"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Sunday 23 September 2012

የቴዲ አፍሮ ሰርግ ለምን ባልተመለደ መልኩ ሐሙስ ቀን እንዲሆን መወሰኑን ያውቁ ኖሩዋል




የቴዲ አፍሮ ሰርግ ለምን ሐሙስ ቀን እንዲሆን ተወሰ? (ያውቁ ኖሩዋል?)
የቴዲ አፍሮ ሰርግ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚደረግ ዘ-ሐበሻ መዘገቡዋ ይታወሳል:: የቴዲ ሰርግ የፊታችን ሐሙስ በሒልተን ሆቴል ሲደረግ 1000 ሺህ ሰዎች የሰርግ ካርድ ተልኮላቸዋል:: ለሰርጌ በሚል የዛሬ 5 ዐመት የሰራውና ለሰርጌ ቀን ብሎ ያስቀመጠው የሰርግ ዘፈን በዚሁ ቀን ይደመጣል:: ይህ ዘፈን ዛሬ በአዲስ አበባ ለአድማጭ መልቀቁ ለዘ-ሐበሻ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::
ከዚህ ውጭ የቴዲ አፍሮ ሰርግ ባልተለመደ መልኩ ለምን ሐሙስ ቀን እንዲሆን መወሰኑን የቅርብ ምንጮች ለዘሐበሻ መረጃውን አድርሰዋል::
መስከረም 17 እና ቴዲ ብዙ ታሪክ አላቸው:-
1ኛ. የመስቀል በዐል ስለሆነ
2ኛ. አባቱ የተቀበረበት ዕለት ስለሆነ
3ኛ. የቴዲ እናት ልደት ነው
4ኛ. የእውቁ ድምጻዊ የዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ልደት ስለሆነ ነው::
ከቴዲ ሚዜዎች መካከል ሸዋንዳኝ ሀይሉ; የቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ቴዲ ባሪያው; ሀይልዬ ታደሰና የእውቋ ሞዴል ሊያ ከበደ ወንድም ኤርሚያስ ከበደ ይገኙበታል:: በአጠቃላይ ከቴዲ በኩል ሰባት; በሚስቱም በኩል 7 ሚዜዎች ይኖሩዋቸዋል:: ከአምለሰት ሚዜዎች መካከል የኤፍሬም ታምሩ ልጅ ቤዛ ኤፍሬም ታምሩ እንደምትገኝበት የዘ-ሐበሻ ምንጮች መረጃውን አድርሰውናል::
የቴዲ የሰርግ ዘፈን ደርሶናል፤ ቀጥሎ ይቀርባል።

No comments:

Post a Comment