሰዎች ቁጥርም እስካሁን እየተጣራ መሆኑም፤ የቆሰሉትም በርካታ እንደሆነ እንጂ ቁጥሩ ለጊዜው እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
የ16 የኪነምህረትን ጾም በማስመልከት በኩክ የለሽ ማርያም ቤ/ክ በርከት ያሉ ምዕምናን ከተለያዩ ቦታዎች በመጓዝ ሱባዔ የሚገቡ ሲሆን ይህ አደጋ መከሰቱ እጅጉን እንዳነጋገረ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ጠቁሟል።
አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች መንግስት ራሱ አፈንድቶ ከሙስሊሞች እንቅስቃሴ ጋር ለማያያዝ ያደረገው ሴራ ሊሆን ይችላል እያሉ ነው።
መረጃውን አጠናቅረን ጠለቅ ያለ ዘገባ ይዘን ለመቅረብ እንሞክራለን።  

No comments:

Post a Comment