"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 23 November 2012

በምስራቅ ኢትዮጵያ ከባድ ዉጊያ እየተካሄደ ነው!



አምባገነኑ የወያኔ መደብ ለአመታት በኬንያ መሽጎ ድርድር ሲያደርግበት የነበረው ውይይት ከተኮላሸ በኋላ በምስራቅ ኢትዮጵያ ከባድ ዉጊያ እየተደረገ መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ምንጮች ጠቆሙ::

በኦጋዴን ቀላፎ እና ጎዴ በሚባሉ ቦታዎች የታጠቁ ሃይሎች  በወያኔ ወታደሮች ላይ በከፈቱት ድንገተኛ ጥቃት ከባድ ጥፋት አድርሰው መሰወራቸዉን የገለጡት እነዚህ ምንጮች ወያኔ በምክር ቤቱ አሸባሪ እያላቸው የሚከሳቸዉን የኦብነግ አባላት  ከህዝብ ተደብቆ ሲደራደር ከቆየ በሁዋላ ድርድሩ መክሸፉን ተከትሎ የተነሳው ዉጊያ ማብረጃ አላገኘም ሲሉ ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ተናግረዋል::

ለቀጠና ጥበቃ በተሰማሩ የወያኔ ወታደሮች ላይ የተደረገውን ጥቃት የቀሰቀሰው ውጊያ በጦሩ ላይ ለደረሰው ጥቃት ተጠያቂ ናችሁ ተብሎ መስመራዊ የጦር መኮንኖች ወደ እስር ቤት ተልከዋል;

በጦሩ ላይ ለደረሰው ጥቃት ራሳቸዉን ነጻ ማድረግ የፈለጉት የምስራቅ እዝ የጦር ኣዛዥ አብርሃ ወ/ማርያም እና ተከታዮቹ ግንባር ላይ ተሰልፈው የነበሩትን መስመራዊ የጦር መኮንኖች ጥፋተኛ በማድረግ ከያሉበት ተለቅመው ሐረር ከተማ በሚገኘው የምስራቅ እዝ ዋና ማዘዣ በሆነው እስር ቤት ዉስጥ መታሰራቸውን ምንጮቹ ተናግረዋል::

በምስራቅ እዝ ዋና አዛዥ የሚመራ አንድ ግብረ ሃይል/ቡድን/ ተቋቁሞ እነዚህን የመስመር መኮንኖች ለመዳኘት እና የጥፋተኝነት ዉሳኔ ለመስጠት በስራ ላይ መሆኑን ዉስጥ አዋቂ ምንጮቹ አመልክተዋል::

No comments:

Post a Comment