"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Tuesday 5 June 2012

ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት


አዬ፤ ምነው እመ ብርሃን? ኢትዮጵያን ጨከንሽባት?
ምነው ቀኝሽን ረሳሻት?
እስከ መቼ ድረስ እንዲህ፤ መቀነትሽን ታጠብቂባት?
ልቦናሽን ታዞሪባት?
ፈተናዋን ሰቀቀንዋን፤ ጣሯን ይበቃል ሳትያት?
አላንቺእኮ ማንም የላት…እና ፈርቼ እንዳልባክን፤ ሲርቀኝ የሃይልሽ ውጋጋን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ፤ በርታ በይኝ እመ ብርሃን
ቃል ኪዳኔን እንዳልረሳት፤ እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን።
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ ተፈትቶ እንዳልከዳት ሰጋሁ…
ታዲያ ዛሬ ኢትዮጵያ ስትወድቅ፤ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በረኝነት ዕድሜ፤ ዓይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥንብ አንሳ ከንፎ፤ ወርዶ በጭለማ በርኖስ
ባክሽ እመ ብርሃን ይብቃሽ፤ ባክሽ ምስለ ፍቁር ወልዳ
ፅናት ስጪኝ እንድካፈል፤ የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ፤
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ፤ ከነደደችበት እቶን
የሷን ሞት እኔ እንድሞታት፤ ገላዋ ገላዬ እንዲሆን።…
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ።…  አቤቱ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ ሆይ!

No comments:

Post a Comment