"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Friday 28 September 2012

ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ታፍኖ ቆየው ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈውን የሙከራ ስርጭት ጀምሯል።



564188_201743973292815_1901961_n
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሙከራ ስርጭት ጀመረ መስከረም ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በገዢው ፓርቲ አፈና ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ታፍኖ ቆየው ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈውን የሙከራ ስርጭት ጀምሯል። ከኒው ሆርን ቴሌቪዥን የአየር ስርጭት በመግዛት በሚቀጥሉት ቀናት ሙሉ ስርጭቱን የሚጀምረው ኢሳት፣ በቅርቡ ተጨማሪ የራሱ ሙሉ የስርጭት ጊዜ
ይኖረዋል። አዲሱ ስርጭት በኤ ቢ 7 በ7 ዲግሪ ዌስት ላይ በ 10815 ሜጋ ሀርዝ፣ በ27 ሺ 500 ሜትር ባንድ ሲምቦል ሬት፣ በ5 ስድስተኛ
ኤፍ ሲ ይተላለፋል። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ናይል ሳትን በመክፈት ስርጭቱን በቀላሉ ለማግኘት ይችላል። ተጨማሪ መግለጫዎችን ሙሉ ስርጭቱ
እንደተጀመረ እንሰጣለን።ባሳለፍነው አመት በአቶ መለስ ዜናዊ አገዛዝ የኢሳት ቴሌቪዥን ለሃገሪቱ ይሰጥ የነበረው የአገልግሎት ስርጭት በአሸባሪነት በመወንጀል  ስርጭቱን እንዲታፈን ማድረጋቸውን በተለያዩ የመረጃ  ተቋማት  መዘገቡን ይታወሳል ሆኖም የኢትዮጵያ መንግስት በሃገሪቱ የሚያደርገውን የመረጃ አፈና ከጊዜ ወደጊዜ እየቀጠለ በመምጣቱ  ብዙ የነጻ ጋዜጦችም ባሳለፍነው አመት መዘጋታቸው እርግጥ ነው ።በዚህ ሳምንት በተጀመረው  ዘመቻ ነጻነት በሚለው የመረጃ መለዋወጥ ሃሳብ ነጻነትን የሚያራምድ አቋም በሃገሪቱ እንዲያንሰራፋ በማለት በነጻነት ጋዜጣ አሳታሚዎች መጀመሩን የደረሰን ዘገባ ያመለክታል ።በተለይም ለማለዳ ታይምስ የደረሰው ወቅታዊ መረጃ በኢትዮጵያ ውስጥ የኢትዮጵያኖችን የመረጃ ማእከሎችን ብቻ ሳይሆን ከግብጽ እና ከኢንዶኔዢያ እየታተመ በዌብሳይት መገናኛ ስርጭት ላይ የዋለውንም ቢኪማሳር የተሰኘውን ዌብሳይት መዝጋታቸው የሚታወቅ ሲሆን ይህንን ዌብሳይት የሙስሊሞችን ወቅታዊ ጥያቄ በተከታታይ ሲዘግብ በመገኘቱ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታይ ማድረጋቸው ይታወቃል ሆኖም ግን ይህንን አስመልክቶ እና በስውድናውያን ጋዜጠኞች ጥያቄ እና መልስ ላይ ከፍተኛ ትኩረትን ወደ ኢትዮጵያ መንግስት ያደረገው ይሄው ሚዲያ አሁንም ድብቁን ሚስጥር ከመናገር ወደኋላ አንልም ሲሉ ሃተታቸውን በትላንትናው እለት አስፍረዋል  በዚህም ዘገባ ተከፈተ ወይንም አየር ኦን የሚል ፎቶ በመለጠፍ ሪፖርታቸው በመገናኛው ሽፋን ላይ ያተኮረ ዘገባ አትተዋል። ሆኖም የአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር የዚህ መረጃ ማእከል ለዘብተኛ ሆነው ሁሉንም የመረጃ ድርጅቶች ክፍት ያደርጋሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የህትመት ዋጋዎችን እና የደህንነት ሚንስቴር የግል ሚዲያዎችን ክትትላቸውን እንዲያቆሙ ያሳውቃሉ ተብሎ የሚጠበቁ ሰው መሆናቸውን እና የነጻነት አርአያ ይሆናሉ ተብሎ ይገመታሉ ። ለዚህ ደግሞ ትልቅ እና ፈታኝ ስራ ይጠብቃቸዋል ።መረጃዎች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ ይፈሳሉ አፈና ሁሉ ይቅር ይላል የማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል ።

No comments:

Post a Comment