"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Tuesday 13 November 2012

“ወይ መዓልቲ” አለ ያገሬ ሰው!

    

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አባል ሀገር ሆና ተመረጠች።
የትኛዋ ኢትዮጵያ!? የትኛው ሰብአዊ መብት!? የትኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን!?
እኔ የምለው ኢትዮጵያዊው የዩልኝታ ባህላችን ያለው ህብረተሰቡ ዘንድ ብቻ መሆኑ በጣም አሳሳቢ ችግር አይመስላችሁም? እንዴ መንግስት እኮ ይሉኝታ ቢኖረው ኖሮ “ተመድ የሰባዊ መብት ኮሚሽን አባል አድርጌ መርጨሀለሁ!” ሲለው… “አረ በህግ አምላክ እኔ አልሆናችሁም ሀገር ተሳስታችሁ ነው! ወይ ደግሞ ባታውቁኝ ነው የመረጣችሁኝ…!” ማለት ነበረበት። ነገር ግን መንግስቴ “ምን ይሉኝ” ያልፈጠረበት ነውና አሜን ብሎ መቀበሉ ሲገርመን፤ ጭራሽ በአደባባይ “እንዲህ ነን እኛ ሰብአዊ መብት ጠባቂዎች” ተብሎ ተነገረን!ኢቲቪ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታማሚ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አማካይነት፤ “ድሮውንም እኛ ለሰብአዊ መብት ጥበቃ ዘብ የቆምን ሰዎች ነን!” ብሎናል።
አቶ ዲና በሚወዱት ይማሉልኝ የሚናገሩት የምርዎትን ነው!? ከማሉልኝ ዛሬ ነገ ሳልል ሀገሬ እመጣለሁ። እኔ ብቻ ሳልሆን ሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰቱን ፈርቶ የወጣው ኢትዮጵያዊ ሁሉ “ምን አለኝ ሀገሬ” (“ለ“ን አጥብቆ) ዘፍኖ እንደወጣው ሁሉ፤ “ምን አለኝ ሀገሬ” በሚል “ለ”ን አላልቶ ዘፍኖ ይመለሳል። ግን እርግጠኛ ነኝ በሚወዱት አይምልሉንም! ለመሆኑ የሚወዱትስ አለ…!? ወይስ ነፍስ ይማር እንበልልዎ!?
የምር ግን ሰብአዊ መብት ማለት ምን ማለት ነበረ!?
“ወይ መዓልቲ” አለ ያገሬ ሰው!     አቤ ቶክቻው 

No comments:

Post a Comment