"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Wednesday 28 November 2012

40ኛውን ዓመት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቲያትር በዓል በትንሹ ለመዘከር ቪዲዮውን ይመልከቱ

በእለቱ በዓሉን ለማክበር የተሰባሰቡት በጡረታ ላይ የሚገኙ አርቲስቶች በቃችሁ ተበለው ከመስራቤቱ የተገለሉ ሲሆኑ እድሜያቸው ቢገ ፋም ተወዛዋዦቹ  እንደ እንዝርት ሲሽከርከሩ መመልከት እጅግ በጣም መንፈስን የሚያስደሰትና የሚያዝናና  ነበር።  ያኔ ወጣት በነበሩበት ሰዓት ምን ያህል ያምሩ  ምን ያህል መድረኩን ያደምቁ  እንደነበር በጊዜው ለነበረው ተመልካች  ፍርዱን እተዋለው።ሙዚቀኞቹ በእውነት ነው የምለው እስካሁን ምትክ የሌላችው አንቱ የተባሉ ብዙ መስራት ማስተማር ሲችሉ እንደቀላል መሰናበታቸው በጊዜው በጣም ነበር የሚያገበግበው[ በጊዜው ስል ይህ ዝግጅት የቆየ  ስለሆነ ነው]ይህንን በዓል ካከበሩት ውስጥ  በአሁን ጊዜ  በህይወት የሌሉ ግን ይህ ስራቸው ታሪክ ሆኖ  ሁል ጊዜ ያስታውሳቸዋል።ለምሳሌ ያህል ከሌሉት ውስጥ 1ኛ ወዳጄነህ ፍልፍሉ ክላርኔትና አልቶ ሳክስ ተጨዋች 2ኛ አሰፋ ባይሳ  ትራምፔት ተጨዋች 3ኛ ጴጥሮስ መኮንን  ባሪቶን ሳክስና  አልቶ ሳክስ4ኛ  ዘነበች[ ጭራ  ቀረሽ]ድምጻዊ ተወዛዋዥና ተዋንያን 5ኛ ደስታ ገበሬ ተወዛዋዥ 6ኛ ብስራት አሰፋ  7ኛ ከተማ  መኮንን 8ኛ ገበያው ገሰሰ 9ኛ ጌታነህ  ሀይሌ  10ኛ ሽታዋ አዳሙ 11ኛ ወረስ ገብረ እግዜሀር .....ወዘተ  ብዬ ልለፈው ። ሌላው የባህል መሳሪያ ተጨዋቾች ፤ የባህል  ክፍል ተወዛዋዦች፤ የዘመናዊ የሙዚቃ   መሳሪያ ተጫዋቾች  ባጠቃላይ  በፊልሙ ላይ  ከምታዩዋቸው  ባለሙያዎች  አሁን ላለነው በበዙ መልኩ መስዋት በመሆን ያቆዩልን ሙያ ነው።በዛ ዘመን ለገንዘብ፤ ለነዋይ፤ለጥቅምና  አጎብድዶ ለመኖር ሳይሆን የሚሰሩት ለሙያቸው  ሲሉ ነው ።የቀጥላል

No comments:

Post a Comment