"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Saturday 2 February 2013

Artist Abebe Melese አበበ መለሰ ህይወቴን ታደጔት ድረሱልኝ ይላል

 


ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ ብዙ የኢትዬጵያ ሙዚቃዎች ጀርባ ሁልጊዜ ስሙ ይጠራል። በ1970 ዎቹ እና 80 ዎቹ ከተሰሩ ሙዚቃዎች የአብዛኞቹ የዜማ ደራሲ ነዉ ቢባል ማጋነን አይሆንም።
abebe melese
Account number: 1000033097453
Owners: Tsegaye Eshetu and Hailye Tadesse and Dawit Yifru
Commercial Bank of Ethiopia, Finfine Branch, Addis Ababa
Swift code: CBETETAA
Tele: +251115518844
ከ ሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑ የዜማ፣ ግጥምና ቅንብር ስራዎች ባለቤት አበበ መለሰ።
ለተወዳጆቹ ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ኤፍሬም ታምሩ፣ አስቴር አወቀ፣ ቴዎድሮስ ታደሰ፣ አረጋሃኝ ወራሽ፣ ኬኔዲ መንገሻ እና ለአያሌ ሌሎች ድምፃውያን በሳል የዜማና የግጥም ስራዎችን አበርክቷል።
በሁለት አስርት አመታት ውስጥ ሁለት ሺህ የሚደርሱ የዜማ፣ የግጥም እና ሙዚቃ ቅንብር ስራዎችን ሰርቶ በኢትዬጵያ ሙዚቃ ውስጥ የማይረሳ አሻራውን አሳርፏል።
እነዚህን ዘመን የማይሽራቸው ሙዚቃዎችን አምጦ ሲወልድ ለከፋ የደም ግፊት በሽታ በመጋለጡ የጥላሁንን ‘ኢትዬጵያ’ ስራ ከሰራ በኋላ የዜማ ስራ እንዳይሰራ በሀኪም ትዕዛዝ ከሙዚቃ ስራ ለረዥም ጊዜ ተገሏል።
በአሁኑ ሰዓት አበበ ከፍተኛ የጤና ቀውስ ላይ ይገኛል ሁለቱም ኩላሊቶቹ አገልግሎት በማቆማቸው በህይወት ለመቆየት በሳምንት 3 ቀናት አርቲፊሻል የደም ማጣራት (Dialysis) ማድረግ ግድ ሆኖበታል።
አበበ በአሁኑ ጊዜ የኩላሊት ተከላ መቀበል ይችላል። ነገር ግን ህክምናዉን ለማድረግ አንድ መቶ ሃምሣ ሺህ የአሜሪካን ዶላር (150,000.00 USD) ያስፈልገዋል። አበበ ህይወቴን ታደጔት! ድረሱልኝ! ይላል።
አበበን ህይወት ለመታደግ ሁላችንም የበኩላችንን ጥረት እንድናደርግ!!!
source : bawza ድረገፅ

No comments:

Post a Comment