"Food is nothing without freedom! We Need Freedom

”Food is nothing without freedom! We Need Freedom!

Monday 25 June 2012

“ሰይጣን አሳስቶኝ ነው” የሚለው ምክንያት አምባገነን ወያኔዎችን ከተጠያቂነት አያድናቸውም


 ከአሰግድ ታመነ




Share This




ከአሰግድ ታመነ

የጥንት ታሪክ ነው። በሩስያ ውስጥ በጭካኔውና በአይለኝነቱ የሚታወቅ ጄኔራል ነበር። ታዲያ አንድ ህፃን በግቢው ሲያልፍ የጄኔራሉ ድንክ ውሻ ስትጫወት ያያታል ድንጋይም አንስቶ ሲወረውር የውሻዋን እግር ይሰብራታል። ጄኔራሉም ከስራ ሲምለስ ውሻው ስታነክስ በማየቱ ጠባቂዎችቹን ጠርቶ ማን እንደሰበራት በከፍተኛ ቁጣና ጩኸት ጠየቃቸው።
 በአካባቢው ያለ አንድ ህፃን ነው ጌታዬ ድንጋይ ወርውሮ የሰበራት ይሉታል።
 በሉ ይኽን ህፃን በፍጥነት ከእናቱ ጋር አምጡልኝ ይላል ጄኔራሉ በቁጣ።
 ጠባቂዎቹም እንደታዘዙት ያመጧቸውና በጄኔራሉ ፊት ያቆሟቸዋል ህፃኑ በእናቱ እቅፍ ውስጥ ልመደበቅ የሚሞክር ይምስላል ደንግጠዋል ስል ጭካኔው በደንብ ያውቃሉና።

ልጁን እንድታወርደው የተነገራት የህፃኑ እናት እባክህ ጌታዬ ህፃን ልጅ ነው ምንም አያቅም የዛሬን ብቻ ማርልኝ ብላ ብትማፅነውም ከእጅዋ ላይ መንጭቆ ህፃኑን ካወረደ በኻላ ልጁን በሚያስፈራ ድምፅ ከዚህ ሩጥ ይልዋል::
 ያ ቲኒሽ ልጅ ምክንያቱ ሳይገባው የሚያሳዝን አይኑን ወደ እናቱ አንዴ ደሞ ወደ ጄኔራሉ ቢያቁለጨልጭም የሚረዳው በማጣቱ በዝያች እግሩ መሮጥ እንደ ጀመረ አዳኝ ውሾች ይለቅበትና ብዙም ሳይሔድ ዘነጣጥለው ይበሉታል።


ታድያ ይህ ጨካኝ ጄኔራል በህዝቡ ላይ የሚፈፅመው ግፍ ይበረታና በህዝባዊ አመፅ ከስልጣን ይወገዳል የተበደሉ ሰዎች እስር ቤት ሄደው ለምን እንዲህ እደረግክ ብለው ሲጠይቁት ስይጣን አሳስቶኝ ነው አለ ይባላል።

በ21 ዐመት የመለሰ ዜናዊ አገዛዝ ያላየነው ግፍና መከራ የለም ብዙ ህፃናት በየትምህርት ቤታቸው ደጃፍ ላይ ተገለዋል በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ በኦሮሚያ በአማራ በደቡብ በኦጋዴንና በ ጋምቤላ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋዎች በዚሁ የወያኔ መሪ መለሰ ዜናዊ ትህዛዝ ተፈፅመዋል።

የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር የነበረው ታምራት ላይኔ ስላደረሰው ግፍና ጭካኔ ከእስር ቤት ከወጣ በዋላ ሲጠየቅ ያለው ነገር ቢኖር ያኔ ሐይማኖት የለኝማ ነበር ሰይጣን አሳስቶኝ ነው የሚል መልህክት ያለው የይቅርታ አጠያየቅ መንገድ ነው የተጠቀመው። በሱ ትህዛዝ ግን በግፍ የሞቱት ሰዎች ደም በየሄደበት ይክተለዋል ጊዜው ይረዝማል እንጂ ለፍርድ መቅረቡ የማይቀር ሀቅ ነው።

የወያኔው መሪ አቶ መለሰ ዜናዊ በጠና ታመዋል በ G-8 ስብሰባ ላይ በጋዜጠኛ አበበ ገላው በደረሰባቸው ውርደት የተነሳ ከአንድ ወር በላይ በሚድያ ያልታዩት አቶ መለስ በደረሰባቸው እመም ለህክምና ቤልጂየም ብራስልስ ቆይተው በ G-20 ስብስባ ሜክሲኮ ላይ የፊት ገፃቸውና ሙሉ ስውነታቸው መሳሳት በጠና መታመማቸውን አሳብቆባቸዋል:: ከክሳታቸው ከመገርጣታቸው የተነሳ እኔ ሳያቸው በእውነቱ እድሜ ማራዘሚያ የሚወስዱ ነው የመሰሉኝ ።ታድያ እኚ ወንበዴ የሰይጣን ጆሮ ይስማውና ቢሞቱስ ኢትዮጵያ ትበታተናለች ብሎ የሚያስብ ካለ ተሳስታል እንዲያውም ሊለያየን ሊበታትነን የጣረውን በፅበል የማይወታው ሴይጣን ተገላገልነው ማለት አይደለም።

የኢትዮጵያ ሕዝብ በዚህ ዘረኛና አንባገነን መሪ ብዙ ፍዳውን አይትዋል ብዙ ተሰቃይታል ባብዛኞቻችንም ሐገራችንን ጥለን በስደት እየተሰቃየን ነው። መብታችንን በመጠየቃችን ብቻ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥረናል ታስረናል አሸባሪ ተብለናል ብዙዎችም ተገለዋል። ታዲያ ይህ አንባገነን የወያኔ መሪ መለሰ ዜናዊ ህመሙ ፅንቶ ወይም በሕዝብ ትግል ስልጣኑን ቢለቅና ስለፈፅማቸው ግፍና መከራ ለምንስ እንደ ፈፅማቸው ቢጠየቅ ሰይጣን አሳስቶኝ ነው ሳይል ይቀራል ነገር ግን የትኛውም ምክንያት እነዚ ወንበዴዎችን ከነመርያቸው ከተጠያቂነትና ከፍርድ ሊያመልቱ አይችሉም ። ወይ የጋዳፊ ካልሆነም የሙባረክ እጣ እንደሚገጥማቸው እነሱም የሚያቱት አይመስለኝም ታዲያ ያኔ ስይጣን አሳስቶኝ ነው ሀይማኖት ስላልነበረኝ ነው….. ምናምን የሚል ምክንያት ከተጠያቂነት አያድናቸውምና።

No comments:

Post a Comment