"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Thursday 3 January 2013

ትግላችን እና ፎቶዋችን


ቁ 1 የኖርዌ ፖሊስ የዋሸበት 
ቁ2 ጂ 20
ቁ1 ነገሩ እንደዚ ነው በእለቱ የኖርዌ ንጉስ በፓርላም በመገኘት ከሚኒስትሮች ጋራ የሚገናኙበት ቀን ስለሆነ  እሳቸውን ለመማጸን  እና መንግስት አልስማንም  እርስዎ ይስሙን ለማለት በጠዋት ሰብሰብ ብለናል።በፎቶው እንደሚታየው ጥቁር የሀዘን ልብስ ለብሰን አፋችንን በፕላስተር ሸፍነን የመናገር፧ የመጻፍ፧የመሰብሰብ ነጻነት በኢትዮጵያ የለም።ዲሞክራሲ፧ፍትህ፧ነጻነትና እኩልነት ሞቷል በማለት የሬሳ ሳጥን በመያዝ ዝም ብለን የሚያልፉበትን መንገድ  ዳሩን ይዘን  እንጠብቃለን ፤የኖርዌ ፖሊስ እኛ የምናደርገውን አጠገባችን በመሆን ይከታተላል፧ካሁን አሁን መጡ እያልን ስንጠብቅ ፖሊሱም ሰዓታቸው ደርሷል ብሎ ምልክት ሲያሳየን እኛም  እሱ ያለንን  አምነን  አይናችን ሲንቀዋለል ንጉሱ መንገድ ቀይረው ከጀርባችን ራቅ ብሎ ባለው ሌላ መንገድ እብስ አሉ።ሰልፉን ፖሊስ ነው የፈቀደው የቆምንበትን ቦታ  የሰጠን ፖሊስ ነው በዚህ ነው የሚያልፉት ብሎ ።ከፊታችን ስንጠብቅ ጀርባችንን አይተው ሄዱ። ያንን ሰልፍ የኖርዌ  ፖሊስ የዋሽበት ቀን በማለት አስታውሰዋለው።                                                                                     ቁ2   ጂ 26   መከራ ና ትግል አንድ ያደረገን፡የሚመጣውን ማንኛውንም ችግር  በጋራ ለመጋፈጥ ቆርጠን የተነሳን በአንድ የምንተነፍስ በአንድነት የምንራምድ።ያሰባሰበን ችግር ቢሆንም በአብሮነት ያሳለፍነው ጊዜ  ግን በፍቅር የተሞላ ነበር።ጂ20 የሚባሉት በሀብት የበለጸጉ ሲሆኑ ፤ጂ26 ደግሞ  በፍቅር የበለጸጉ ነበሩ።አንዱ የፍቅር ማሳያ  ፎቶው ላይ  እንደሚታየው  ባንዲራችን እንዲታይ ወጥረው የያዙት እናንተ  ተስተካክላችሁ ተነሱ  እኛ ባንዲራ መስቀያ እንሆናለን ብለው ቅድሚያውን ለብዙሀኑ ሲሰጡ።ትንሹዋ ምሳሌ  ነች ።በወቅቱ ትግላችን የነበረው ጨቋኝ እና ዘረኛ የሆነው የኢትዮ ጵያ  መንግስት በህዝቦቹ ላይ የሚያደርሰው ግፍና መከራ በዛ በተጨማሪ የኖርዌ መንግስት ገዳይ እና አረመኔ ለሆነው ለመለስ ዜናዊ አስተዳደር አሳልፎ  ሊሰጠን ነው አግባብ አይደለም የስደተኛ መብት አልተከበረም ለበዙ ዓመት በስራ ላይ በመቆየት  ግብር በመክፈል በህጋዊነት ስንሰራ  የቆየን  ነን  ስለዚ አስረው እንዳይመልሱን ችግራችንንም የዓለም ህዝብ ይወቅልን በማለት ወደ ስዊድን በመሄድ ድምጻችንን ያሰማን የበፊት ታጋዮች ያሁን ጓደኛሞች።                                                                                                                                                      ቁ3  የፍረሃት ቀን ያልኩት በፎቶው ላይ እንደምታዩት ፕሮግራሙ የሻማ ማብራት ስነስርአት ነው። ይህ  ፕሮግራም የኖርዌ  መንግስት ለእኛ የመኖሪያ ፍቃድ ለሌለን ኢትዮጵያውያን[ፓፒር ሎስ ወይም ኡሎቭሊ]  የመጨረዛው ቀን ነው።ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ  ፖሊስ ማጅራታችንን  እያነቀ  አንጠልጥሎ  ወደ ኢትዮጵያ  እንደሚመልስ እየፎከረ እያቅራራ  በተደጋጋሚ መግለጫ እያወጣ በኛ በምስኪን ስደተኞች ላይ ሽብር እያፈጠረ ነበር።ስለዚ አብዛኛው ስደተኛ ነገሩ እስኪጣራ በማለት በየ ዘመድ አዝማድ ለመደበቅ የሚኖርበትን መጠለያ[ካምፕ]በመተው ኦስሎ የተሰበሰበበት ቀን ነበር  ።ያም የፍርሃት ቀን አለፈ ። እኛም በፕሮግራሙ ላይ እንዲ በለን ዘምረን እንባችንን አፍሰን እግዛብሄርን ለምነን ነበር።ሀይል የእግዛብሄር ነው፤ማዳን የእግዛቤር፧አንመካም በጉልበታችን፤እግዛቤር ነው የኛ ሀይላችን።
ቁ4   አርያዎቻችን
 ቁ4 ጉዋዲት ገነት ግርማ ና ጉዋድ እያሱ አለማየሁ ሁለቱም  በትግል ለብዙ ጊዜ  እድሜያቸውን ማለት ይቻላል ብዙ መከራ ስቃይ ስደትና ችግርን ያሳለፉ፤ ለፍትህ ለዲሞክራሲ ለእኩልነትና ለህዝቦች ነጻነት ሲሉ የታገሉ አሁንም እየታገሉ ያሉ እውነተኛ ኢትዮ ጵያዊ ናቸው።አንድ ነገር ልበል በዛ የመከራ ወቅት የኖርዌ መንግስት አላስቆም አላስቀምጥ ብሎ ከዛሬ ነገ ያዘን ወደ ነብሰ በላው የወያኔ  መንግስት አሳልፎ  ሰጠን ብልን  በተጨነቅንበትጊዜ በኖርዌ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሰደተኞች በደል እየተፈጸመባቸው ነው።ወደ አረመኔው  የወያኔ መንግስት አስረው ሊልኳቸው ነው።በማለት ጄኔቭ በሚገኘው  የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ላይ ችግራችንን አንስተው የተከራከሩልን እውቅ  ታጋይ ናቸው።

No comments:

Post a Comment